Ethiopia Electric utility Bahir Dar Region

Ethiopia Electric utility Bahir Dar Region Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopia Electric utility Bahir Dar Region, Government Organization, Bahir Dar.

በኢትዮጵያ እና ኬንያ መካከል አንድ ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በ24 ብር ከ07 ሳንቲም ማቅረብ የሚያስችል የኃይል አቅርቦት ስምምነት ተፈረመየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኬንያው የኤሌክትሪ...
10/07/2026

በኢትዮጵያ እና ኬንያ መካከል አንድ ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በ24 ብር ከ07 ሳንቲም ማቅረብ የሚያስችል የኃይል አቅርቦት ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኬንያው የኤሌክትሪክ ኃይል ኩባንያ (Kenya Power and Lighting Company - KPLC) ጋር አንድ ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በ24 ብር ከ07 ሳንቲም ለማቅረብ የሚያስችለው አዲስ ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኤሌክትሪክ ንግድ ለማጠናከር፣ በድንበር አካባቢዎች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት እና የምስራቅ አፍሪካን የኢነርጂ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው።

የኃይል አቅርቦት ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው እና የኬንያው አቻቸው ዶ/ር ኢ/ር ጆሴፍ ሲሮር ጋር በጋራ ሆነው ፈርመዋል።

በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር ጌቱ እንደገለጹት፤ የምስራቅ አፍሪካ ጎረቤት ሀገራት በአንድነትና በትብብር ሲሠሩ ትልቅና ስኬታማ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚችሉ ይህ ስምምነት ማሳያ ነው።

ስምምነቱ የጋራ ህልም የሆነችውን ይበልጥ የተገናኘች ምስራቅ አፍሪካን (Connected East Africa) እውን ለማድረግ የሚረዳ መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ጌቱ፣ ኢነርጂ የሀብት ምንጭ ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ሕዝብ ወደ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያደርስ ድልድይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የኬንያው KPLC ማኔጂንግ ዳይሬክተርና ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኢ/ር ጆሴፍ ሲሮር በበኩላቸው፣ ስምምነቱ ከኃይል አቅርቦት ትስስር ባሻገር በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ሰላምና የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።

በተለይም በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር አካባቢ የሚገኙ ማህበረሰቦች ከዚህ ስምምነት ቀጥተኛ ተጠቃሚ መሆናቸው በሁለቱ ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረው አክለው ገልጸዋል።

ይህ ስምምነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኃይል ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከማሻሻል ባለፈ፣ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተቀናጀ የኃይል አቅርቦት ስርዓት (Regional Power Pool) ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት ትልቅ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን በማሳደግ የቀጣናውን የኢኮኖሚ እድገት ለማበረታታት እና ለሕዝቦች የተሻለና ጥራት ያለው አገልግሎት ለማቅረብ እንደሚያስችል ይጠበቃል።

በስምምነቱ መሰረት የኬንያው የኤሌክትሪክ ኃይል ኩባንያ በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት ለኢነርጂ 24 ብር 07 ሳንቲም እንዲሁም ለዲማንድ ቻርጅ 1 ሺህ 10 ብር ከ89 ሳንቲም የሚከፍል ይሆናል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ  በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካ ክፍለ ከተማ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት አካባቢ የኤሌክትሪክ መሰ...
01/07/2026

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካ ክፍለ ከተማ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት አካባቢ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡

የየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ህግ ቢሮ ጋር በመተባበር ባደረጉት ኦፕሬሽን ከ3.8 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ኬብሎች፣ አልሙኒየሞችና መዳቦች በመስረቅ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት አካባቢ አከማችተው የተገኙ ግለሰቦች ባሳለፍነው መጋቢት ወር መጨረሻ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወሳል፡፡

በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ ችሎት 2ኛ ወንጀል ችሎት ምስክሮችን በማዳመጥ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመ ግለሰብን በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

በተያያዘም በየካ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ኬብሮን መድኃኒት ቤት አካባቢ በግንባታ ላይ ከሚገኝ ህንፃ ላይ የወደቀ ህንፃ መወጣጫ ዊንች በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብልና በትራንስፎርመር ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡፡

ከህንፃው 12ኛ ፎቅ ላይ የወደቀው ህንፃ መወጣጫ ዊንች በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ኬብል ላይ በማረፉ ከኬብሉ ጋር የተያያዘው ትራንስፎርመር የተሸከመ ኮንክሪት ፖል ከነትራንስፎርመሩ ከጥቅም ውጪ ሆኗል፡፡

ተቋሙ ጉዳት የደረሰበትን የኤሌክትሪክ ኬብልና ትራንስፎርመር በመተካት ወደ አገልግሎት ለመመለስ ከ1 ሚሊየን 9 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ አድርጓል፡፡

ተቋሙ ለደረሰበት ጉዳት ካሳ ክፍያ እንዲፈፀም የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ህግ ክፍል ለየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መመሪያ ክስ መስርቷል፡፡

በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ 2ኛ ፍ/ብሔር ችሎት በቀረበለት የፍ/ብሔር የክስ መዝገቡን ሲመለከት ቆይቶ ማስረጃዎችን ከመረመረ በኋላ ውሳኔ ሰቷል። በዚህም ጉዳት ያደረሰው ድርጅት ለተቋሙ 1 ሚሊየን 959 ሺህ 783 ብር የጉዳት ካሳ ክፍያ እንዲፈፅም ተወስኖበታል፡፡

በአሁኑ ሰዓት ተከሳሽ 250 ሺህ ብር ክፍያ የፈፀመ ሲሆን ቀሪውን ክፍያ ለመፈፀም በቀጠሮ ላይ ይገኛል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞቻችን ፣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለሀገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት ጀርባ አጥንት የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ በአስተማማ...
29/06/2026

ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞቻችን ፣

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለሀገራችን ሁለንተናዊ ዕድገት ጀርባ አጥንት የሆነውን የኤሌክትሪክ ኃይል በመላ ሀገሪቱ በአስተማማኝ፣ ተደራሽና ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማቅረብ ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል። ይሁን እንጂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለዕለት ተዕለት ሕይወታችን መሠረታዊ ፍላጎት ቢሆንም፣ በአጠቃቀም ወቅት በሚፈጠሩ ጥንቃቄ የጎደላቸው ስህተቶችና የደህንነት መመሪያዎችን ባለመከተል ምክንያት ቀላል የማይባሉ የንብረትና የሕይወት ጉዳቶች ሊከሰቱ ይችላሉ።

​ስለዚህ በቤትዎም ሆነ በሥራ ቦታዎ የኤሌክትሪክ ደህንነትን ማረጋገጥ ምርጫ ሳይሆን የሁላችንም የማይታለፍ ግዴታ ነው ብለን እናምናለን።

​እንደ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰጪ ተቋም፣ በምናከናውናቸው የኃይል ማከፋፈልና ጥገና ሥራዎች ሁሉ የሠራተኞቻችንን ብቻ ሳይሆን የክቡራን ደንበኞቻችንን እና የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ ዋነኛ ኃላፊነታችን ነው።

ከዚህም በላይ ደንበኞቻችን በየቤታቸውና በየድርጅቶቻቸው ከኤሌክትሪክ አደጋ ራሳቸውን እንዲጠብቁ የማስተማርና የማስገንዘብ ሥራዎችን በልዩ ትኩረት እየሠራን እንገኛለን።

“ቅድሚያ ለደህንነት” የሚለው መርህ በተቋማችን ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ደንበኛችን ቤትና የሥራ ቦታ የእለት ተእለት ባህል መሆን አለበት።

​ይህንን ግንዛቤ ለማሳደግ ተቋማችን በየሦስት ወሩ የ“የሥራ ላይ ደህንነት ንቅናቄ ሳምንት” በማካሄድ፣ የአገልግሎት አሰጣጣችንን ከአደጋ የፀዳ እንዲሆንና የደንበኞቻችንን ደህንነት በላቀ ሁኔታ ለመጠበቅ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል። የዚህ ንቅናቄ ዋና ዓላማ እኛም ሆንን እናንተ ደንበኞቻችን ከትላንቱ በተሻለ ዛሬ ለኤሌክትሪክ ደህንነት ከፍተኛ ትኩረት እንድንሰጥ ነው።

​ይህንን ከአደጋ የፀዳ አካባቢ የመፍጠር የጋራ ግብ ለማሳካት፣ እናንተም ክቡራን ደንበኞቻችን በሚከተሉት ነጥቦች ላይ አጋር እንድትሆኑን እንጠይቃለን፦

• በየቤታችሁና በየድርጅቶቻችሁ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መስመሮችንና ዕቃዎችን በጥንቃቄ መያዝና አደጋ እንዳያደርሱ መከታተል፣

• ​በአካባቢያችሁ የወደቁ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ወይም አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ሁኔታዎችን ሲመለከቱ በፍጥነት ለተቋማችን ማሳወቅ፣

• ​የሚተላለፉ የኤሌክትሪክ ደህንነት የጥንቃቄ መልዕክቶችንና መመሪያዎችን በተግባር ላይ ማዋል፣

• ​ሕገ-ወጥ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታዎችንና ግንኙነቶችን በመከላከል ራስዎንና ቤተሰብዎን መጠበቅ።

​ቅድሚያ ለደህንነት መስጠት ዛሬን በሰላምና በሕይወት እንድንኖር፣ ነገም በሥራችን ውጤታማ እንድንሆን የሚያስችለን መሠረታዊ ነገር ነው። ማንኛውንም የኤሌክትሪክ መሣሪያ ከመጠቀምዎ በፊት ለደህንነትዎ ቅድሚያ መስጠት የዘወትር ልማድዎ እንዲሆን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

​በመጨረሻም፣ ከአደጋ የፀዳ የኤሌክትሪክ አጠቃቀምን ማረጋገጥ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት በመሆኑ፣ ከጎናችን ሆናችሁ አብራችሁን እንድትሠሩ በአክብሮት እጠይቃለሁ።
​አመሰግናለሁ!

​ኢንጂነር ጌቱ ገረመው
ዋና ሥራ አስፈፃሚ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

​ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
#ለደንበኞቻችንደህንነት
#ቅድሚያለደህንነት

የ3 ቢሊዮን ብር የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈረመየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አልፋ (Alpha TND & LTD ) እና ካፒታል( Capital electech ) ከተሰኙ ኢንጂነሪን...
26/06/2026

የ3 ቢሊዮን ብር የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አልፋ (Alpha TND & LTD ) እና ካፒታል( Capital electech ) ከተሰኙ ኢንጂነሪንግ እና ዕቃ አቅራቢ ተቋማት ጋር የ3 ቢሊየን ብር የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) እንዳሉት ፕሮጀክቱ በከተሞቹ ያለውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት አስተማማኝ በማድረግ ደንበኞች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያግዝ ፕሮጀክት መሆኑን አመላክተው ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብና የጥራት ደረጃ መጠናቀቅ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በአምቦ፣ ነቀምት እና አሶሳ ከተሞች የሚከናወን ሲሆን፣ በእነዚህ ከተሞች የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን በማዘመንና በማጠናከር የአገልግሎቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ ያለመ ነው።

የመልሶ ግንባታና የማሻሻያ ፕሮጀክቱ 325 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ ቮልቴጅ የኤሌክትሪክ መስመር የማሻሻያ ሥራዎች የሚከናወኑ ሲሆን፣ ይህም የኔትወርኩን አቅም ከማሳደግ ባለፈ የኃይል መቆራረጥ እና የቴክኒክ ችግሮችን ለመቀነስ እንደሚረዳ ተጠቁሟል ።

በተጨማሪም 235 ትራንስፎርመሮች ላይ የማሻሻያና የመልሶ ግንባታ ሥራ የሚከናወን ሲሆን፣ ከእነዚህ 70 በአምቦ፣ 121 በነቀምት እና 44 በአሶሳ እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡

ዋና መቀመጫቸውን በጋና እና ሕንድ ያደረጉት የእነዚህ ተቋማት ተወካዮች በኤሌክትሪክ መሣሪያዎች አቅርቦት፣ በዲስትሪቢዩሽን ኔትወርክ ግንባታና ማሻሻያ፣ እንዲሁም በኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ዘርፍ ለተቋሙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ገልፀዋል።

በቀጣይም በመሰል ፕሮጀክቶች የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትን በማዘመን፣ የአገልግሎት ጥራትን በማሻሻል እና የደንበኞችን ተጠቃሚነት በማሳደግ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለማቅረብ የጀመረውን ሥራ እንደሚያጠናክር ተገልጿል።

ፕሮጀክቱ ከወርልድ ባንክ በተገኘ 1.2 ቢሊዮን ብር እና 12 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ የሚተገበር ሲሆን፣ በአጠቃላይ በ3 ቢሊዮን ብር የሚከናወን ፕሮጀክት መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን በሁለት ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅም ተገልጿል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ⚡️

103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዘጠኝ ወራት 103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክ...
05/05/2026

103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ዘጠኝ ወራት 103 አዲስ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረጉን የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ገለፁ፡፡

አገልግሎቱ ፍትሃዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ባከናወነው ዘርፈ-ብዙ ስራ ከዋናው ግሪድና ከግሪድ የራቁ በርካታ አዳዲስ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን ያነሱት ዋና ስራ አስፈፃሚው፤ ከጤናና ማህበራዊ ተቋማት በተጨማሪ ከ31 ሺህ በላይ አባዎራዎችና እማዎራዎችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርገዋል ብለዋል፡፡

በዚህም በዘጠኙ ወራት ተጠቃሚ ከሆኑት ውስጥ 82ቱ ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ (ግሪድ) እንዲሁም 21 የገጠር ከተሞችና መንደሮችን ደግሞ በፀሃይ ኃይል አማራጭ (ኦፍግሪድ) የተገናኙ መሆናቸውን ዋና ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ተደራሽነትን ከማረጋገጥ አኳያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 423 ሺህ 200 አዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡ አፈፃፀሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ18 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን ነው ያነሱት፡፡

እንደ ዋና ስራ አስፈፃሚው ገለፃ ኃይል ከተገናኘላቸው አዳዲስ ደንበኞች ውስጥ 31 ሺህ 298 ያህሉ አዲስ የኤሌክትሪክ ተደራሽ በሆኑት የገጠር ከተሞችና መንደሮች ተጠቃሚ የሆኑ ናቸው፡፡

ኢንጅንር ጌቱ አክለውም አዲስ ኤሌክትሪክ ካገኙ ደንበኞች መካከል 74 ነጥብ 2 ከመቶ የድህረ ክፍያ እንዲሁም 25 ነጥብ 8 በመቶ የቅድመ ክፍያ ቆጣሪ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

ያለፉት ዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ጨምሮ በአሁን ወቅት አጠቃላይ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ደንበኞች (እማዎራዎች/አባዎራዎች) ቁጥር 5.64 ሚሊዮን መድረሱንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ክፍያን በአንድ ጊዜ መክፈል ለማይችሉ ደንበኞች የእፎይታ ጊዜ የሚሰጥ አዲስ የአሰራር ሥረዓት ይፋ ተደረገ   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ...
29/04/2026

የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ክፍያን በአንድ ጊዜ መክፈል ለማይችሉ ደንበኞች የእፎይታ ጊዜ የሚሰጥ አዲስ የአሰራር ሥረዓት ይፋ ተደረገ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ክፍያን በአንድ ጊዜ መክፈል ለማይችሉ ደንበኞች የእፎይታ ጊዜ የሚሰጥ አዲስ የአሰራር ስርዓት መዘርጋቱን አስታወቀ።

ተቋሙ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የአሰራር ሥረዓቱ በገንዘብ እጥረት ምክንያት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት ያልቻሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጿል።

የተቋሙ የማርኬቲንግ፣ ሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ደንድር በመግለጫው ላይ እንደተናገሩት፣ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን ለማድረግ እና ደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ ዘመናዊ አሰራሮችን እየተገበረ ይገኛል።

አዲሱ የጊዜ ገደብ ክፍያ ስርዓትም ደንበኞች የማስቀጠያ ክፍያውን እስከ 2 ዓመት በሚደርስ ጊዜ ውስጥ ከወርሃዊ የፍጆታ ክፍያቸው ጋር እንዲከፍሉ የሚያስችል ነው" ብለዋል።

ይህ አሰራር ተግባራዊ የሚሆነው ለነጠላ ፌዝ (Single Phase) ቆጣሪ አመልካቾች ብቻ ሲሆን፣ደንበኞች ምንም አይነት የማረጋገጫ ሰነድ ማቅረብ ሳይጠበቅባቸው ማመልከቻ በመሙላትና 10 በመቶ ቅድመ ክፍያ በመፈፀም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ።

እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ፤ክፍያውን በ6 ወራት ውስጥ ለሚያጠናቅቁ ደንበኞች ምንም አይነት ወለድ የማይታሰብ ሲሆን፣ ከ6 ወር በላይ ለሚጠቀሙ ግን እንደየጊዜው ርዝማኔ ከ3 እስከ 9 በመቶ የወለድ ምጣኔ ይኖረዋል።

የአሰራር ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ደንበኞች በየወሩ የሚከፍሉት መጠን ከፍጆታ ክፍያቸው ጋር ተደምሮ እንዲቀርብ የሚደረግ መሆኑም ታውቋል።

የአዲስ ኃይል ማስቀጠያ ክፍያውን በአንድ ጊዜ የመክፈል አቅም ያላቸው በአንድ ጊዜ ክፍያ በነባሩ ውል የሚስተናገዱ ሲሆን ሙሉ ክፍያውን በአንድ ጊዜ መክፈል የማይችሉ ደንበኞች ደግሞ በደንበኞቹ ፍላጎት ላይ መሰረት በማድረግ ከፍተኛውን እስከ 24 ወራት ጊዜ (2 ዓመት) በሚቆይ የአከፋፈል ስርዓት ተከፋፍሎ በየወሩ ከወርሃዊ የኢነርጂ ፍጆታ ክፍያቸው ጋር እየተደመረ እንዲከፍሉ ይደረጋል ብለዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የኤሌክትሪክ ሃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎችን ስለማሳወቅ # # # # # በኮሪደር ልማት ስራ ምክንያት የሚነሱ የኤሌክትሪክ መስመር ምሰሶ ማዘዋወሪያ ስራ ለመስራት መጋቢት 21/2018 ዓ.ም ...
29/03/2026

የኤሌክትሪክ ሃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎችን ስለማሳወቅ
# # # # #
በኮሪደር ልማት ስራ ምክንያት የሚነሱ የኤሌክትሪክ መስመር ምሰሶ ማዘዋወሪያ ስራ ለመስራት መጋቢት 21/2018 ዓ.ም ከ ጠዋቱ 2:00 እስከ 11:30 ሰዓት ድረስ ቀበሌ 13 ማለትም ካቶሊክ፤ ሳሚ ቁርጥ ቤት አካባቢ፤ባታ ፤ ሀይሌ ት/ቤት እና አምሳሉ ሜዳ አካባቢ፤ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፤ ኦክስጅን ማምረቻ፤ የፊስቱላ ታሚሚዎች ህክምና መስጫ እና በተጠቀሱት አካባቢዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦ የሚዉል መሆኑን በአክብሮት እያሳወቅን ክቡራን ደንበኞቻችን የታቀደው ስራ ተጠናቆ የኤሌክትሪክ ኃይል እስከሚገናኝ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ እየጠየቅን በምርት እና በጥሬ እቃዎች ላይ ብክነት እንዳይከሰት ከወዲሁ ጥንቃቄ እንድታደርጉ ወይም ሌላ የአማራጭ ሀይል እንድትጠቀሙ በአክብሮት እናሳውቃለን።
የባህር ዳር ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የአሜሪካ የንግድና ልማት ኤጀንሲ (USTDA) በኃይል ዘርፍ ዘመናዊነት ላይ ውይይት አካሄዱየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢ/ር ጌቱ...
27/03/2026

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና የአሜሪካ የንግድና ልማት ኤጀንሲ (USTDA) በኃይል ዘርፍ ዘመናዊነት ላይ ውይይት አካሄዱ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢ/ር ጌቱ ገረመው ከአሜሪካ ንግድና ልማት ኤጀንሲ (USTDA) የልዑካን ቡድን ጋር በቢሮአቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚው በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ተቋሙ የኃይል ማከፋፈያ ስርዓቱን ለማጠናከርና የኤሌክትሪክ መረቡን (Grid) ዘመናዊ ለማድረግ በሚያስችሉ ዕድሎች ላይ ከኤጀንሲው ጋር ፍሬያማ ምክክር አድርገዋል።

በውይይቱም የኃይል ማከፋፈያ ስርዓታችንን ማጠናከር በሚቻልባቸው እድሎች፣ የኤሌክትሪክ መረብን (grid) ዘመናዊ ማድረግ፣ እንዲሁም እንደ ስማርት ሜትር (smart metering)፣ የኃይል ማከማቻ (energy storage) እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ባሉ የፈጠራ መፍትሄዎች ዙሪያ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል፡፡

ኢ/ር ጌቱ አክለውም፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና ለሀገሪቱ ዘላቂ የኃይል አቅርቦት ለመገንባት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም ከኤጀንሲው ጋር የሚመሰረተው ጠንካራ አጋርነት በውይይቱ የተነሱትን ሃሳቦች ወደ ተጨባጭና ተፅዕኖ ፈጣሪ ፕሮጀክቶች እንደሚቀይራቸው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የትራንስፎርመር ደህንነትን ለመጠበቅ የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ላይ የስምምነት ፊርማ ስነ ስርዓት ተካሄደ$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አገልግሎቱን ይበ...
05/03/2026

የትራንስፎርመር ደህንነትን ለመጠበቅ የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ላይ የስምምነት ፊርማ ስነ ስርዓት ተካሄደ
$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አገልግሎቱን ይበልጥ ዘመናዊ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ለማድረግ ከጀርመን ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ተፈራርሟል።

ስምምነቱ የተፈረመው ከአለም አቀፍ የጀርመን ተራዶ ድርጅት Deutsche Gesellschaft für Internationale Zusammenarbeit (GIZ) እና ካርልስሩሄ የቴክኖሎጂ ተቋም Karlsruhe Institute of Technology (KIT) ጋር ነው፡፡

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው እየጨመረ የመጣውን የሃይል ፍላጎት መሸከም የሚችል የኤሌክትርክ መሰረተ ልማትን ለማዘመን አዳዲስ አሰራሮች በመተግበር ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ከአጋር አካላት ጋር መሥራት የዲስትሪቡሽን ኔትዎርክን ለማጠናከር እንዲሁም ትራንስፎርመሮችን ጨምሮ ተቋሙ ያሉትን ንብረቶች ለመከታተል እና ለመቆጣጠር በተጨማሪም ኪሳራን ለመቀነስ እንደሚረዳ ጠቁመዋል፡፡

አለም አቀፍ የጀርመን ተራዶ ድርጅት (GIZ) እና ካርልስሩሄ የቴክኖሎጂ ተቋም (KIT) ተወካይ በበኩላቸው ተቋሙ ጋር ለመስራት ዕድሉን በማግኘታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው፤ የኃይል ስርጭቱን ወደ ዘመናዊ የዲጂታል አስተዳደር ለማሻሻል የሚያስችል አስፈላጊ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።

ቴክኖሎጂው ወቅቱን የጠበቀ የዲስትርቡሽን ትራንስፎርመር ደህንነት መረጃ በርቀት በመሰብሰብ ችግር ከመከሰቱ በፊት ለመለየት የሚያስችል ነው፡፡

በፕሮጀክት ሥራው በመጀመሪያ ደረጃ በአዲስ አበባ በሚገኙ ትራንስፎርመሮች ላይ በሙከራ ደረጃ የሚተገበር ሲሆን፣የቴክኖሎጂው አዋጭነት እና ውጤታማነት ከተረጋገጠ በኋላ በሌሎች ከተሞችና ክልሎች የሚተገበር ይሆናል፡፡

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የኃይል አቅርቦትን አስተማማኝነት በማጠናከር የደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ፣ የትራንስፎርመር ጉዳትን ለመቀነስ እና የሀገራችንን የኃይል ዘርፍ ወደ ዲጂታል ዘመን ለመውሰድ ትልቅ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ይህንን   ሰምተዋል? ወርሃዊ ንባቤን አልተነበበልኝም፤ ቆጣሪ አንባቢ ቀረብኝ የሚል ቅሬታን የሚያስቀር ቴክኖሎጂ መተግበር ጀመረ👇   የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የድህረ ክፍያ ደንበኞቹን...
21/02/2026

ይህንን ሰምተዋል? ወርሃዊ ንባቤን አልተነበበልኝም፤ ቆጣሪ አንባቢ ቀረብኝ የሚል ቅሬታን የሚያስቀር ቴክኖሎጂ መተግበር ጀመረ👇

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የድህረ ክፍያ ደንበኞቹን የእጅ ስልካቸውን ተጠቅመው ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ ንባባቸውን ከቤታቸው ሆነው የሚያስገቡበት የቴሌግራም ቻት ቦት () የመኩራ ትግበራ በተመረጠ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል ይፋ አደረገ፡፡

የሙከራ ትግበራው (Pilot test) በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን መተግበር ጀምሯል፡፡

ማዕከሉ ከ16 ሺህ በላይ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞች ያሉት ሲሆን፤ እነዚህ ደንበኞች በያዝነው ወር ከየካቲት 13 እስከ 23 ድረስ የፍጆታ ንባብን በቀላሉ ቤታቸው ሆነው በeeuchatbot ቴሌግራም ተጠቅመው ለተቋማችን እንዲልኩ ጥሪ ቀርቧል፡፡

👉 ቁጥር 4 አገልግሎት መስጫ ማዕከል የሚገኘው
➡️ጳውሎስ ሆስፒታል ፊት ለፊት

👉 ማዕከሉ የሚያካልላቸው አካባቢዎች፡-

1️⃣ ከእንቁላል ፋብሪካ አደባባይ በሩፋኤል ቤተክርስቲያን አድርጎ፣ በጉለሌ ወረዳ 9፣ በእምቢልታ ሆቴል፣ በሚሊኒየም ሰፈር፣ በሸጎሌ አካባቢ፤

2️⃣ ከሚሊኒየም ሰፈር፣ በዊንጌት፣ በጴጥሮስ ቤተ-ክርስቲያን፣ በኮልፌ አጠና ተራ፣ በፓሪስ ካፌ፣ በ18 መብራት ኃይል ፊት ለፊት፣ በሻንቅላ ወንዝ በአማኑኤል ቤተ-ክርስቲያን መሻገሪያ ድልድይ፣

3️⃣ በመሳለሚያ ወደ 18 አደባባይ፣ በደጉ ሆቴል ወደ ሰፈረ ሰላም ድልድይ፣ በታይዋን፣ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፣ በአበበ ቢቂላ፣ በአዲሱ ሚካኤል አካባቢ፣ በጨው በረንዳ፣ በእስላም መቃብር፣ በእንቁላል ፋብሪካ እና በጳውሎስ አካባቢ፣

👉 () ወርሃዊ የፍጆታ ንባብ በቀላሉ መላክ የሚያስገኘው ጠቀሜታ

➡️ የፍጆታ ሂሳብን በወቅቱ ለመፈፀም
➡️ ወርሃዊ ንባቤን አልተነበበልኝም የሚልን ቅሬታ ለማስቀረት፤
➡️ ቆጣሪ አንባቢ ቀረብኝ የሚል ቅሬታን ለማስቀረት፣
➡️ ጊዜና ወጪን ለመቆጠብ

👉 ቀጣይ ትግበራ

የሙከራ ትግበራው (Pilot test) የሚያመጣቸውን ዕድሎችንና ተግዳሮቶችን በመለየት በቀጣይ በሌሎች ሪጅኖችና አገልግሎት መስጫ ማዕከላት የሚተገበር ይሆናል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia Electric utility Bahir Dar Region posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share