01/08/2026
የመሎ ኮዛ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ወጣቶች ክንፍ የ2019 ፈጻሚ ማዘጋጃ መድረክ አካሄደ
ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም
በጎፋ ዞን በመሎ ኮዛ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ወጣቶች ክንፍ የ2018 ዓ.ም አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 ፈጻሚ ማዘጋጃ መድረክ አካሂዷል ።
የግምገማ መድረኩን የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙኔ በትሶ ያስጀመሩት ስሆን የወጣቶችን አደረጃጀት በማጠናከር ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የወጣቶች ክንፍ ኃላፊ አቶ አየለ አማሬ የ2018 ዓ.ም አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ አቅርበው ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎበታል ።
በውይይቱም በቀጣይ በትኩረት ሊሰሩ ሚገቡ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ተደረሶ መድረኩ ተጠናቋል ።