Gofa zone pp youth league office

Gofa zone pp youth league office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gofa zone pp youth league office, Political organisation, Awassa.

በምርጫ ሂደት ውስጥ የወጣቱ ትውልድ ተሳትፎ የማንኛውም አገር የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እና የወደፊት እጣ ፈንታ ወሳኝ አካል ነው ። ወጣቶች አዳዲስ ሀሳቦችን ማምጣት፣ ለውጥን ማፋጠን እና ...
16/05/2026

በምርጫ ሂደት ውስጥ የወጣቱ ትውልድ ተሳትፎ የማንኛውም አገር የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እና የወደፊት እጣ ፈንታ ወሳኝ አካል ነው ።

ወጣቶች አዳዲስ ሀሳቦችን ማምጣት፣ ለውጥን ማፋጠን እና የህብረተሰቡን ድምፅ ማጉላት ይችላሉ


በዚህም ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የላሃ ከተማ ወጣቶች ለብልፅግና ፓርቲ ድምጻቸውን ለመስጠት በሁሉም ማህበራዊ መሰረት የድምፅ መስጫ ቀኑን በንቃት እየተጠባበቁ ይገኛሉ ።

#ፓርቲያችን ብልጽግና ነው!
#ምልክታችን የስንዴ ነዶ ነው!
#ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር!
#ብልጽግና ፓርቲን ይምረጡ!

ወጣቱ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በዕውቀት እራሱንና ሀገሩን ለመቀየር ለሚያደርገው ጉዞ ብልጽግና ፓርቲ ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደርጋል። አቶ ቦረና ቦላዶየሀገራችን የለውጥ ሞተር፣ የአዲስ አስተሳሰ...
16/05/2026

ወጣቱ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በዕውቀት እራሱንና ሀገሩን ለመቀየር ለሚያደርገው ጉዞ ብልጽግና ፓርቲ ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደርጋል። አቶ ቦረና ቦላዶ

የሀገራችን የለውጥ ሞተር፣ የአዲስ አስተሳሰብ ምንጭ እና የነገዋ ሀገር እጣ ፈንታ ወሳኝ አካል ነው። ድህነትን ለማሸነፍ ነገን መጠበቅ ሳይሆን ዛሬውኑ መንቀሳቀስ መጀመር ለነገ የማይባል የቤት ስራ እንደሆነ ብልጽግና ፓርቲ ለወጣቱ ልዩ ትኩረት ይሰጣል።

የፈጠራ ስራ እና የስራ ፈጣሪነት መንፈስ
​የስራ እድልን ከመጠበቅ ይልቅ የስራ ፈጣሪነትን መንገድ በመምረጥ ወጣት ሚሊየነር መፍጠር የፓርቲያችን ተቀዳሚ ግቡ ነው።

​በትናንሽ ጅምሮች በአገር በቀል እውቀቶች እና በአካባቢው በሚገኙ ግብዓቶች ላይ በመመስረት አዳዲስ እሴቶችን መፍጠር የድህነት ቅነሳ ዋነኛው መፍትሔ ለማምጣት የወጣቱን ነቁ አዕምሮ ትልቅ የእድገት ሀብታችን ነው።

ወጣቱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን፣ የዲጂታል ሚዲያዎችን እና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን በመጠቀም ለአካባቢያዊ ችግሮች አለምአቀፋዊ መፍትሄዎችን ማመንጨት ይችላል በሚል ፓርቲያችን ጽኑ አቋም አለው።

ብልጽግና መምረጥ የነገ ሀገር ተረካቢ ማፍራት ነው !!!

አቶ በረና ቦላዶ
በጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ

‎በመሎ ጋዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት ስፖርት ለጤናችን፣ ብልጽግና ምርጫችን" በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የይምረጡ ቅስቀሳ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።‎ግንቦት 8...
16/05/2026

‎በመሎ ጋዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት ስፖርት ለጤናችን፣ ብልጽግና ምርጫችን" በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የይምረጡ ቅስቀሳ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ግንቦት 8/2018 ዓ/ም የመሎ ጋዳ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት

‎በጎፋ ዞን የመሎ ጋዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት "ስፖርት ለጤናችን ፣ብልጽግና ምርጫችን" በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የይምረጡ ቅስቀሳ አካል የሆነው ሁለተኛ ዙር በዎምባ ከተማ ተካሄዷል።

‎ማስ ስፖርት ከግለሰብ ጤና ባለፈ ማህበረሰባዊ መስተጋብር ትስስርን የሚያጠናክር፣ የአንድነትና የጋራ ዓላማ ስሜትን የሚፈጥር ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ነው።

‎ስፖርት ጤናማ ማህበረሰብ ከመገንባት ባሻገር ብልጽግና ፓርቲ ልዩ ትኩረት ሰጥተው ከሚሰራባቸው ወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ለማጎልበት ትልቅ አቅም የሚሆን ነው።

‎በመርሐግብሩ የመሎ ጋዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ዮሴፍ ብርሃኑ፣ የወረዳው አሰተባባሪ አካላት፣ አመራሮች፣ የቴኳንዶ ክለብ አስልጣኞች፣ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች የተሳተፉበት ሲሆን መጪው ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ያላቸውን ዝግጁነት ገልጸዋል።

‎ዘገባው፦ የመሎ ጋዳ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ነው።

‎ኮሚዩኒኬሽን_የሕዝብና_የመንግሥት_አይንና_ጆሮ_ነው!

በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ ስፖርት ለጤናዬ ብልጽግና ምርጫዬ በሚል መርህ ቃል ማስ ስፖርት ተካሄደ በወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት የማስ ስፖርቱ የተደረገ ሲሆን በቦታው የዞን፣የከተማ አመራሮች እን...
16/05/2026

በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ ስፖርት ለጤናዬ ብልጽግና ምርጫዬ በሚል መርህ ቃል ማስ ስፖርት ተካሄደ

በወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት የማስ ስፖርቱ የተደረገ ሲሆን በቦታው የዞን፣የከተማ አመራሮች እንዲሁም የስፖርተ ቡድኖች እና የክንፉ አባላት ተገኝተዋል ::

በኦይዳ ወረዳ " ፣  " በሚል መሪ ቃል በወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት ደማቅ የማስ ስፖርት ተካሄደ።ግንቦት 7/2018 ዓ.ምበጎፋ ዞን ኦይዳ ወረዳ 7ኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የ...
15/05/2026

በኦይዳ ወረዳ " ፣ " በሚል መሪ ቃል በወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት ደማቅ የማስ ስፖርት ተካሄደ።

ግንቦት 7/2018 ዓ.ም

በጎፋ ዞን ኦይዳ ወረዳ 7ኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ ያዘጋጀው የማስ ስፖርት መርሃ ግብር " ፣ " በሚል መሪ ቃል በሸፊቴ ከተማ በድምቀት ተካሂዷል።

በዕለቱ በተካሄደው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ላይ የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አመራር ወጣት ተካልኝ ጴጥሮስ፣ የከተማዋ ወጣቶች እና በርካታ የስፖርት ባለሙያዎች በአንድነት ተሳትፈዋል።



ስፖርት የአካልና የአእምሮ ጤናን በመገንባት ንቁና ምርታማ ዜጋን እንደሚፈጥር ሁሉ፣ ወጣትነትም የአንድ ሀገር የልማትና የለውጥ ሞተር ነው።

ዛሬ በሸፊቴ አደባባይ የታየው ስፖርታዊ አንድነትና የወጣቶች መነቃቃት፣ ነገ በምርጫ ካርዳችን ለምናረጋግጠው ብሔራዊ ስኬት ትልቅ ማሳያ ነው። ጤናማና ንቁ ወጣት ለልማት እንደሚተጋ ሁሉ፣ በሰከነና በበሰለ ፖለቲካ የሚመራው ብልፅግና ፓርቲም ኢትዮጵያን በአፍሪካ አልፎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተምሳሌት የሆነች ሀገር ለማድረግ በትጋት እየሰራ ይገኛል። ይህ የወጣቶችና የፓርቲው ቅንጅት ሀገራችንን ወደ ተመኘነው የብልፅግና ማማ የሚያሸጋግር ጽኑ መሠረት ነው።

፣ !


#ምርጫችን፦ ብልፅግና ፓርቲ!
#ምልክታችን፦ የስንዴ ነዶ!
#ራዕያችን፦ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገርነት ማሸጋገር!

! !
#ዘገባው፦

13/05/2026
በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ እና ኦይዳ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት የክንፉ አባላትና ደጋፊዎች በማሳተፍ "አከባቢያን ከቆሻሻ አፀዳለው ብልፅግናን እመርጣለሁ " በሚል መሪ ...
13/05/2026

በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ እና ኦይዳ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት የክንፉ አባላትና ደጋፊዎች በማሳተፍ "አከባቢያን ከቆሻሻ አፀዳለው ብልፅግናን እመርጣለሁ " በሚል መሪ ቃል የፅዳትና የምርጫ ቅስቀሳ ስራ ተካሄደ ።

ጠንካራ የወጣቶች ክንፍ ለጠንካራ ፓርቲ!!

የዛላ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በወጣቶችና በጎ አ/ጽ/ቤት እና የወጣቶ ክንፍ ጽ/ቤት "በወጣቶች ነቃ ተሳትፎ ሠላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ" በሚል መሪ ቃል የወጣቶች ንቅናቄ መድረክ ተ...
01/05/2026

የዛላ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በወጣቶችና በጎ አ/ጽ/ቤት እና የወጣቶ ክንፍ ጽ/ቤት "በወጣቶች ነቃ ተሳትፎ ሠላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ" በሚል መሪ ቃል የወጣቶች ንቅናቄ መድረክ ተካሄዷል።

ሚያዝያ 23/2018 ዓ/ም(ዛላ ወረዳ ብ/ፓ/ወጣቶች ክንፍ ሚዲያ)

በመድረኩ የተገኙት የዛላ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፍ አቶ አብድቄ አውቴ እንደገለፁት ሀገራችን ኢትዮጵያ የጀመረችው የማንሰራራት ጉዞ ለማጠናከርም ሆነ የነገይቷን ኢትዮጵያ ለማስቀጠል የወጣቶች ሚና የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

አያይዘውም 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማሳካት ያነገባቸው የሂደት እና የስኬት ግቦችን በማጠናከር የተጀመረውን የምርጫ ቅስቀሳ ሂደት ውስጥ የነቃ ተሳትፎ በማሳየት የፓርቲያችን ምልክት የሆነውን "ስንዴ ነዶ" ለማስተዋወቅ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስበዋል።

የዛላ ወረዳ ወጣቶችና በጎ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት መምህሩ ማልዳዬ እንደገለጺት ወጣቶች ሀገር ተረካቢ ብቻ ሳይሆን የሀገር ባለቤት መሆናቸውን ገልጸዋል።

የወጣቶች ሚና ለሁለንተናዊ ብልጽግና ወሳኝ ነው ያሉት ወጣት መምህሩ የኢትዮጵያ ዘላቂ ከፍታ በእናንተ ይረጋገጣል ስሉ ገልጸዋል።

የዛለ ወረዳ ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ ዘርፍ ኃላፊ ወንድም ጎጃሜ ጎላ በበኩላቸው የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ሰላማዊ፣ፍትሃዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል።

አያይዘውም ወጣቶች ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የሚደረገውን የብልጽግና ትልሞችን በማጉላት ብልጽግናን ይምረጡ ቅስቀሳ በይበልጥ ማጠናከር ይገባል ብሏል።

በጎፋ ዞን ኦይዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት የ2018 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ  ሂደት ውስጥ የወጣቶች ሚና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥና የሀገርን ቀጣይ አ...
30/04/2026

በጎፋ ዞን ኦይዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት የ2018 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ውስጥ የወጣቶች ሚና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥና የሀገርን ቀጣይ አቅጣጫ ለመወሰን እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ተገለፀ።

ሚያዝያ፦ 22/2018ዓ.ም

በጎፋ ዞን ኦይዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት የ2018 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ውስጥ የወጣቶች ሚና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና የምርጫ ማነፌስቶ ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሄዷል ።

የመርሃ-ግብሩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኦይዳ ወረዳ ም/አስተዳደርና ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ነብሮ የዚህ መድረክ ዋነኛ ዓላማው በየደረጃ የሚገኙ ወጣቶች መጪው 7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በምዝገባ ወቅት ያስመዘገበውን ጠንካራ ጎን በምርጫ ቅስቀሳ ወቅትም አካባቢያዊ ፣ሀገራዊ፣አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎችንና ከለውጡ በኋላ የተመዘገቡ ስኬቶችን በተገቢው ግንዛቤ ወስጥ በማስገባት የማይተካ ሚና እንዲወጡ የጋራ ተግባቦት ለመፍጠር እንደሆነ አብራርቷል ።።

''ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር'' በሚል መሪ ሀሳብ በወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት አዘጋጅነት የ7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ መወዳደሪያ ምልክት፤ የፓርቲው የምርጫ የማስተዋወቅ ላይ ለተገኙት ወጣቶች ትልቁና ሁሉን አቀፍ ፓርቲ የሆነዉን ብልጽግና ፓርቲ እንዲመርጡ ጥሪያቸውን አስተላልፏል ።

የኦይዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና ህዝብ ግኑኝነት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አበዛሽ አልቶ በበኩላቸዉ ብልጽግና ፓርቲ በባለፉት ዓመታት የተለያዩ ፈተናዎችን በድል በማሻገር ዘርፈ ብዙ ተግባራትና በርካታ ትሩፍቶች ለህዝቡ ተጠቃሚነትና ተደራሽነት ከማትረፉ በዘለለ ብዙ የተሞክሮ ተምሳሌቶችን ያተረፈ መሆኑን በመርሃ-ግብሩ ላይ ገልጿል ።

የኦይዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት አቶ ተካልኝ ጴጥሮስ የ2018 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ሂደት ውስጥ የወጣቶች ሚና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና የፓርቲው የምርጫ መነፌስቶ ማስተዋወቂያ ዙሪያ የተዘጋጀዉን በማቅረብ 7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን በየደረጃ የሚገኙ የሁሉም ወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተጠቅሶ ቀጣይ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማረጋገጥ በዘርፉ ብዙ ተግባራት ላይ ወጣቶች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።

የመድረኩ ተሳታፊ ወጣቶች አስተያየታቸዉን ስሰጡ 7ኛው ዙር ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ ቃል ገብቷል::

በመርሃ-ግብሩም የኦይዳ ወረዳ ም/አስተዳደርና ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ነብሮ፣ የወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና ህዝብ ግኑኝነት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አበዛሽ አልቶ ፣ የወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘገዬ ዘካሪያስ ፣ የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ቅ/ጸ/ቤት ኃላፊዎች፣ የወረዳው ወጣቶች ክንፍ ሥራ አስፈፃሚዎች እና ከእያንዳንዱ ቀበሌያት የተወጣጡ የወጣቶች ክንፍ አመራሮች ተገኝተዋል።

በጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/"ቤት አማካኝነት"ስፖርት ለጤናችን"ብልጽግና ፓርቲ ምርጫችን በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ አባላት በሣውላ ከተማ የምርጫ ቅስቀሳ...
29/04/2026

በጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/"ቤት አማካኝነት"ስፖርት ለጤናችን"ብልጽግና ፓርቲ ምርጫችን በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ አባላት በሣውላ ከተማ የምርጫ ቅስቀሳና የእግር ኳስ ወዳጅነት ጨዋታ አደረጉ።

ሚያዝያ 21/2018 ዓ/ም

"ስፖርት ለጤናችን ፣ ብልጽግና ፓርቲ ምርጫችን"በሚል መሪ ቃል የብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ አባላት የምርጫ ቅስቀሳ የእግርኳስ ወዳጅነት ጨዋታ አድርገዋል።

በዞን ማዕከል የወጣት አደረጃጀት አመራሮች እና በሣውላ ከተማ የወጣት አደረጃጀት አመራሮች መካከል የተደረገው የእግር ኳስ ውድድር በሣውላ ከተማ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወንድም ይሁን ደምሴ በመገኘት የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የወጣት አደረጃጀት አመራሮች የእግር ኳስ ውድድር አስጀምረዋል።

በመረሃ ግብሩ የጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወንድም ይሁን ደምሴ እንዲሁም የጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ክሩቤል ይስሐቅ ጨምሮ የዞኑ/ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።



Address

Awassa

Telephone

+251930619796

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gofa zone pp youth league office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share