Ha/Qu/Loosu, Loosisiranotena Loosasinete Biddishsha ሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አ/ሠራተኛ መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • Ha/Qu/Loosu, Loosisiranotena Loosasinete Biddishsha ሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አ/ሠራተኛ መምሪያ

Ha/Qu/Loosu, Loosisiranotena Loosasinete Biddishsha
ሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አ/ሠራተኛ መምሪያ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ
Hawaasi Quchumi Gashshooti Loosu, loosisiranotena Loosasinete Biddishsha

የመሀል ክፍለ ከተማ የሥራ፣ አሠሪና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት በክፍለ ከተማዋ ባለፉት 2 ወራት የተከናወነውን የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም ገምግሟልነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | ሀዋሳየመሀል ክፍለ ከተማ...
03/09/2026

የመሀል ክፍለ ከተማ የሥራ፣ አሠሪና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት በክፍለ ከተማዋ ባለፉት 2 ወራት የተከናወነውን የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም ገምግሟል

ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

የመሀል ክፍለ ከተማ የሥራ፣ አሠሪና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት በክፍለ ከተማዋ ባለፉት 2 ወራት የተከናወነውን የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም የገመገመ መድረክ አካሂዷል።

በግምገማ መድረኩ የሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ኃላፊ ክቡር አቶ ሽታ ኤብሶ፣ የሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ም/ኃላፊና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ታምሬ ተፈራ፣ የመሀል ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮሐንስ ኤርምያስ፣ የክፍለ ከተማዋ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም የሥራ ዕድል ፈጠራ ቴክኒክና ስትሪንግ ኮሚቴ አባላት ተሳትፈዋል።

በግምገማው ወቅት የ2 ወራቱ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም በዝርዝር በመገምገም የተመዘገቡ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና በቀጣይ የሚወሰዱ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ተለይተው ተቀምጠዋል። በተጨማሪም የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎችን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተሰጥተዋል።

የሥራ ዕድል ፈጠራን በማስፋት፣ ወጣቶችን በማብቃትና የክፍለ ከተማዋን ኢኮኖሚያዊ አቅም በማጠናከር የተጨባጭ ውጤት ለማምጣት ሥራው በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለወጣቶቻችን!

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ፦

🔵 ፌስቡክ (Facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ አሰሪና ሰራተኛ መምሪያ አስተባባሪነት የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ከኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመቀናጀት፣ በሀዋሳ ከተማ ለተለያዩ ወጣቶች የሥራ...
03/09/2026

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ አሰሪና ሰራተኛ መምሪያ አስተባባሪነት የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ከኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመቀናጀት፣ በሀዋሳ ከተማ ለተለያዩ ወጣቶች የሥራ ፈጠራ ክህሎት ስልጠና ተሰጠ።

ስልጠናው ከሀዋሳ ከተማ ሰባቱም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ ወጣቶች የተሰጠ ሲሆን፣ ወጣቶች የሥራ ፈጠራ አስተሳሰብና ክህሎት እንዲያዳብሩ፣ ያላቸውን እውቀትና አቅም ወደ ምርታማ የሥራ ዕድል እንዲቀይሩ እና የራሳቸውን የሥራ ዕድል መፍጠር እንዲችሉ ያለመ ነው።

የሀዋሳ ከተማ ሥራ አሰሪና ሰራተኛ መምሪያ ም/ኃላፊ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ታምሬ ተፈራ በመልዕክታቸው፣ ወጣቶች የሥራ ፈላጊነትን ብቻ ሳይሆን የሥራ ፈጣሪነትንም እንደ አማራጭ በመውሰድ ያላቸውን ክህሎትና እውቀት ተጠቅመው ለራሳቸውና ለሌሎች የሥራ ዕድል መፍጠር እንደሚገባቸው ገልጸዋል። የሥራ ፈጠራ ሥርዓቱን ለማጠናከር ወጣቶች፣ መንግስትና የልማት አጋሮች በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም አመልክተዋል።

የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወጣት በቃሉ መሠረት በመልዕክታቸው፣ ወጣቶች የሀገርና የክልል ኢኮኖሚያዊ እድገት ዋነኛ አቅም በመሆናቸው የሥራ ፈጠራ ክህሎታቸውን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የወጣቶችን አቅም ወደ ተጨባጭ የሥራ ዕድል ለመቀየር ተከታታይ ስልጠናዎችና የተግባር ድጋፎች እንደሚያስፈልጉ በመግለጽ፣ የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ወጣቶችን በእውቀት፣ በክህሎትና በዕድል ለማገናኘት የሚያደርገውን ስራ እንደሚያጠናክር አስታውቀዋል።

የኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ሪጅናል ኮርድኔተር አቶ ጌትነት ሳሙኤል በበኩላቸው፣ የሥራ ፈጠራ ስልጠናው ወጣቶች የሚያስቡትን ሀሳብ ወደ ተግባራዊ የንግድ ሥራ ለመቀየር የሚያግዛቸውን እውቀትና ክህሎት ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። ተቋሙ ወጣቶችን በሥራ ፈጠራና በኢንተርፕሪነርሺፕ ለማብቃት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር መስራቱን ጠቁመው፣ በቀጣይም በሲዳማ ክልል ያሉ ወጣቶች ተጠቃሚ የሚሆኑበት ተመሳሳይ ስልጠናዎች እንደሚቀጥሉ አመልክተዋል።

ስልጠናው የሲዳማ ክልል ወጣቶች ማህበርና ኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት በጋራ በክልል ደረጃ 1,000 ወጣቶችን ለማሰልጠን ከያዙት እቅድ አካል ነው። በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው ይህ የጋራ ትብብር በቀጣይ በሲዳማ ክልል አራቱም ዞኖች በተመሳሳይ ሁኔታ የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም በርካታ ወጣቶች በሥራ ፈጠራ እውቀትና ክህሎት በመታገዝ የራሳቸውን የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ፣ ለሌሎች ወጣቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥሩ ስኬታማ የሥራ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ የሚያግዝ የሥልጠናና የትብብር ሂደት መሆኑ ተመልክቷል።

ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለወጣቶቻችን!!

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ፦

🔵 ፌስቡክ (Facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑ ተገለጸነሐሴ 27/2018 ዓ.ም | ሀዋሳይህ ሀሳብ የተገለጸው ዛሬ በባህል አደራሽ ክፍለ ከተማ በተካሄደው የድጋፍ...
02/09/2026

ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑ ተገለጸ

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

ይህ ሀሳብ የተገለጸው ዛሬ በባህል አደራሽ ክፍለ ከተማ በተካሄደው የድጋፍና ክትትል መድረክ ላይ ሲሆን፣ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ኃላፊ ክቡር አቶ ሽታ ኤቢሶ እና የመምሪያው ምክትል ኃላፊና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ታምሬ ተፈራ በመገኘት ውይይቱን መርተዋል።

በመድረኩም ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር በሀገር ደረጃ የተጀመሩ ጥረቶችን በተዋረድ ያሉ መዋቅሮች በተቀናጀና በጠንካራ አሠራር ማስቀጠል እንደሚገባ ተገልጿል።

በተጨማሪም በዘርፉ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግና ሥራ ፈላጊ ወጣቶችን ወደ ሥራ ለማስገባት ከርየታ ጀምሮ ወጣቶች ወደ ሥራ እስኪሰማሩ ድረስ ያሉ ሂደቶችን በቅርበት በመከታተል መሥራት አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል።

ሁሉም አመራሮችም የሥራ ዕድል ፈጠራን “የእኔም ሥራ ነው” በሚል አመለካከት በትኩረት ሊተገብሩት እንደሚገባ ተገልጿል።

በባህል አደራሽ ክፍለ ከተማ እስካሁን የተከናወኑ ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸው ተጠቅሶ፣ ይህንን ጥረት በቀጣይነት ማስቀጠል እንደሚገባ በመድረኩ የመደምደሚያ ሀሳብ ተሰጥቷል።

ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለወጣቶቻችን!!!

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ፦

🔵 ፌስቡክ (Facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

በምስራቅ ክፍለ ከተማ የ100 ቀን እቅድ ክንውንና የእስከ አሁን የአፈጻጸም ሂደት ግምገማ ተካሄደነሐሴ 27/2018 ዓ.ም | ሀዋሳየሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ የድጋ...
02/09/2026

በምስራቅ ክፍለ ከተማ የ100 ቀን እቅድ ክንውንና የእስከ አሁን የአፈጻጸም ሂደት ግምገማ ተካሄደ

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ የድጋፍ ቡድን በምስራቅ ክፍለ ከተማ ስራ አሰሪና፣ ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት የ100 ቀን እቅድ ክንውን እና እስከ አሁን ያለውን አፈጻጸም ገመገመ።

በግምገማው የእቅዱ አፈጻጸም ሂደት፣ የተመዘገቡ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና በቀጣይ ሊሰጣቸው የሚገባ ልዩ ትኩረት የሚሹ ተግባራት በስፋት ተመልክተዋል።

በቀጣይም በተለይ ትኩረት ተሰጥቷቸው መሰራት በሚገባቸው ተግባራት ላይ በቅንጅትና በትብብር በመረባረብ፣ የተያዙ ዕቅዶችን በተሻለ አፈጻጸም ለማሳካት በመግባባት የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።

ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለወጣቶቻችን!!!

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ።

🔵 ፌስቡክ (Facebook):

https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

በሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም ድጋፋዊ ግምገማ ተካሄደ27/12/2018 ዓ.ም | ሀዋሳየሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ አስተዳደር የሥራ አሠሪና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ከሀዋሳ ከተማ ...
02/09/2026

በሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም ድጋፋዊ ግምገማ ተካሄደ

27/12/2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

የሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ አስተዳደር የሥራ አሠሪና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ኃላፊዎች ጋር፣ የክ/ከተማው ስትሪንግ ኮሚቴና ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸምና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ድጋፋዊ ግምገማ ተካሄደ።

በግምገማው የቀጣዩን 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት፣ የሥራ ፈላጊዎችን የመለየትና የመመዝገብ ሂደት፣ የባለድርሻ ተቋማት የሥራ ዕድል ፈጠራ ግብ ስምምነት፣ እንዲሁም ሌሎች የመንግስት ድጋፍና አገልግሎቶች በክፍለ ከተማው በተግባር እንዲደርሱ ስለሚያስፈልጉ ቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄዷል።

በተጨማሪም በክፍለ ከተማው ያሉ የሥራ ዕድል ፈጠራ አቅሞችን በመለየትና የፀጋ ልየታ ማድረግ፣ የሥራ ፈላጊዎችን ፍላጎትና አቅም በተገቢው መልኩ በማጣመር ዘላቂና ውጤታማ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተመላክተዋል።

የሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ኃላፊ ክቡር አቶ ሽታ ኤብሶ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸሙን የበለጠ ለማጠናከር የሚያስፈልጉ የድጋፍና የክትትል አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

በመጨረሻም የሥራ ዕድል ፈጠራ ዕቅዶች በተጨባጭ ውጤት እንዲመዘኑ፣ ተቋማት በቅንጅትና በትብብር እንዲሠሩ እና ለሥራ ፈላጊዎች የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ዘላቂና ውጤታማ እንዲሆኑ በቀጣይ ጊዜ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ተገልጿል።

ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለወጣቶቻችን!!!

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ።

🔵 ፌስቡክ (Facebook):

https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

በምስራቅ ክፍለ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም አጠቃላይ ግምገማ ተካሄደነሐሴ 25፤ 2018 ዓ.ም | ሀዋሳበሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የከተማ አመራሮችና የሥራ ዕድል ፈጠ...
01/09/2026

በምስራቅ ክፍለ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም አጠቃላይ ግምገማ ተካሄደ

ነሐሴ 25፤ 2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የከተማ አመራሮችና የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም አጠቃላይ ግምገማ ተካሂዷል።

በግምገማው ወቅት በተያዘው ዕቅድ መሠረት የተከናወኑ ተግባራት፣ የተመዘገቡ ውጤቶች፣ በአፈጻጸም ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችና ተግዳሮቶች በስፋት ተገምግመዋል። በተጨማሪም የታዩ ክፍተቶችን ለማረም፣ የተገኙ ውጤቶችን ለማስቀጠልና አፈጻጸሙን ይበልጥ ለማሻሻል በቀጣይ መከናወን በሚገባቸው ተግባራት ላይ ውይይት ተደርጓል።

በተለይም የሥራ ዕድል ፈጠራ ሂደቱን ይበልጥ ለማጠናከር፣ ወጣቶችና ሴቶችን በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በማሰማራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ፣ እንዲሁም የተፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን በዘላቂነት ለማስቀጠል በቀጣይ በትኩረት መሰራት ባለባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመጨረሻም የሥራ ዕድል ፈጠራ ዕቅዶችን በተቀናጀ አሠራር፣ በተጠያቂነትና በትጋት በመፈጸም ተጨማሪ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር፣ የተፈጠሩትን የሥራ ዕድሎች ለማስቀጠልና ዘላቂ ውጤት ለማስመዝገብ በጋራ መሥራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለወጣቶቻችን !!!

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ።

🔵 ፌስቡክ (Facebook):

https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

ሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራ የ50 ቀናት አፈጻጸምን ገመገመነሐሴ 21/2018 ዓ.ም | ሀዋሳየሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ በክፍለ ከተማዋ የተከናወነውን የ50 ቀናት የሥራ ዕድል ፈጠ...
27/08/2026

ሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ የሥራ ዕድል ፈጠራ የ50 ቀናት አፈጻጸምን ገመገመ

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

የሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ በክፍለ ከተማዋ የተከናወነውን የ50 ቀናት የሥራ ዕድል ፈጠራ አፈጻጸም ገምግሟል።

በግምገማ መድረኩ የሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሽታ ኤብሶ፣ የሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽጉጠ ሹራሞ፣ የመምሪያው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ታምሬ ተፈራ፣ የሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ ቴክኒክና ስትሪንግ ኮሚቴ አባላት ተሳትፈዋል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ሽታ ኤብሶ ሀዌላ ቱላ ክፍለ ከተማ በሥሩ ባሉ 12 ቀበሌያት የሚገኙ ወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ መልኩ በቅንጅትና በትብብር መሥራት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል። በተጨማሪም የታቀዱ የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባራት በጥራትና በውጤታማነት መፈጸማቸውን በጥልቀት መገምገም እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

በመድረኩ በተለይም፦

👉 እስከአሁን የተከናወነው የሥራ ፈላጊ ልየታ አፈጻጸምና ጥራት፤

👉 የግንዛቤ ማስጨበጫ፣ አጫጭር ሥልጠናዎችና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ሥልጠናዎች አፈጻጸም፤

👉 የተለዩ ሥራ ፈላጊዎችን በባዮሜትሪክስ የመመዝገብ ሂደት፤

👉 የሥራ ዕድል ፈጠራ አማራጮችና የጸጋ ልየታ፤

👉 የቁጠባና ብድር ስርጭት፣ አመላለስ እና በዚህ ረገድ የመጣው ለውጥና ውጤት፤

👉 እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ዋና ዋና ተግባራት በዝርዝር ተገምግመዋል።

ግምገማው የተገኙ ውጤቶችን በመለየት፣ ያሉ ክፍተቶችን በማረም እና ቀጣይ የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባራትን በተሻለ ቅንጅትና በተጠያቂነት ለማስፈጸም አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መሆኑ ተገልጿል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ፦

🔵 ፌስቡክ (Facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

የ2019 በጀት ዓመት የሥራ ስምሪት ዕቅድ በቅንጅት ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደነሐሴ 21፤ 2018 ዓ.ም | ሀዋሳበሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ...
27/08/2026

የ2019 በጀት ዓመት የሥራ ስምሪት ዕቅድ በቅንጅት ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ

ነሐሴ 21፤ 2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ የሥራ ስምሪት ዘርፍ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን በቅንጅት ለማሳካትና ከተለያዩ ኤጀንሲዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ለመሥራት ያለመ የምክክርና ውይይት መድረክ አካሂዷል።

የውይይቱን መድረክ የመሩት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሽታ ኤብሶ ሲሆኑ፣ በመድረኩ የመምሪያው ምክትል ኃላፊና የሥራ ስምሪት ዘርፍ ኃላፊ አቶ በዛብህ በላይ፣ የሥራ ሂደት አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

በውይይቱ ላይ በ2019 በጀት ዓመት በሥራ ስምሪት ዘርፍ ለማከናወን የታቀዱ ዋና ዋና የሥራ ዕቅዶች ቀርበው ተገምግመዋል።

ተሳታፊዎችም በቀረበው ዕቅድ ላይ ሀሳብና አስተያየቶቻቸውን በማቅረብ፣ ዕቅዱን በተሻለ መልኩ ለመፈጸም የሚያግዙ የአፈጻጸም ሀሳቦችና አቅጣጫዎችን አንስተዋል።

በተጨማሪም በ2019 በጀት ዓመት እስከዚህ ወቅት ያለው አፈጻጸም ቀርቦ በዝርዝር ተገምግሟል። ከአፈጻጸሙ የተገኙ ውጤቶች፣ የታዩ ተግዳሮቶችና በቀጣይ ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሔ አቅጣጫዎችም በውይይቱ ተካተዋል።

በቀጣይ የሥራ ስምሪት ተግባራትን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ፣ የተለያዩ አጋርና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ፣ በቅንጅትና በትብብር መሥራት እንዲሁም የተያዙ ዕቅዶችን በተግባር ለማሳካት የሚያስችሉ ስልቶች ተለይተዋል።

በመጨረሻም የመምሪያው ኃላፊ አቶ ሽታ ኤብሶ በሰጡት አቅጣጫ፣ በ2019 በጀት ዓመት ከተለያዩ ኤጀንሲዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት የታቀዱ ተግባራትን በትኩረትና በተጠያቂነት መፈጸም እንደሚገባ ገልጸዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ፦

🔵 ፌስቡክ (Facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም 4ኛ ዙር ማስጀመሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ​ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ምበመድረኩ የተገኙት ​የሀዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤ...
25/08/2026

የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም 4ኛ ዙር ማስጀመሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ

​ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም

በመድረኩ የተገኙት ​የሀዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ባቢሶ ባናታ በንግግራቸው፤ የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የሥራ አጥነትን ቁጥር በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

​ኃላፊው ፕሮግራሙ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት መመዘኛ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶችን በግልጽና በጥንቃቄ ሊመርጡ እንደሚገባ ገልጸዋል።

​የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የሥራ፣ አሰሪና ሠራተኛ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሽታ ኤቢሶ በበኩላቸው፤ በ4ኛ ዙር የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት 1 ሺህ 802 ወጣቶች ተጠቃሚ እንደሚደረጉ ገልጸዋል።

​የብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ዋና ዓላማ ወጣቶች በቀጣሪ ድርጅቶች ውስጥ ተግባራዊ የሥራ ልምምድ በማግኘት ወደ ቋሚ ቅጥር እንዲሸጋገሩና በከተማው ያለውን የሥራ አጥነት ቁጥር መቀነስ እንደሆነም ተናግረዋል።

​ኃላፊው የምልመላ ሂደቱ ፍትሃዊ፣ ግልጽና ተጠያቂነትን በጠበቀ መንገድ ሲከናወን ፕሮግራሙ የታለመለትን ዓላማ በተሻለ ሁኔታ እንደሚያሳካም አክለው ገልጸዋል።

​የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ከ12ኛ ክፍል በታች ትምህርታቸውን ያቋረጡ፣ ከ18 እስከ 29 ዓመት ዕድሜ ያላቸው፣ ምንም የሥራ ልምድ የሌላቸውና ከፍተኛውን ድርሻ ሴቶች የሚወስዱበት መሆኑንም ኃላፊው አስረድተዋል።

​የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ከሥራ ዕድል ፈጠራ ባሻገር በድህነት ቅነሳ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ገልጸው፣ ሥራውን ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ እንደሚያከናውኑ አረጋግጠዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ፦

🔵 Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድና እስካሁን ያለው አፈፃፀም ተገመገመነሐሴ 18፤ 2018 ዓ.ም | ሀዋሳበሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የ2019 በ...
24/08/2026

የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድና እስካሁን ያለው አፈፃፀም ተገመገመ

ነሐሴ 18፤ 2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድና እስካሁን ያለውን አፈፃፀም የሚመለከት ውይይት አካሂዷል።

መድረኩን የመሩት የመምሪያው ም/ኃላፊና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ታምሬ ተፈራ ሲሆኑ፣ በመድረኩ የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የሥራ ሂደት አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የ2019 በጀት ዓመት በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ለማከናወን የታቀዱ ዋና ዋና ተግባራትና በየሥራ ሂደቱ የተዘጋጁ ዕቅዶች ቀርበዋል። በቀረቡት ዕቅዶች ላይም ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት በመስጠት ዕቅዶቹ የበለጠ ውጤታማና ተግባራዊ እንዲሆኑ ግብዓት አቅርበዋል።

በተጨማሪም በ2019 በጀት ዓመት እስካሁን የተመዘገበው አፈፃፀም ቀርቦ፣ የተገኙ ውጤቶች፣ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችና በቀጣይ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በስፋት ተዳስሰዋል።

በቀጣይ የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራዎችን የበለጠ ውጤታማና ዘላቂ ለማድረግ፦

👉🔹 ያሉ የሥራ ዕድል ፈጠራ ጸጋዎችን መለየትና በአግባቡ መጠቀም፤

👉🔹 በርካታ ወጣቶችን ወደ የሥራ ዕድል ማስገባት፤

👉🔹 የመሥሪያና መሸጫ ቦታዎችን አጠቃቀም ማሻሻል፤

👉🔹 ለሥራ ፈጣሪዎች የገበያ ትስስርና የተለያዩ ድጋፎችን ማመቻቸት፤

👉🔹 የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋት የሥራ አፈፃፀሙን ማጠናከር፤ እና

👉🔹 የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመድረኩ እስካሁን ባለው አፈፃፀም ጥሩ ውጤቶችና መልካም ተሞክሮዎች መመዝገባቸው ተገልጾ፣ የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠልና የታቀዱ ተግባራትን በተጠናከረ መልኩ በመፈጸም የሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅስቃሴውን የበለጠ ውጤታማና ዘላቂ ለማድረግ ትኩረት እንደሚሰጥ ተጠቁሟል።

በመጨረሻም የመምሪያው ም/ኃላፊና የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ታምሬ ተፈራ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶች ውጤት ሊያመጡ በሚችሉ መልኩ የተዘጋጁ በመሆናቸው፣ በዕቅዱ መሠረት ሥራዎችን በትጋት፣ በቅንጅትና በተጠያቂነት ማከናወን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሥራ፣ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ

🌐 ለተጨማሪ መረጃዎችና ወቅታዊ ዜናዎች የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻችንን ይከተሉ፦

🔵 Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=61578511693825

#ሀዋሳ

Address

Sidaama
Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ha/Qu/Loosu, Loosisiranotena Loosasinete Biddishsha ሀዋሳ ከተማ ሥራ፣ አ/ሠራተኛ መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share