Bahir Dar City Adminstration Zonal Health Department

Bahir Dar City Adminstration Zonal Health Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bahir Dar City Adminstration Zonal Health Department, Government Organization, Amhara Regione, Bahir Dar.

የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር በ901 ማህበራት የተደራጁ 19ሺ 698 ነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ የብሎክ እጣ መርሀ ግብር ተካሄደ ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም (ባሕርዳር ከተማ ኮሙ...
13/08/2026

የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር በ901 ማህበራት የተደራጁ 19ሺ 698 ነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ የብሎክ እጣ መርሀ ግብር ተካሄደ

ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም (ባሕርዳር ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ) የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር የመንግስት ሰራተኞችን የመኖሪያ ቤት እጦት ችግር በመፍታት ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ከመሬት ዝግጅት ጀምሮ ፣የማደራጀት ፣እውቅና የመስጠትና የካሳ ግምት ክፍያ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።

በመሆኑም ከዚህ በፊት የቤት ማሕበር እውቅና ያገኙ እና የካሳ ክፍያ ያጠናቀቁ የ789 እና 119 ህብረት ስራ ማሕበራት የክልል ፣የከተማ እና ክፍለ ከተማ አመራሮች ፣የማህበራት አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ተካሄዷል።

የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው የራዕያችን መዳረሻ የባሕርዳርን ተጨማሪ ውበት ፣ልማትና ተመራጭነት ማጉላት ብቻ ሳይሆን በዘላቂ እድገት በተቃኘ ማስተር ፕላን ታግዞ ጥራትና ተደራሽነቱ የተረጋገጠ መሰረተ ልማት እና የነዋሪዎችን ፍላጎት ያማከለ የመኖሪያ ቤት ማሟላት ነው ብለዋል።

ለዚህም መላ አመራሩ ለመኖሪያ ቤት እጦት አንገብጋቢ ችግር ትኩረት በመስጠት በመንግስትና በግል ድርጅቶች ተቀጥረው ለህዝብና መንግስት አገልግሎት የሚሰጡ ከ26ሺ በላይ ነዋሪዎችን በመመዝገባና በማጣራት በመጀመሪያው ዙር የተለዩ 19ሺ 696 ሰዎችን ተጠቃሚ ያደረገ የብሎክ እጣ እንዲያወጡ መደረጉን ገልፀዋል።

በዚህም ተነሽ አርሶ አደሮች ማግኘት ያለባቸውን መብትና ጥቅም በማስጠበቅ ተገቢ ካሳ እና ትክ በመስጠት በኩልም በውጤታማነት የተከናወነ ቁልፍ ተግባር እንደነበር ተናግረዋል።

ባሕርዳር በለውጥ ጎዳና ላይ ናት ስንል በሚከናወኑ የመሰረተ ልማት ትሩፋቶቿ ብቻ ሳይሆን በመኖሪያ ቤት አቅርቦትና መሰል ሰው ተኮር ስራዎች ዙሪያ በሚመዘገቡ ውጤቶች ጭምር ነው ብለዋል።

በቀጣይም በማጣራት ሂደት ላሉ ፣በባሕርዳር ዙሪያ ለተደራጁ እና ሌሎች ነዋሪዎች ተደራሽ ለማድረግ ሰፋ ያለ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን በመግለፅ ባልተገባ መንገድ ቦታ ለመውሰድ የሚሞክሩ አካላትን የመከላከል ጉዳይ በትኩረት የተያዘ መሆኑን ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኀላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 1ሺ 045 ሄክታር መሬት በማዘጋጀት በመጀመሪያ ዙር ብቻ ከ19ሺ 696 በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ በማድረጉ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።

የመኖሪያ ቤት ልማት ጉዳይ ለግለሰብ ብቻ ሳይሆን ለሀገር ልማትና ብልፅግና እንዲሁም የተረጋጋና ኢኮኖሚያዊ ምህዳሩ የሰፋ አካባቢ ለመፍጠር ድርሻው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል።

ለከተሞች መስፋፋትና መዘመን የቤት ልማት ፕሮግራን ጥራትና ተደራሽነት ማረጋገጥ ዋነኛው ጉዳይ እንደሆነ ገልፀው ለዚህ ተግባር ውጤታማነት ደግሞ የሁሉንም አካል የጋራ ጥረት የሚጠይቅ እንደሆነ አሳስበዋል።

የባሕርዳር ከተማ አስተዳድር መሬት መምሪያ ኀላፊ ወ/ሮ መልካም ስራ ካሳው በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ ለመኖሪያ ቤት እጦት ችግር መፈታት በሰጠው ልዩ ትኩረት በ4 ሳይቶች 1ሺ 045 ሄክታር መሬት አዘጋጅቶ ለዚህ አድርሷል ብለዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የባሕርዳር ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ገጽ ይወዳጁ:-
Facebook
https://www.facebook.com/BahirdarcityGovenmentalCommunicationAffairsoffice
YouTube
https://www.youtube.com/channel/UCNoAcvzPiExah4lyaAb6_BQ
Telegram
https://t.me/Bahirdarcitycommunication
Twitter
https://x.com/BahirdarO8493?s=35
Tiktok
https://www.tiktok.com/

12/08/2026
07/08/2026
07/08/2026
የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለዛሬ ንቃት፣ለነገ ጤናማና ደስተኛ ህይወት" በሚል መሪ ቃል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በባህርዳር ከተማ ተካሄደ።የአብክመ ጤና ቢሮ ከባህርዳር ከተማ  ባህል ቱሪዝም ስ...
07/08/2026

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለዛሬ ንቃት፣ለነገ ጤናማና ደስተኛ ህይወት" በሚል መሪ ቃል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በባህርዳር ከተማ ተካሄደ።

የአብክመ ጤና ቢሮ ከባህርዳር ከተማ ባህል ቱሪዝም ስፖርት መምሪያ እና ከባህርዳር ከተማ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አካሂዷል።

ጤናማና ንቁ ማህበረሰብ ለመፍጠር ታሳቢ ተደርጎ በተካሄደው በዚህ ስፖርታዊ ዝግጅት ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ጌትነት አባት በንግግራቸው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ የአካልና የአእምሮ ንቃትን ለመጨመር ፣ የስራ ተነሳሽነትን ለመጨመርና ንቁ ለመሆን እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

ኃላፊው በመልክታቸው በአሁኑ ወቅት በከተማችን እጨመረ የመጣውን በ ከፍተኛ ሁኔታ ለሰው ልጆች ሞትና እክል ጉዳት እየዳረጉ ያሉትን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እንደ ደም ግፊት፣ ስኳር፣ ስቴሮክ እና ሌሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሳምንት ከ30 ደቂቃ ያለነሰ በሳምን ከ3 እስከ 5 ቀናት የዕለት ከዕለት የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በአካል ብቃት እንቅስቃሴው ላይ የክልልና የከተማ አመራሮች፣ የስፖርት ባለሙያዎች እና የስፖርቱ ቤተሰቦች ተሳታፊ ሆነዋል።

በአንድ ጊዜ 5ሺህ ከረጢት ደም ማከማቸት የሚችል የደም ማቀዝቀዣ ማዕከል ተመረቀ፤በባሕር ዳር ደም እና ኅብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት በአንድ ጊዜ 5ሺህ ከረጢት ደም ማከማቸት የሚችል የደም ማ...
07/08/2026

በአንድ ጊዜ 5ሺህ ከረጢት ደም ማከማቸት የሚችል የደም ማቀዝቀዣ ማዕከል ተመረቀ፤

በባሕር ዳር ደም እና ኅብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት በአንድ ጊዜ 5ሺህ ከረጢት ደም ማከማቸት የሚችል የደም ማቀዝቀዣ ማዕከል ተመርቋል።

የማቀዝቀዣ ማዕከሉን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ አብዱልከሪም መንግሥቱ መርቀው ሥራ አስጀምረውታል።

በምረቃ መርሐ ግብሩ መልዕክት ያስተላለፉት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ የደም ባንክ አገልግሎትን የተሻለ ለማድረግ ዘላቂ የኾነ የግብዓት አቅርቦት ላይ መሥራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

የደም እና የኅብረ ሕዋስ አገልግሎት በሰፊው ወደ ሕዝብ ለማድረስ በዲጂታላይዜሽን የዘመነ አገልግሎት መስጠት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ስለመኾኑም ጠቁመዋል።

ይህንን አገልግሎት የሚያሳልጥ የማቀዝቀዣ፣ አገልግሎቶችን የማስተካከል እና የማዘመን ሥራዎችን በየደረጃው ከሚገኙ አጋር እና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሥራት ይገባል ነው ያሉት።

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኀላፊ አብዱልከሪም መንግሥቱ እንደተናገሩት የባሕር ዳር ደም እና የኅብረ ሕዋስ አገልግሎት ባለፉት ዓመታት የተሻለ አፈጻጸም ሲያስመዘግብ የቆየ ነው።

አሁንም ዘመናዊ አሠራሮችን በመከተል ዲጂታላይዜሽንን እውን ማድረግ ችሏል ነው ያሉት። ለዚህም የተቋሙ መሪዎች እና ባለሙያዎች ያላቸው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

የባሕር ዳር ደም ባንክ እና ኅብረ ሕዋስ አገልግሎት ኀላፊ ምክሩ ሽፈራው ዛሬ የተመረቀው የዲጂታል ሲስተም የደም ማቀዝቀዣ ማዕከል በአማራ ክልል የመጀመሪያ መኾኑን ገልጸዋል።

የማቀዝቀዣ ማዕከሉ በአንድ ጊዜ እስከ 5ሺህ ከረጢት መያዝ የሚችል ነው ብለዋል። ይህም በቂ ደም በመሠብሠብ በአግባቡ ለተጠቃሚዎች እንዲደርስ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

አማራ ኮሙኒኬሽን

‎የጡት ማጥባት አስፈላጊነት እና ጥቅሞች‎___________‎‎የጡት ማጥባት ለሕፃናት ጤናማ እድገትና የበሽታ መከላከል አቅም እንዲሁም ለእናቲቱ ጤና እጅግ አስፈላጊ የሆነ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው...
05/08/2026

‎የጡት ማጥባት አስፈላጊነት እና ጥቅሞች
‎___________

‎የጡት ማጥባት ለሕፃናት ጤናማ እድገትና የበሽታ መከላከል አቅም እንዲሁም ለእናቲቱ ጤና እጅግ አስፈላጊ የሆነ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው። ህጻናት በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት የእናት ጡት ወተት ብቻ (Exclusive Breastfeeding) ማግኘት አለባቸው።

‎👉በጡት ማጥባት ወቅት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ፦

‎▪️የመጀመሪያውን ወተት (እንገር / Colostrum) ለህጻኑ ይስጡ:- እንገር የመጀመሪያው የእናት ወተት ሲሆን ሕፃኑን ከበሽታዎች የሚጠብቅ በጣም ከፍተኛ የመከላከያ ኃይል ያለው ነው። ይህ ወተት ከፍተኛ የበሽታ መከላከል አቅም ያላቸውን ንጥረ ነገሮች ይዟል።

‎▪️ጡት ማጥባትን በመጀመሪያው 1 ሰዓት ውስጥ ይጀምሩ:- ሕፃኑ ከተወለደ በኋላ በመጀመሪያው 1 ሰዓት ውስጥ ጡት ማጥባት መጀመር ለሕፃኑ ሕይወት ማዳን፣ ለእናቱም ፈጣን ማገገም ይረዳል። እንዲሁም የጡት ወተት ምርት በቶሎ እንዲጀምር እና በቂ የሆነ ወተት እንዲመነጭ ያደርጋል።

‎▪️ህጻኑ/ኗ በፈለገ/ች ጊዜ ያጥኑ:- ሕፃኑ/ኗ በፈለገ/ች ጊዜ በቀንና በሌሊት በተደጋጋሚ ጡት ያጥቡ። ይህ የወተት ምርትን ያበረታታል።

‎▪️ትክክለኛ የማጥባት ሁኔታን ይጠቀሙ (Positioning & Latching)፦ በአግባቡ ለማጥባት እናቲቱ በተመች ሁኔታ ተቀማጣ ማጥባት አለባት። ሕፃኑ አፉን በደንብ ከፍቶ ጠቆር ያለዉን የጡትዎን ክፍል አብዛኛዉን በመጉረስ፣ ጉንጮቹ ሞላ በመድረግና በመሀል ትንሽ እያረፈ በደንብ መሳቡን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡

‎▪️ሙሉ በሙሉ በጡት ወተት ብቻ ማሳደግ፦ በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ውስጥ ውሃን ጨምሮ ምንም አይነት ተጨማሪ ምግብ ወይም ፈሳሽ ሳይሰጥ በጡት ወተት ብቻ ህጻናትን ማሳደግ ይገባል። ይህም የጡት ወተት በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ለህጻናት እድገት የሚያስፈልጉትን ንጥረ ምግቦች እንዲሁም ውሃን ስለሚይዝ ነው።

‎▪️የበሽታ መከላከል ጥቅሞች፦ የጡት ወተት ሕፃናትን ከተቅማጥ፣ ከሳንባ ነቀርሳ (Pneumonia) እና ከጆሮ ኢንፌክሽን የሚከላከል ሲሆን እናቶችንም ከጡት እና ከማህፀን ካንሰር ተጋላጭነት ይከላከላል።

‎▪️በህመም ወቅት ጨምረው ጡት ያጥቡ:- ከ 6 ወር በታች የሆኑ ህጻናት በተለያየ ህመም በሚጠቁበት ወቅት ከሌላ ጊዜ አብልጠው/ጨምረው ያጥቡ። ይህም በህመም ወቅት በሽታን ለመቋቋም እንዲሁም በቶሎ ለማገገም ይረዳቸዋል።

‎▪️ከ6 ወር ጀምሮ(181 ቀን) ከተጨማሪ ምግብ ጎን ለጎን ጡት ማጥባትን ይቀጥሉ:- ከ 181ኛ ቀን ጀምሮ እድሜውን የሚመጥን፣ የተመጣጠነና የተሰባጠረ ተጨማሪ ምግብ በመጀመር ጡት ማጥባቱን እስከ 2 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ይቀጥሉ።

‎▪️የበቂነት ምልክቶች፦ ሕፃኑ በቀን ቢያንስ ከ6-8 ጊዜ የሚሸና ከሆነ እና በቂ የክብደት እድገት የሚያሳይ ከሆነ፥ ህጻኑ በቂ ወተት ማግኘቱን ማረጋገጥ ይቻላል።

‎▪️የእናቶች ስነ-ምግብ ሁኔታ፦ የሚያጠቡ እናቶች ከሌላው ጊዜ ተጨማሪ ሁለት ጊዜ የተሰባጠረ ምግብ ማገኘት የሚገባዘው ሲሆን፣ በቂ ፈሳሽ (ውሃ፣ ሾርባ) እና አትክልትና ፍራፍሬዎችንም አብዝተው መመገብ ይኖርባቸዋል።

‎👉 የአባቶች እና የቤተሰብ ሚና፦
‎የቤት ውስጥ ስራዎችን ማገዝ፦ አባቶችና ቤተሰብ የሚያጠቡ እናቶችን በቤት ውስጥ ስራ በማገዝ በቂ የእረፍት ጊዜ እንዲኖራቸው ማድረግ አለባቸው።
‎‎▪️ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ መስጠት፦ በእናቶች ላይ የሚፈጠረውን ድካም እና ጭንቀት ለመቀነስ አዎንታዊ እና ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ ማድረግ ወሳኝ ነው።
‎‎▪️የተመጣጠነ ምግብ ማቅረብ፦ እናቲቱ በቂ እና የተመጣጠነ ምግብ ማግኘቷን ማረጋገጥ እና ማበረታታት

Address

Amhara Regione
Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahir Dar City Adminstration Zonal Health Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share