Amhara Water Development Fund

Amhara Water Development Fund Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara Water Development Fund, Government Organization, Bahir Dar.

Amhara Water Development Fund is an Institution established to be the main source of fund for the supply of potable water and provision of sanitation services in Amhara Region.

02/06/2026

#የውኃ መስመሮች እንክብካቤና የጋራ ኃላፊነታችን

ውኃ የሕይወት መሠረት፣ የጤናችንና የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ዋስትና ነው። ንጹሕ የቧንቧ ውኃ እስከ ቤታችን ድረስ ተደራሽ እንዲሆን የውኃ መስመሮች (አውታሮች) የሚጫወቱት ሚና በቀላሉ የሚገመት አይደለም። ይሁን እንጂ እነዚህን ውድ ንብረቶች መጠበቅና መንከባከብ የመንግሥት ወይም የባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው።


1. የውኃ መስመሮችን መንከባከብ ለምን አስፈለገ?

ብክነትን ለመቀነስ፦ በየቀኑ በሚያፈሱና በተሰበሩ መስመሮች ምክንያት የሚባክነው ውኃ ከፍተኛ ነው። መስመሮቹን በመጠበቅ የውኃ እጥረትን መቅረፍ ይቻላል።

ንጽሕናን ለመጠበቅ፦ የተበላሹና የተቀደዱ የውኃ ቧንቧዎች ቆሻሻና ተላላፊ በሽታ አምጪ ተህዋስያን ወደ ንጹሑ ውኃ እንዲገቡ በር ይከፍታሉ።

የንብረት ውድመትን ለመከላከል፦ የመስመሮች መፍሰስ የመንገዶች መበላሸትን፣ የህንጻዎች መሠረት መዳከምንና የአፈር መሸርሸርን ያስከትላል።


2. የእኛ ድርሻ እና ኃላፊነት ምንድን ነው?

"ንጹሕ ውኃ ለሁሉም እንዲደርስ፤ እያንዳንዱ የውኃ ቧንቧ ጥበቃ ያስፈልገዋል!"

አርቆ ማሰብና ጥንቃቄ ማድረግ፦ በየአካባቢያችን ግንባታዎችን ስናከናውን፣ መሠረተ ልማት ስንዘረጋ ወይም ለእርሻና ለተለያዩ ሥራዎች መሬት ስንቆፍር የውኃ መስመሮች እንዳይበጠሱ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ።

ፈጣን ጥቆማ መስጠት፦ በየመንገዱም ሆነ በሕዝብ መገልገያ ቦታዎች ላይ የውኃ መፍሰስ (ሊኬጅ) ሲያጋጥም፣ ሳይዘገዩ በአቅራቢያዉ ላለ የዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ቅርንጫፍ በአካል ወይም በስልክ ጥቆማ መስጠት።

ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን መከላከል፦ ያለአግባብና ያለቆጣሪ ከመስመር ውኃ መጥለፍን (ሕገ-ወጥ ቅጥያ) መከላከልና መቆጣጠር። ይህ ድርጊት የውኃ ግፊትን ከመቀነሱም በላይ የሌሎችን ዜጎች ዉኃ የማግኘት መብት ይጋፋል።

የውስጥ መስመሮችን መፈተሽ፦ በየቤታችንና በየተቋማቶቻችን ያሉትን የውኃ መውረጃዎች፣ ቧንቧዎችና የፊቲንግ ዕቃዎች በየጊዜው በመፈተሽ ብልሽቶችን በፍጥነት ማስተካከል።


የውኃ መስመሮችን በአግባቡ መያዝ ማለት የራሳችንን ጤና፣ ኢኮኖሚና የወደፊት ሕይወት መንከባከብ ማለት ነው። ዛሬ የምናደርገው እያንዳንዷ ጥንቃቄ ነገ ለልጆቻችን የሚተርፍ ንጹሕ መሠረተ ልማት ለመገንባት መሠረት ነው።

#ኃላፊነታችንን እንወጣ፤ የውኃ መስመሮቻችንን እንጠብቅ!
የባህር ዳር ከ/መ/ዉ/ፍ/አገ/ድርጅት

ለባሕር ዳር ከተማና ለአካባቢው ማህበረሰብ ደህንነቱ የተጠበቀ፣አስተማማኝ፣ዘላቂና በተመጣጣኝ ዋጋ የዉኃና ፍሳሸ አገልግሎቶችን ማቅረብ።
Provide Safe, Reliable, Sustainable and Affordable water and sewerage service to Bahir Dar city and the serawunding.

የላሊበላ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ  በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።በላሊበላ ከተማ አስተዳደር የንፁህ መጠጥ ውሃን ለከተማዋ ማህበረሰብ ለማቅረብ ያስቻሉ በርካታ ስራዎ...
29/05/2026

የላሊበላ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።

በላሊበላ ከተማ አስተዳደር የንፁህ መጠጥ ውሃን ለከተማዋ ማህበረሰብ ለማቅረብ ያስቻሉ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን የላሊበላ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል።

ድርጅቱ የውሃ አቅርቦቱን ለማዘመን ያስቻሉ ማሻሻያዎች መስራቱን ነው ያስታወቀው።

የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ መለሰ አየለ ፦ከአለም አቀፉ ቀይ መስቀል ድርጆት ጋር በመሆን የከተማውን የንፁህ መጠጥ ውሃ እጥረት ለመቅረፍ ያስቻሉ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ነው ያነሱት።

ከ100ሺህ ያላነሰ ማህበረሰብን እያገለገሉ መሆኑን ያነሱት ሃላፊው ቀደም ሲል ከሹም ሽሃ ተስቦ የመጠውን ውሃ ፣ማቀባበያ ጣቢያዎች የኤሌክትሮ መካኒካል ዕቃዎችን የማዘመን ስራ መሰራቱን ነው የገለፁት።

ስድስት ቦታዎች ላይ የሶላር ፕሮጀክቶች መገንባታቸውንና
የውሃ የማቀባበያ ጣቢያዎችን ሙሉ በአዲስ እቃዎች መቀየር መቻሉም ነው የተገለፀው።

ከዚህ ቀደም በመብራት ብቻ ይገፋ የነበረውን የንፁህ መጠጥ ውሃ ከመብራት በተጨማሪ በሶላር ሌትና ቀን ውሃን በመግፋት ለማህበረሰቡ የማድረስ ስራ እየተሰራ መሆኑም ነው የተገለፀው።

በአለም አቀፉ ቀይ መስቀል ማህበር ከ400 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የንፁህ መጠጥ ውሃን በሶላር ለማድረስ የሚያስችል ስራ መሰራቱን ነው ሃላፊው የገለፁት።

ተቋሙ በራሱ ወጭ በከተማው በተለያዩ አካባቢዎች ቦኖዎችን በመስራት ለማህበረሰቡ የንፁህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ እያደረገ ስለ መሆኑም ተመላክቷል።

አምስት ተጨማሪ የንፁህ መጠጥ ውሃ መገኛ ቦታዎችን የመለየት ስራ መሰራቱን የገለፁት የድርጅቱ ሃላፊ መለሰ አየለ ከውሃ ቢሮና ከፌደራል ተቋማት ጋር በመሆን የውሃ ጉድጓዶችን ለመቆፈር እየተሰራ ስለ መሆኑም ነው ያነሱት።

የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን በተሰሩ ስራዎች የቆጣሪ ንባብና የውሃ ክፍያን ወደ ድጅታል በመቀየርና ከባንኮች ጋር በማስተሳሰር ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ነው ከድርጅቱ የተገኘው መረጃ የሚያመለክተው።

26/05/2026

ዒድ ሙባረክ!

የአብክመ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች @ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።

በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የመረዳዳትና የአብሮነት እንዲሆን ከልብ ይመኛል።

ዒድ ሙባረክ!
አብክመ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት

በ340 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በአማራ ክልል ለሚገነቡ 12 የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች የጥልቅ ውኃ ጉድጓድ ቁፋሮ ውል ተፈረመ።የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል ለሚገኙ 12 የመጠጥ ውሃ ፕ...
23/05/2026

በ340 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በአማራ ክልል ለሚገነቡ 12 የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች የጥልቅ ውኃ ጉድጓድ ቁፋሮ ውል ተፈረመ።

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል ለሚገኙ 12 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ በ340 ሚሊየን 288 ሺ 311 ብር ወጪ ከውኃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ጋር ነው የውል ስምምነት የተፈረመው።

ፕሮጀክቱ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃኃ ልማት ፕሮጀክት አካል ሲሆን፣ ተቋራጩ ተቋም የጉድጓድ ቁፋሮ እና ተያያዥ የውኃ ሥራዎችን በ60 ቀናት ውስጥ አጠናቆ ለማስረከብ ውል መውሰዱ ተገልጿል።

“ይህ ፕሮጀክት በተለይ የውሃ እጥረት በሚስተዋልባቸው አካባቢዎች ለሚኖሩ ዜጎች እፎይታ የሚፈጥር ነው” ያሉት አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የሚኒስቴሩ ሚኒስትር ዴኤታ።

የውኃ ስራዎች ኮንስትራክሽን በበኩሉ፣ የተሰጠውን ሥራ በተፈለገው የጥራት ደረጃ እና በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።

ፕሮጀክቶቹ በዓለም ባንክ ድጋፍ የሚገነቡ መሆኑም ተገልጿል።

22/05/2026
የአብክመ ዉኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ከወልድያ ከተማ መጠጥ ዉኃና ፍሳሽ አገልገሎት ድርጅት ጋር በመተባበር ለድርጅቱ ሰራተኞችና አመራሮች  ስልጠና ተሰጥቷል።በክልሉ የሚገኙ የከተማ መጠጥ ዉኃና ...
21/05/2026

የአብክመ ዉኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ከወልድያ ከተማ መጠጥ ዉኃና ፍሳሽ አገልገሎት ድርጅት ጋር በመተባበር ለድርጅቱ ሰራተኞችና አመራሮች ስልጠና ተሰጥቷል።
በክልሉ የሚገኙ የከተማ መጠጥ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶች ለሰዉ ልጅ ህይወት ህይወት የሚሰጠዉን ንጹህ የመጠጥ ዉኃ እንዲያርቡ ኃላፊነት የተሰጣቸዉ አካላት ናቸዉ። የንጽህ መጠጥ ዉኃ አቅርቦት ደግሞ ከተፈጥሮ እስከ በሰዉ ሰራሽ ችግሮች የተተበተበ እንደሆነ ይታወቃል። ከእነዚህ ችግሮች አንዱ እና ዋንኛዉ የአቅም ዉስንነት ነዉ። ጽ/ቤቱ ከዚህ ቀደም ክልሉን በአራት ቀጠና በመክፈል የድርጅት ስራ አስኪያጆችንና የስራ አስተባባሪዎችን በተለያዩ ጉዳዮች ስልጠና እንደሰጠ ይታወቃል። አሁን ደግሞ በየከተሞቹ በመንቀሳቃስ ለድርጅቱ መላ ሰራተኞች በተመረጡ አጀንዳዎች ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። በዚህም መሰረት ለወልድያ ከተማ መ/ዉ/ፍ/አገ/ድርጅት ሰራተኞች እና አመራሮች በተቋም ግንባታ ምንነት እና አስላጊነት፣ በለዉጥ ምንነትና አስላጊነት፣ በጊዜ እና የጊዜ አጠቃቀም እንዲሁም አገልግሎት እና ጥራት ያለዉ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ስልጠና መስጠት ተችሏል። ስልጠናዉን የተከታተሉ ሰልጣኞች አንደዚህ አይነት ስልጠናዎች ለዉጥ እስኪመጣ ድረስ ተጠናክረዉ ሊሰጡ ይገባል ብለዋል። በተለይም ደግሞ ሰራተኛዉ የአመለካከትና የአስተሳስብ ለዉጥ በማምጣት በዘርፉ የሚስተዋሉ በርካታ ችግሮችን በመፍታት ህብረተሰቡን ማገልገል እንዳለባቸዉ ይህ ስልጠና አንደሚጠቅማቸዉ ተናግረዋል። እኛም አቅም በፈቀደ መጠን ከተሞች የሚገጥማቸዉን ችግሮች በራስ አቅም እንዲቀርፉ ጥረታችንን አጠናክረን የሚቀጥል ሲሆን በቀጣይ በተለያዩ ከተሞች በመገኘት ስልጠናዉን የምንሰጥ ይሆናል። ይህ ስልጠና እንዲሳካ ላደረጉ የወልደያ ከተማ መጠጥ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የስራ አመራሮች በተለይም ስራ አስኪያጁ ለአቶ ጌታቸዉ ሞገስ በታላቅ ክብር ምስጋናችንን እናቀርባለን።

የባሕር ዳር ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በፌደራል ዉኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስተባባሪነት የውሃና መሬት ሃብት ማዕከል /WLRC/ ብራይት /BRIGHT/ ፕሮጀክት በተገኘ የሁለት ሚሊዮን ብር...
18/05/2026

የባሕር ዳር ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በፌደራል ዉኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስተባባሪነት የውሃና መሬት ሃብት ማዕከል /WLRC/ ብራይት /BRIGHT/ ፕሮጀክት በተገኘ የሁለት ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ በባሕር ዳር ዙሪያ ወረዳ ለወገልሳ ቀበሌ ነዋሪዎች የሁለት የማህበረሰብ አቀፍ የዉኃ ቦኖ ግንባታ እና የዉኃ ፓይፕ ዝርጋታ ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡

ለግንባታዉ የሚያስፈልግ ቁሳቁስ ግዢ ተፈፅሞ ወደ ማዕከሉ የተጓጓዘ ሲሆን የዉኃ መስመር ቁፋሮና ፓይፕ ዝርጋታ እንዲሁም የዉኃ ቦኖ ግንባታ ስራዉ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ስራዉ ከተጠናቀቀ በኋላ የወገልሳ ቀበሌ ድንጋይ ጎጥ ነዋሪዎች የንፁህ መጠጥ ዉኃ ችግራቸዉ ይቀረፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ2.1 ሚሊዮን በላይ  ደርሷልደሴ ፣ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ደቡብ ወሎ ኮሙዩኒኬሽን)የደቡብ ወሎ ዞን ውኃና ኢነርጂ መምሪያ የዘ...
29/04/2026

በደቡብ ወሎ ዞን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚዎች ቁጥር ከ2.1 ሚሊዮን በላይ ደርሷል

ደሴ ፣ሚያዚያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ደቡብ ወሎ ኮሙዩኒኬሽን)

የደቡብ ወሎ ዞን ውኃና ኢነርጂ መምሪያ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ጋር በደሴ ከተማ ገምግሟል።

በመድረኩ ላይ በውኃ ግንባታ፣ በጥገና እና በኢነርጂ ቴክኖሎጂዎች ስርጭት ረገድ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ጌታቸው ፅጌ እንደገለጹት፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለመጠጥ ውኃ ግንባታ ከ45 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲሁም ለጥገና ሥራዎች ከ24.4 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ፣ በጉልበትና በቁሳቁስ የማሰባሰብ ሥራ ተከናውኗል።

በበጀት ዓመቱ 530 የመጠጥ ውኃ ተቋማትን ለመገንባት ታቅዶ 331 የሚሆኑት ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

በዚህ የግንባታ ሂደት 149 ሺህ 964 አዲስ ተጠቃሚዎችን ማፍራት የተቻለ ሲሆን፣ በዞን ደረጃ አጠቃላይ የንጹህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ ዜጎች ቁጥር ከ2.1 ሚሊዮን በላይ ደርሷል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት የንጹህ መጠጥ ውኃ ሽፋኑን በ1.27 በመቶ በማሳደግ አጠቃላይ የዞኑን ሽፋን 70.77 በመቶ ማድረስ ተችሏል።

በአፈጻጸም ረገድ ከለላ፣ መቅደላ፣ ተንታ እና ለጋምቦ ወረዳዎች ከፍተኛ ውጤት ሲያስመዘግቡ፤ በአንጻሩ ቦረና፣ አምሓራ ሳይንት፣ ጃማ፣ አርጎባ፣ ወግዲ እና መሐል ሳይንት ወረዳዎች ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየባቸው መሆኑ ተጠቁሟል።

የውኃ ተቋማትን ዘላቂነት ለማረጋገጥ ሰፊ የጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል፦2 ሽህ 250 ተቋማት ቀላል ጥገና፣ 1ሽህ 497 መካከለኛ ጥገና እና 595 ተቋማት ደግሞ ከባድ ጥገና ተደርጎላቸዋል።

በዚህም ምክንያት የውኃ ተቋማት የብልሽት ምጣኔ ከነበረበት 23 በመቶ ወደ 20 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
የማኅበረሰቡን የኃይል አጠቃቀም ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት፦ማገዶ ቆጣቢ ቴክኖሎጂ፦ 35 ሺህ ለማሰራጨት ታቅዶ 33 ሺህ 826 የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎች ተሰራጭተዋል። (መቅደላ፣ ወረኢሉ፣ ወግዲ፣ ከለላ፣ ተንታ፣ አልብኮ እና ጃማ ወረዳዎች የተሻለ አፈጻጸም አሳይተዋል።)

ባዮ ጋዝ፦ 568 ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ የ311 ፕላንቶች ግንባታ ተጠናቋል።ቀሪዎቹ በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ አቶ ጌታቸው ገልጸዋል፡፡

የሶላር ቴክኖሎጂ፦ 3ሽህ 859 ሶላር ላንተርን እና ከ3 ሺህ በላይ ሶላር ሆም ሲስተሞች ለማኅበረሰቡ ተደራሽ ሆነዋል።

በግምገማ መድረኩ ማጠናቀቂያ ላይ፣ በቀሪዎቹ ወራት የታዩ ጉድለቶችን በማስተካከልና ግንባታዎችን በማጠናቀቅ የዓመቱን ዕቅድ በስኬት ለማጠናቀቅ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

25/04/2026
የአብክመ ዉኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።የአብክመ ዉኃ ልማት ፈንድ ጽ...
11/04/2026

የአብክመ ዉኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

የአብክመ ዉኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አደም ወርቁ የ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እና ለተቋሙ አባላት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዋና ስራ አስኪያጁ በመልእክታቸው በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ በመልዕክታቸዉ በክርስትና እምነት ተከታዮች የትንሳኤ በዓል ጨለማ በብርሃን የተተካበት ፣ ሞት ድል የተነሳበት ታላቅ ሃይማኖታዊ በዓል በመሆኑ ከምንም በላይ ታላቅ ፍቅር የተገለጠበት፣ እርቅና ሰላም የሰፈነበት ህዝበ ክርስቲያኑ የተጣሉትን በማስታረቅ፣ የተራቡትን ማዕድ በማጋራትና የተቸገሩትን በመርዳት ሊያከብረው እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይም በሀገራችን ያለውን የአብሮነትና የመደጋገፍ እሴት በማጠናከር በዓሉን ሁሉም በደስታ፣ በፍቅርና በሰላም እንዲያሳልፉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ዋና ስራ አስኪያጁ አያይዘውም በዓላትን ስናከብር ለንፁህ መጠጥ ዉኃ እና ለስነ ንፅህና ጉዳዮች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሊሆን ይገባል። ዉኃ ህይወት ላለዉ ፍጥረታት ሁሉ እጅግ አስፈላጊ እና በማንኛዉም ሁኔታ ላይ ሁነን ልናጣዉ የማይገባ የተፈጥሮ ሀብት ነዉ። ስለሆነም የዉኃ ሀብታችንና አካላትን መጠበቅ እና መንከባከብ፣ ከብክለት እና ከብክነት መከላከል የዘወትር ስራችን ሊሆን ይገባል።

ከዚህ በተጨማሪም የአብክመ ዉኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት እንደ ተቋም የተቋቋመዉ ህብረተሰቡ ዘላቂ የንፁህ መጠጥ ዉኃ እና የሳኒቴሽን አገልግሎት እንዲያገኝ የፋይናንስ ክፍተቱን ለመሙላት እና ድርጅቶች እራሳቸዉን ችለዉ ህዝባቸዉን ተጠቃሚ ለማድረግ ነዉ። ስለሆነም የከተማ መጠጥ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶች ጽ/ቤቱን ለማጠናከር በሚደረገዉ ጥረት የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እና ግዴታችሁን በመወጣት አጋርነታችሁን እንድታሳዩን በማለት ያሳሰቡ ሲሆን በመጨረሻም ማህበረሰቡ በአሉን ሲያከብር ዉኃን በቁጠባ በመጠቀም እና በንጽህና በመያዝ እንዲሆን ያሉት ዋና ስራ አስኪያጁ በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ እና የፍቅር እንዲሆን በድጋሜ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Address

Bahir Dar
088

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Water Development Fund posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share