Sidama Football Federation

Sidama Football Federation ይህ የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይፋዊ ገጽ ነው

"Ayiidde Cambalaalla!"Hawalle 2019 M.D Sidaamu Daga Diru Soorro Fichee Cambalaallate Ayyaanira Keerunni iillishinke/iill...
14/03/2026

"Ayiidde Cambalaalla!"

Hawalle 2019 M.D Sidaamu Daga Diru Soorro Fichee Cambalaallate Ayyaanira Keerunni iillishinke/iillishinonke! Haaru

​እንኳን ለ2019 ዓ.ም የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ "ፊቼ-ጫምባላላ" በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!

​ፊቼ-ጫምበላላ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የመቻቻል ተምሳሌት የሆነ ታላቅ በዓል ነው። ይህ አዲስ ዓመት ለሁላችንም የሰላም፣ የብልጽግና እንዲሁም በስፖርቱ ዘርፍ የምንተጋበትና በስኬት የምንደምቅበት እንዲሆንልን የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል።

አይዴ ጫምባላላ

 #ማስታወቂያለከ17 ዓመት በታች ታዳጊ ምልመላ የተመዘገባችሁ በሙሉስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረዉ ከ17 ዓመት በታች ተዳጊወች እግር ኳስ ምልመላ ተመዝግባችሁ ስፈርቱን አሟልታችሁ ከተራ ቁጥ...
25/02/2026

#ማስታወቂያ

ለከ17 ዓመት በታች ታዳጊ ምልመላ የተመዘገባችሁ በሙሉ

ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረዉ ከ17 ዓመት በታች ተዳጊወች እግር ኳስ ምልመላ ተመዝግባችሁ ስፈርቱን አሟልታችሁ ከተራ ቁጥር 1-45 ያላችሁ ለአሰልጣኝ ይድነቃቸዉ ጥላሁን ስልክ ቁጥር 0916829181 እና ከተራ ቁጥር 46-90 ስማችሁ የተዘረዘረዉ ለአሰልጣኝ ሀበታሙ ዮናስ ስልክ ቁጥር 0919193090 በመደወል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ዉስጥ የሚትጫወቱበትን ቦታ እንድታሳዉቁ እና ቅዳሜ በቀን 21/06/2018 ዓ.ም ቡድን 1 (አንድ) ከተራ ቁጥር 1-45 ያላችሁ በኢንተርናሽናል ስታዲዬም ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ሙሉ ትጥቃችሁን አሟልታችሁ በሰዓቱ እንድትገኙ እና ቡድን 2 (ሁለት) ከተራ ቁጥር 46-90 ያላችሁ እሁድ በቀን 22/06/2018 ዓ.ም በተመሰሳይ ስታዲዬም በተመሳሳይ ሰዓት እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- በተጠቀሰዉ ስዓት የማይገኝ አና ተጥቁን ያላሟላ ተጨዋች የማናስተናግድ መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን፡፡

 #ማስታወቂያ​ለከ17 ዓመት በታች እግር ኳስ ተጫዋቾች በሙሉ፦​በሲዳማ ክልል እና አጎራባች ክልሎች የሚገኙ ከ17 ዓመት በታች ታዳጊዎች ለሀገር አቀፍ ውድድር እና ለ2026 G.C ለአፍሪካ ዋ...
15/02/2026

#ማስታወቂያ

​ለከ17 ዓመት በታች እግር ኳስ ተጫዋቾች በሙሉ፦

​በሲዳማ ክልል እና አጎራባች ክልሎች የሚገኙ ከ17 ዓመት በታች ታዳጊዎች ለሀገር አቀፍ ውድድር እና ለ2026 G.C ለአፍሪካ ዋንጫ ሀገርን ወክለው የሚሳተፉ ታዳጊ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን ስለምንመልም፤ እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር ከመስከረም 2002 ዓ.ም ወዲህ የተወለዳችሁና የፋይዳ መታወቂያችሁን ከታኅሣሥ 14/04/2018 ዓ.ም በፊት ያወጣችሁ ታዳጊዎች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ4 (አራት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት በመገኘት እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን።

​ማሳሰቢያ፦ ለምዝገባ ስትመጡ የፋይዳ መታወቂያችሁን ኦሪጅናል እና ኮፒ ይዛችሁ እንድትመጡ!!

​ለበለጠ መረጃ፦
0916064580
0935879990

ማስታወቂያ​ለካፍ ‘D’ ላይሰንስ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ፡-​የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ በመተባበር የ2018 በጀት ዓመት 5ኛ ዙር የካፍ ዲ ...
14/02/2026

ማስታወቂያ

​ለካፍ ‘D’ ላይሰንስ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ፡-

​የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ በመተባበር የ2018 በጀት ዓመት 5ኛ ዙር የካፍ ዲ ላይሰንስ ለመስጠት ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ሲሆን ስልጠናውን መሰልጠን እና መስፈርቱን የምታሟሉ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 (አስራ አምስት) ተከታታይ በስራ ቀናት ውስጥ የ10ኛ ክፍል ወይም ከዚያ በላይ ት/ት ማስረጃችሁን ኮፒ በማምጣት በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን፡፡

​ለሴት ሰልጣኞች ቅድሚያ ይሰጣል!!

​ለበለጠ መረጃ፡-
0916064580
0935879990

 #ማስታወቂያ​ለCAF “C” ላይሰንስ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ፦​የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት የCAF “C” ላይሰንስ ስልጠ...
10/02/2026

#ማስታወቂያ

​ለCAF “C” ላይሰንስ ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ፦

​የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት የCAF “C” ላይሰንስ ስልጠና መስፈርቱን የምታሟሉ እና የመመዝገቢያ ክፍያን መክፈል የምትችሉ አሰልጣኞች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሁለት ተከታታይ ቀናት ውስጥ እንድትመዘገቡ እየሳወቅን የመመዝገቢያ መስፈርቶች እንደሚከተሉት ይሆናሉ፦

1.​የዲ ላይሰንስ ያለው/ያላት።
2.​በዲ ላይሰንስ አገልግሎት ከሁለት ዓመት በላይ የሆነ።
3.​ከምስረታ ሊግ፣ ፕሪሚየር ሊግ (ወንድ/ሴት)፣ ከፍተኛ ሊግ (ወንድ/ሴት)፣ አንደኛ ሊግ (ወንድ)፣ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ፣ ክልል ከፍተኛ ዲቪዚዮን፣ አንደኛ ዲቪዚዮን፣ከ17 ዓመት በታች እና ፕሮጀክት ላይ እየሰራ ያለ እና የድጋፍ ደብዳቤ ማምጣት የሚችል/የምትችል።
4.​ለክልሉ በሙያው ያገለገለ/ያገለገለች ቅድሚያ ይሰጣል።
5.​የመመዝገቢያ ክፍያ 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ብር በወቅቱ የሚከፍል።

​ለበለጠ መረጃ፦
​0916064580
​0935879990

D ላይሰንስ ሰልጣኞች በሙሉየሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የአሰልጣኞች D ላይንስ ስልጠና መስጠቱ የሚታወስ ሲሆን ስለጠናውን ወስ...
29/12/2025

D ላይሰንስ ሰልጣኞች በሙሉ

የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የአሰልጣኞች D ላይንስ ስልጠና መስጠቱ የሚታወስ ሲሆን ስለጠናውን ወስዳችሁ የሰልጠናችሁበት ዲፕሎማ ሰርተፍኬት ስለመጣላችሁ እንዲትወስዱ ለማሳውቅ እንወዳለን።

በመሆኑም ከነገ ማክሰኞ ጅምሮ ወደ ሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በአካል በመቅረብ መውሰድ ትችላላችሁ።

 #ማስታወቂያ ለU15 እና U17 ሴት እና ወንድ እግር ኳስ ፕሮጀክቶች በሙሉከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ...
22/12/2025

#ማስታወቂያ

ለU15 እና U17 ሴት እና ወንድ እግር ኳስ ፕሮጀክቶች በሙሉ

ከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ በመተባበር 2018 ዓም የሚያዘጋጀው U 25 እና U 17 ሴት እና ወንድ እግር ኳስ ፕሮጀክት ውድድር ለመወዳደር የሚትፈልጉ በሲዳማ ክልል እና አጎራባች ክልሎች የሚትገኙ ፕሮጀክቶች የምዝገባ ጊዜ ከታህሳስ 13 እስከ ታህሳስ 25 ድረስ ብቻ በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ በሁሉቱም ፆታ እንድትመዘገቡ እያሳወቅን ከተጠቀሰው ቀን ውጪ የሚመጣ ማንኛውም ክለብ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳስባለን።

እንኳን ደስ አለን!የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን (ቀይ ቀበሮዎቹ) ኬንያን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለአፍሪካ ዋንጫ በማለፋቸው እንኳን ደስ አለን።በስፖርቱ ዘርፍ ታዳጊዎች...
02/12/2025

እንኳን ደስ አለን!

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን (ቀይ ቀበሮዎቹ) ኬንያን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለአፍሪካ ዋንጫ በማለፋቸው እንኳን ደስ አለን።

በስፖርቱ ዘርፍ ታዳጊዎች ላይ በርትተን ከሰራን እግር ኳሳችን በአህጉራዊና በዓለም አቀፋዊ መድረኮች ከፍ የሚልበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን ይህ ስኬት አመላካች ነው፡፡

የዛሬው ውጤት እንዲገኝ እኛም በክልል ደረጃ ውድድር ከማዘጋጀት ባሻገር ለብሔራዊ ቡድናችን ታዳጊዎችን በማስመረጥ በዚህ ታሪካዊ ድል አካል እንዲሆኑ በማድረጋችን እንደ ሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽኝ ላቅ ያለ ደስታ ተሰምቶናል።

ለውጤቱ መምጣት የድርሻችሁን ለተወጣችሁ አካላት ሁሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን።በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!

 #ማስታወቂያ ለሲዳማ ሊግ ተወዳዳሪዎች በሙሉከላይ በርዕሱ እንደተጠቀሰው የ2018 ዓም የሲዳማ ሊግ እግር ኳስ ውድድር ለመጀመር ዝግጅቱን ያጠናቀቅን ሲሆን የ2018 ዓም ውድድር ዓመት ምዝገባ...
01/12/2025

#ማስታወቂያ

ለሲዳማ ሊግ ተወዳዳሪዎች በሙሉ

ከላይ በርዕሱ እንደተጠቀሰው የ2018 ዓም የሲዳማ ሊግ እግር ኳስ ውድድር ለመጀመር ዝግጅቱን ያጠናቀቅን ሲሆን የ2018 ዓም ውድድር ዓመት ምዝገባ ከህዳር 22/03/2018 ዓም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 26/04/2018 ዓም ድረስ ብቻ ስለሆነ በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ዘውትር በስራ ሰዓት በአካል በመገኘት በደብዳቤ የተደገፈ መረጃ በማቅረብ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን።

ለበለጠ መረጃ-0916064580/0935879990 ይደውሉ

የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን

ሻምፒዮኖች ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ክልላችንን ወክለው ወጣቶች ኦሎምፒክ ውድድር ላይ በመሳተፍ አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች በሀዋሳ ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደርጓል።በአዲስ አበባ ከ...
03/11/2025

ሻምፒዮኖች ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

ክልላችንን ወክለው ወጣቶች ኦሎምፒክ ውድድር ላይ በመሳተፍ አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡ ስፖርተኞች በሀዋሳ ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደርጓል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተናጋጅነት ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ በተደረገው የኢትዮጵያ ታዳጊ ወጣቶች ኦሎምፒክ ውድድር ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የሲዳማ ክልል ልዑክ ቡድን በእግር ኳስ በሴትም በወንድም ሻምፒዮን መሆናቸው የሚታወስ ሲሆን ዛሬ ወደ ክልሉ መዲና ሀዋሳ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ልዑክ ቡድን ከእግር ኳስ ባሻገር በተሳተፈባቸው ከአስራ አምስት በላይ ስፖርት አይነት በርከት ያሉ የወርቅ የብር እና የነሐስ ሜዳሊያዎችን ማግኘት ችሏል።

በእግር ኳሱ ሻምፒዮን የሆኑት ታዳጊዎቹ ሀገራችን ኢትዮጵያን በመወከል አንጎላ ላይ በሚደረገው አፍሪካ አሀጉር አቀፍ ወጣቶች ኦሎምፒክ ላይ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።

በድጋሚ እንኳን ደስ አለን።

እንኳን ደስ አለን!የሲዳማ ክልል በሁለቱም ፆታ በወንዶቹም በሴቶቹም የታዳጊ ወጣቶች ኦሎምፒክ ወድድር በእግር ኳስ ሻምፒዮን ሆኗል።በአዲስ አበባ ከተማ እየተደረገ በሚገኘው የኦሎምፒክ ውድድር ...
01/11/2025

እንኳን ደስ አለን!

የሲዳማ ክልል በሁለቱም ፆታ በወንዶቹም በሴቶቹም የታዳጊ ወጣቶች ኦሎምፒክ ወድድር በእግር ኳስ ሻምፒዮን ሆኗል።

በአዲስ አበባ ከተማ እየተደረገ በሚገኘው የኦሎምፒክ ውድድር ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የሲዳማ ክልል ልዑክ ቡድን በእግር ኳሱ ዘርፍ ሻምፒዮን በመሆኑ እንኳን ደስ አለን። ቡድኖቹ ሻምፒዮን መሆን የቻሉት በሴቶቹ አዲስ አበበ ከተማን 2ለ1 በመርታት ሲሆን በወንዶቹ ደግሞ ደቡብ ኢትዮጵያን 2ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነው።

ይሄ የትጋት ውጤት የሆነው ታሪካዊ ድል በመምጣቱ በየዘርፉ የለፋቹ ባለድርሻ አካላት እንኳን ደስ አላችሁ። ተባብረን ከሰራን ክልላችን በእግር ኳስ ምን ያህል ታዳጊዎቹ ላይ እየሰራ እንደሆነ ማሳያ በመሆኑም የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተሰማውን ጥልቅ ደስታ ይገልፃል።

ፌዴሬሽናችን አዲስ ሀላፊነት ዛሬ ይረከባልየ2018 ዓም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በዛሬው እለት ጅማሮውን የሚያደርግ ሲሆን የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአንዱ ምድብ አስተናጋጅ እንዲሆን ...
01/11/2025

ፌዴሬሽናችን አዲስ ሀላፊነት ዛሬ ይረከባል

የ2018 ዓም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በዛሬው እለት ጅማሮውን የሚያደርግ ሲሆን የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን የአንዱ ምድብ አስተናጋጅ እንዲሆን ተመርጧል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ውስጥ አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር በሁለት ምድቦች ተከፍሎ በሀዋሳ እና በጅማ ዛሬ ከሰዓት በይፋ የሚጀምር ሲሆን ፌዴሬሽናችን እንደተለመደው ሀላፊነት ተቀብሎ የሚያስተናግድ ይሆናል።

ስለሆነም መላው የክልላችን ስፖርት ወዳዱ ማህበረሰብ ጨዋታዎችን እንዲታደም የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥሪ ያቀርባል።

ውድድሩ ዛሬ ከሰዓት በሚደረግ አንድ መከፈቻ ጨዋታ የሚጀምር ሲሆን ቀን 9:30 ቡራዩ ክ/ከተማ ከ የካ ክ/ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

Address

Hawassa Sidama Prosperity Party Street
Awassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Football Federation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Sidama Football Federation:

Share