29/03/2026
የኤሌክትሪክ ሃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎችን ስለማሳወቅ
# # # # #
በኮሪደር ልማት ስራ ምክንያት የሚነሱ የኤሌክትሪክ መስመር ምሰሶ ማዘዋወሪያ ስራ ለመስራት መጋቢት 21/2018 ዓ.ም ከ ጠዋቱ 2:00 እስከ 11:30 ሰዓት ድረስ ቀበሌ 13 ማለትም ካቶሊክ፤ ሳሚ ቁርጥ ቤት አካባቢ፤ባታ ፤ ሀይሌ ት/ቤት እና አምሳሉ ሜዳ አካባቢ፤ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፤ ኦክስጅን ማምረቻ፤ የፊስቱላ ታሚሚዎች ህክምና መስጫ እና በተጠቀሱት አካባቢዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦ የሚዉል መሆኑን በአክብሮት እያሳወቅን ክቡራን ደንበኞቻችን የታቀደው ስራ ተጠናቆ የኤሌክትሪክ ኃይል እስከሚገናኝ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ እየጠየቅን በምርት እና በጥሬ እቃዎች ላይ ብክነት እንዳይከሰት ከወዲሁ ጥንቃቄ እንድታደርጉ ወይም ሌላ የአማራጭ ሀይል እንድትጠቀሙ በአክብሮት እናሳውቃለን።
የባህር ዳር ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት