Amhara Water Development Fund

Amhara Water Development Fund Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara Water Development Fund, Government Organization, Bahir Dar.

ANRS Office of Water Development Fund is an Institution established to be the main source of fund for the supply of potable water and provision of sanitation services in Amhara Region.

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽህፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት በ4 ከተሞች  ለንፁህ መጠጥ ውኃ ማስፋፊያ የሚውል 59 ሚሊዬን ብር ብድር ሰጥቷል።--------------------------...
04/09/2026

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽህፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት በ4 ከተሞች ለንፁህ መጠጥ ውኃ ማስፋፊያ የሚውል 59 ሚሊዬን ብር ብድር ሰጥቷል።
-------------------------------------
የጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አደም ወርቁ እንደገለጹት የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት በከተሞች የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን ለማሳደግ የሃገር ውስጥ የፋይናንስ አቅም ለመፍጠር የተቋቋመ ነው።

በመሆንም ለከተሞች የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ማስፋፊያ የሚውል የብድር አገልግሎት በረዥም ጊዜና በአነስተኛ ወለድ በማቅረብ፣ የገቢ አቅማቸውን በማሳደግ፣ የቀረብውን ብድር በማስመለስ ሌሎች ከተሞችንም በተመሳሳይ ተጠቃሚ ለማድረግ የተቋቋመ ነው ጽህፈት ቤቱ።

ጽ/ቤቱ ሲቋቋም የመነሻ ሃብት ያልነበረው ቢሆንም በተከታታይ አመታት በተሰራው ስራ በየበጀት ዓመቱ እያደገ ያለ የብድር አመላለስና የብድር አቅርቦት እያደረገ እንደሚገኝም የጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመትም ከሰበሰበው ሃብት 40 ሚሊዬን ብር ለከተሞች ለማበደር አቅዶ የብድር አመላለሱን በማሳደግና ተጨማሪ ፋይናንስ በማፈላለግ 59 ሚሊዬን ብር ለከተሞች በብድር አቅርቧል።

በዚህም የጎንደር፣ የዳንግላ፣ አገው ግምጃ ቤት እና አርጎባ ልዩ ወረዳ መዲና ከተማ ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል።

ጽ/ቤቱ በ2019 የበጀት ዓመት ክልሉ ባለው የመልማት አቅም ልክ ሃብት ለመሰብሰብ፣ የተሻለ ብድር ስርጭት ለማድረግና ለማስመለስ የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አስታውቋል።

"የንጹህ መጠጥ ውኃ ተደራሽነትን በራስ አቅም  ለማሳደግ የኢንቨስትመንት ወጭና ገቢ ስርዓቱ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል።"ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር-ኢ/ር)የአብክመ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ከው...
04/09/2026

"የንጹህ መጠጥ ውኃ ተደራሽነትን በራስ አቅም ለማሳደግ የኢንቨስትመንት ወጭና ገቢ ስርዓቱ ላይ በትኩረት መስራት ይገባል።"
ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር-ኢ/ር)

የአብክመ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ከውኃና ኢነርጂ መምሪያዎች እና ከከተማ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶች ጋር የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል።

የአብክመ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር-ኢ/ር) ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤቱ የክልሉን የንጹህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ለማሻሻል ሰፊ ስራ እየሠራ እንደሆነ ገልጸው፥ ተቋማት በብድር የወሰዱትን ገንዘብ ለታለመለት ዓላማ በማዋልና በወቅቱ በመመለስ የኢንቨስትመንት ወጭና ገቢ ስርዓቱን ማፋጠን ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አደም ወርቁ በበኩላቸው በ2018 በጀት ዓመት ለከተሞች የንፁህ መጠጥ ውኃ ማስፋፊያ የሚውል 59 ሚሊዬን ብር ብድር ተሰጥቷል። ሲሉ ተናግረዋል።

የአማራ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት የተቋቋመለት ዓላማ የውኃ ልማት ኃብት አቅምን በማሰባሰብ መልሶ ለከተሞች የውኃ ልማት ማስፋፊያ እንዲውል የብድር አገልግሎት መስጠትና ከተሞች በብድር የወሰዱትን ሃብት ለታለመለት ዓላማ እንዲያውሉትና የህዝብን የመጠጥ ውኃ ችግር በዘላቂነት እንዲፈቱበት የሚያስችል የስልጠናና የክትትል ድጋፍ ስራ ይሰራል።

ጽ/ቤቱ ሲቋቋም የመነሻ ሃብት ያልነበረው ቢሆንም በተከታታይ አመታት በተሰራው ስራ በየበጀት ዓመቱ ከዕቅድ በላይ የሆነ የሃብት አሰባሰብና የብድር ስርጭት እያደረገ እንደሚገኝ የጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አደም ወርቁ ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ከሰበሰበው ሃብት 40 ሚሊዬን ብር ለከተሞች ለማበደር የታቀደ ሲሆን 59 ሚሊዬን ብር ከዕቅድ በላይ አፈፃፀም አሳይቷል።

በዚህም ዳንግላ፣ ጎንደር፣ አገው ግምጃ ቤት ከተማዎች እና አርጎባ ልዩ ወረዳ ወረዳ መዲና ከተማ በበጀት ዓመቱ የብድር አገልግሎቱ ተጠቃሚዎች መሆናቸው ተገልጿል።

የውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤቱ ክልሉ ባለው የመልማት አቅም ልክ ሃብት ለመሰብሰብ፣ የተሻለ ብድር ስርጭት ለማድረግና ለማስመለስ የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከባለድርሻ ተቋማት ጋር ያለ ቅንጅት፣ የብድር አገልግሎት የሚውል ሃብት በበቂ ሁኔታ መመደብ፣ የፕሮጀክቾች አጠቃላይ አፈፃፀም የተሟላ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸውም ተብሏል።

በመድረኩ የአብክመ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር- ኢ/ር) የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።

በበጀት በዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም የነበራቸው መምሪያዎችና የከተማ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶች እውቅና ተሰጥተዋል።

30/08/2026

I got over 50 reactions on my posts last week! Thanks everyone for your support! 🎉

"የመጠጥ ውኃና አነርጂ ዘርፍን ጥራት ለማረጋገጥ የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ ይገባል" – ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር ኢንጂነር)የውኃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ~~~~~~~~~~~~~~የአማራ ክልል ውኃና ...
30/08/2026

"የመጠጥ ውኃና አነርጂ ዘርፍን ጥራት ለማረጋገጥ የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ ይገባል" – ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር ኢንጂነር)
የውኃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ
~~~~~~~~~~~~~~
የአማራ ክልል ውኃና ኢነርጂ ቢሮ የውኃ ልማት ሥራዎችን በጥራትና በተሻለ ብቃት ለማከናወን የባለሙያዎችን ዕውቀትና ክህሎት ማሳደግ ዋነኛ ትኩረቱ መሆኑን የቢሮ ኃላፊው ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር ኢንጂነር) ገለጹ።

የመጠጥ ውኃ ለሰው ልጅ ሕልውና መሠረታዊ በመሆኑ፣ ጥራት ያለው የውኃ መረብ ዲዛይን፣ በግንባታ ወቅት ጥራትና የጊዜ ገደብ ጠብቆ መሥራት እንዲሁም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በኢነርጂ ዘርፍ ማስፋፋት የባለሙያዎች አቅም ላይ የተመሠረተ መሆኑን አስገንዝበዋል።

20/08/2026

What is Water Supply Design ❔❓
የውሃ አቅርቦት ዲዛይን ምንድነው
📶 የውሃ አቅርቦት ዲዛይን ማለት ከተፈጥሯዊ ምንጭ ወደ ተጠቃሚዎች ንጹህ፣ በቂ እና የማያቋርጥ ውሃ ለማድረስ የሚያስችል ሙሉ ስርዓት ለመንደፍ የሚያገለግል የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ነው። ይህ ስራ ቧንቧ መዘርጋት ብቻ አይደለም ሂደቱ የሃይድሮሊክስ፣ የአካባቢ ሳይንስ፣ የሕዝብ ጤና እና የመሠረተ ልማት እቅድ የሚያካትት ሙሉ ስርዓት ዲዛይን ንድፍ ነው።
በመሠረቱ ዓላማው ቀላል ነው፡ ውሃን ከሚገኝበት ቦታ ወደ ሚፈለግበት ቦታ በትክክለኛ ጥራት፣ መጠን እና ግፊት በተረጋጋ እና በዘላቂ መንገድ ማድረስ።
1. የውሃ አቅርቦት ዲዛይን የሚያካትተው ምንድነው
ትክክለኛ ዲዛይን የውሃ መንገድ ሙሉ የሕይወት ሂደትን ያካትታል፦
1. የውሃ ማሰራጨት (Abstraction)
ውሃን ከምንጭ (ወንዝ፣ ሐይቅ፣ ከመሬት በታች ውሃ፣ ዝናብ) መውሰድ።
2. ማስተላለፊያ (Conveyance)
ጥሬ ውሃን ወደ ማጣሪያ ተቋም ማጓጓዝ።
3. ማጣሪያ (Treatment)
አካላዊ፣ ኬሚካላዊ እና ባዮሎጂካል ብክለቶችን ማስወገድ።
4. ማከማቻ (Storage)
የፍላጎት መለዋወጥን ለማመጣጠን ታንኮች ወይም ሪዘርቫይሮች መጠቀም።
5. ስርጭት (Distribution)
በቧንቧ መረብ ውሃን ለተጠቃሚዎች ማድረስ።
2. ለምን ይህ ዲዛይን አስፈላጊ ነው
ትክክል ያልሆነ ዲዛይን ብቻ አይተገበርም በተግባር ለውጥን ይፈጥራል፦
• የበሽታ መተላለፍ (ንጹህ ያልሆነ ውሃ)
• ቋሚ እጥረት (ትንሽ የተነደፈ ስርዓት)
• ቧንቧ መፈንዳት (ከፍተኛ ግፊት)
• ከፍተኛ የኃይል ወጪ (ያልተቀናጀ ፓምፕ ስርዓት)
• የተሳሳተ ስርጭት (እኩል ያልሆነ መዳረሻ)
3. የሚካተቱ የኢንጂነሪንግ ዘርፎች
ይህ ዲዛይን ብዙ ዘርፎችን ያጣምራል፦
• ሃይድሮሊክስ – ፍሰት፣ ግፊት፣ የኃይል መጥፋት
• ሃይድሮሎጂ – ዝናብ፣ የወንዝ ፍሰት፣ የመሬት ውሃ
• የአካባቢ ኢንጂነሪንግ – የውሃ ጥራት እና ብክለት መቆጣጠር
• ሲቪል ኢንጂነሪንግ – ቧንቧ፣ ታንክ፣ ሪዘርቫይር ንድፍ
• የከተማ እቅድ – የሕዝብ መጨመር እና የመሬት አጠቃቀም
• የሕዝብ ጤና ኢንጂነሪንግ – በውሃ በሽታ መከላከል
4. መሠረታዊ መርህ: ፍላጎት vs አቅርቦት
ስርዓቱ ሁልጊዜ ሚዛን ይፈልጋል፦
• ፍላጎት በሰዓት ይለዋዋጣል
• በቀን ይለዋዋጣል
• በወቅት ይለዋዋጣል
• በዓመት ይጨምራል
👉 ስለዚህ ዲዛይኑ ይህን ሁሉ መቆጣጠር አለበት፦
• አማካይ ፍላጎት
• ከፍተኛ የቀን ፍላጎት
• ከፍተኛ የሰዓት ፍላጎት
5. ዋና የዲዛይን መለኪያዎች
• የወደፊት ሕዝብ ብዛት (Design Population)
• የሰው በቀን የውሃ ፍላጎት (Per capita demand)
• አጠቃላይ ፍላጎት
• ፍሰት፣ ፍጥነት፣ ግፊት
• የንድፍ ጊዜ (20–30 ዓመት ያህል)
6. የስርዓቱ አመክንዮ
ጥሩ ዲዛይን ይህን መንገድ ይከተላል፦
• ምንጭ መምረጥ
• ምንጩ ፍላጎትን መሸፈን መቻል
• ማጣሪያ
• ማከማቻ
• ስርጭት
• የኃይል እና ኪሳራ መቀነስ
7. የሚገጥሙ ግዴታዎች
• የመሬት ቅርፅ (ተራሮች/ሸለቆ)
• ወጪ ግዴታ
• የውሃ ጥራት ልዩነት
• የቧንቧ እና ቁሳቁስ ገደብ
• ጥገና አቅም
8. በግራቪቲ እና ፓምፕ ስርዓቶች
• በግራቪቲ የሚሰሩ ስርዓቶች
o ውሃ በተፈጥሮ ይፈሳል
o ትንሽ ወጪ
o በጣም አስተማማኝ
• ፓምፕ የሚጠቀሙ ስርዓቶች
o ውሃ በሜካኒክ ኃይል ይነሳል
o ከፍተኛ የኃይል ወጪ
o በጠፍጣፋ መሬት ይፈልጋል
9. የንድፍ አስተሳሰብ (System Thinking)
• ሕዝብ ቢጨምር ምን ይሆናል?
• ፓምፕ ቢበላሽ?
• ድርቅ ቢኖር?
• ፍሳሽ ቢጨምር?
10. የዲዛይን ውጤት
• የስርዓት ካርታ
• የቧንቧ ንድፍ
• የሃይድሮሊክ ስሌቶች
• ፓምፕ መግለጫ
• ታንክ መጠን
• የማጣሪያ ተቋም
• የወጪ ግምት
• የግንባታ እቅድ
11. ቀላል መረዳት
የውሃ አቅርቦት ስርዓትን እንደ ሕያው አካል ብታስብ፦
• ምንጭ = ልብ
• ቧንቧ = ደም ስር
• ፓምፕ = ጡንቻ
• ታንክ = ማከማቻ አካል
• ማጣሪያ = የመከላከያ ስርዓት

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት በአርጎባ ልዩ ወረዳ ከመዲና ከተማ መጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ጋር የ11 ሚሊዮን ብር የብድር ውል ስምምነት ተፈራረመ፡፡ከተሞች የመንግስትን ...
20/08/2026

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት በአርጎባ ልዩ ወረዳ ከመዲና ከተማ መጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ጋር የ11 ሚሊዮን ብር የብድር ውል ስምምነት ተፈራረመ፡፡
ከተሞች የመንግስትን እና ረጂ ድርጅቶች ድጋፍ ሳይጠብቁ በራሳቸው አቅም የውኃ አቅርቦቱን እንዲያሳድጉ አልሞ የሚሰራው የአብክመ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት በበጀት ዓመቱ ለበርካታ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶች የብድር አገልግሎት እየሠጠ ይገኛል፡፡

ጽ/ቤቱ በዛሬው ዕለት ለፕሮጀክት ማስፋፊያና ለኤሌክትሮ ሜካኒካል ማሻሻያ የሚውል 11 ሚሊየን ብር ለመዲና ከተማ በአነስተኛ ወለድ ብድር አበርክቷል፡፡ ብድሩ በ8 ዓመት ውስጥ የሚመለስ ሆኖ የከተማዋን የፋይናንስ ውስንነት በመቅረፍ የውኃ አቅርቦቱን ለማሻሻል ፋይዳው የጎላ ነው፡፡

የመዲና ከተማ መጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ አወል ሰይድ እንደተናገሩት፤ በብድር የተገኘውን ገንዘብ በከተማዉ የዉኃ መስመር ማስፋፊያ እና ለፓምፕ ማሻሻያ አገልግሎት በማዋል የከተማውን ነዋሪ የመጠጥ ውኃ ተደራሽ የምናደርግበት ይሆናል ያሉ ሲሆን፤ ብድሩን በወቅቱ ለመመለስ ቁርጠኞች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ጥያቄያችን ፈጣን ምላሽ በማግኘቱ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አደም ወርቁ በበኩላቸው፤ በክልሉ በንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት በመስጠጥ ኃላፊነት የተሰጣቸዉ ተቋማት ራሳቸዉን ችለው ለህብረተሰቡ ዘላቂነት ያለዉ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ጽ/ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራና እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ጽ/ቤቱ በከተሞች የሚገነቡ የመጠጥ ውኃና ሳኒቴሽን ተቋማትን ለማስፋፋት የሚያስችል አቅም ያለው የፋይናንስ ተቋም ለመሆን ከፍተኛ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ መሆኑን ተከትሎ የብድር አሰጣጥ መስፈርቶችን አሟልተው ፋይናንስ ለሚጠይቁ ከተሞች የብድር አገልግሎቱን ለመፍቀድ ዝግጁ መሆናቸውን ነው ያመላከቱት አቶ አደም፡፡

18/08/2026
የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽሕፈት ቤት ለንጹሕ መጠጥ ውኃና  ሳኒቴሽን  ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ  የማድረግ ተልዕኮውን እየፈጸመ ይገኛል፡፡  አረጋ ካሳ - የአብክመ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ምክ...
18/08/2026

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽሕፈት ቤት ለንጹሕ መጠጥ ውኃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ የማድረግ ተልዕኮውን እየፈጸመ ይገኛል፡፡ አረጋ ካሳ - የአብክመ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ለጎንደር ከተማ መጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የ20 ሚሊዮን ብር የብድር ስምምነት ፈጽሟል፡፡

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ የተገኙት አቶ አረጋ ካሳ (የአብክመ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ ም/ኃላፊ) እንደገለጹት፤ ጽ/ቤቱ በክልሉ የንጹሕ መጠጥ ውኃ፣ የሳኒቴሽን እና የውኃ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በፋይናንስ በመደገፍና ልማቱን በማፋጠን ረገድ ጉልህ አበርክቶ እያሳየ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ብድር ወስደው ውጤታማ የፕሮጀክት ማስፋፊያና የጥገና ስራዎችን የሚሰሩ የውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶች አቻ ተቋማት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተነሳሽነትን ይፈጥራሉም ብለዋል፡፡

ዛሬ ከጎንደር ከተማ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ጋር የተፈጸመው የብድር ውል ስምምነት ለታለመለት ዓላማ በዋል የነዋሪዎችን የመጠጥ ውኃ አቅርቦተት የሚያሻሽል ይሆናል ሲሉም አመላክተዋል ኃላፊው፡፡

የአብክመ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ በበኩላቸው በክልሉ የሚገኙ የከተማ መጠጥውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅቶችን አቅም ለማጠናከርና የአገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማሻሻል ሁነኛ የፋይናንስ ምንጭ ሆኖ እየሰራ ያለው የአማራ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት፤ ህጋዊ መስፈርቶችን አሟልተው ብድር ለሚጠይቁ አገልግሎት ድርጅቶች የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ቁልፍ የመፍትሔ አካል ሁኗል፡፡ ብለዋል

አያይዘውም ጽ/ቤቱ ለጎንደር ከተማ መጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ያበረከተው የ20 ሚሊዮን ብር የብድር ድጋፍ ለውኃ መሰረተ ልማት ግንባታዎችና ጥገናዎች አስፈላጊ የሆነውን የክሬን ማሽን ግዥ ለመፈጸም የሚያስችለው ሲሆን በርካታ የጉድጓድ የውኃ መገኛ ላላቸው ከተሞች በእጅጉ የሚያስፈልግና ጠቀሜታው ከፍ ያለ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የጎንደር ከተማ መጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ላቂያው አንዳርጌ በተገኘው ገንዘብ የክሬን ማሽን ገዝተው ለድርጅቱ አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች አነስተኛ የውኃ ተቋማት በትውስት እንደዚሁም በአነስተኛ ገቢ አገልግሎት እንዲሰጥ በማድረግ የድርጅቱን የገቢ አማራጭ የማሳደግ ስራ እንሰራለን ብለዋል፡፡

ብድሩን ቢቻል አስቀድመን አሊያ ደግሞ በወቅቱ ለመመለስ ፍጹም ዝግጁዎች ነን ያሉት ስራ አስኪያጁ፤ የአብክመ ውኃና ኢነርጂ ቢሮ እና የአማራ ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት የጎንደር ከተማን የውኃ አገልግሎት ለማሻሻያ ለሚደረገው ያልተቆጠበ ድጋፍና አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽሕፈት ቤት የሚሰጣቸው መሰል የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፎች የከተሞችን የውኃ ሽፋን ማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ጉልህ ሚናውን እየተጫወተ ይገኛሉ።

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት የከተሞችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተደራሽነት ለማሳደግ የሚያስችል የብድር አቅርቦት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ጽ/ቤቱ ከአገው ግምጃቤት ከተማ መጠጥ ውኃና...
14/08/2026

የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት የከተሞችን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተደራሽነት ለማሳደግ የሚያስችል የብድር አቅርቦት ስራውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

ጽ/ቤቱ ከአገው ግምጃቤት ከተማ መጠጥ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ጋር የ10 ሚሊየን ብር የብድር ውል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች አሟልተው ብድር ለሚጠይቁ የክልሉ ከተሞች የገንዘብ አቅርቦት እያመቻቸ የሚገኘው ጽ/ቤቱ፤ ለአገው ግምጃቤት ከተማ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት በመጪዎቹ ስምንት ዓመታት ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ የ10 ሚሊየን ብር ውል ስምምነት ፈጽሟል፡፡

የአገው ግምጃቤት ከተማ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ጌታሁን ገበየሁ እንደገለጹት ‹‹ከተማችን በቂ የውኃ ሀብት ክምችት ያለው ቢሆንም በኤሌክትሪክ መቆራረጥ ምክንያት የውኃ ተደራሽነቱን በሚጠበቀው ልክ ለማሳካት አዳጋች ሆኖብናል፡፡ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በዛሬው ዕለት ከአማራ ውኃ ልማት ፈንድ ድርጅት የተገኘው ብድር ለሶላር ፓኔል ግዥ አገልግሎት የሚውል ሆኖ፤ የከተማውን የመጠጥ ውኃ ተቋማት የኃይል አቅርቦት ከነዳጅ ወደ ፀኃይ ኃይል በመቀየር ማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውኃ ተደራሽ የምናሻሽልበት ይሆናል ብለዋል፡፡

የከተማው የመጠጥ ውኃ ሽፋን 53.8 በመቶ ላይ እንደሚገኘ የገለጹት ስራ አስኪያጁ፤ በቀጣይ ተቋማትን ከነዳጅና ኤሌክትሪክ ጥገኝነት በማላቀቅ ሶላራይዝ በማድረግ፤ ሽፋኑንም ወደ 100 ፐርሰንት ለማድረስ የምንሰራ ይሆናል ነው ያሉት፡፡

የከተሞች ብድር የመጠየቅና የውሃ ልማቱን የማፋጠን ፍላጎት ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ያሉት ደግሞ የአማራ ክልል ውኃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አደም ወርቁ ናቸው፡፡

አገልግሎት ድርጅቶች የሚጠበቅባቸዉን የፕሮጀክት ኢንቨስትመንት ወጭ እና የወሰዱትን ብድር በወቅቱና በተሟላ ሁኔታ የመመለስ ልምዳቸው እያደገ መምጣቱን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ ይህ መልካም ልምምድ የራሳቸውን ኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር፣ ፈንዱ ለሌሎች ተጨማሪ ከተሞች የፋይናንስ አቅርቦቱን ተዳራሽ እንዲያደርግ ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር አጠናክረው ሊቀጥሉበት እንደሚገባ አሳስበዋል። ከዚህ በተጨማሪም ከተሞች በብድር የሚወስዱትን ገንዘብ ለታለመለት አላማ ብቻ በማዋል ህብረተሰባቸዉን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባቸዉ አሳስበዋል።

በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ከ25 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ ዉኃ ተመርቶ ከ18 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚሆነዉ መሰራጨቱ ተገለፀ፡፡ባሕር ዳር፤ ነሴ 3/2018 ዓ/ም (ባሕ/ዉ/ፍ/አገ/ድ) ...
09/08/2026

በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ከ25 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ ዉኃ ተመርቶ ከ18 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚሆነዉ መሰራጨቱ ተገለፀ፡፡

ባሕር ዳር፤ ነሴ 3/2018 ዓ/ም (ባሕ/ዉ/ፍ/አገ/ድ) የባሕር ዳር ከተማ ዉኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የ2018 በጀት አመት የስራ ክንዉኑንና የ2019 በጀት አመት እቅዱን በገመገመበት ወቅት የድርጅቱ የእቅ/ዝግ/ዳ/ቤ/አስተ/ የስራ ሂደት መሪ አቶ ጥላየ አለነ እንዳስረዱት በ2018 በጀት አመት 30 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ ዉኃ ለማምረት ታቅዶ 25,403,137 ሜትር ኪዩብ ማምረት ተችሏል፡፡ በዚህም የዕቅዱን 84% ማሳካት ተችሏል ያሉት ስራ ሂደት መሪዉ ከተመረተዉ ከዚህ ዉኃ ዉስጥ 18,061,630 ሜትር ኪዩብ ዉኃ መሰራጨቱንና በዚህም የእቅዱን 80 በመቶ ማሳካት መቻሉን አብራርተዋል፡፡

የዉኃ አቅርቦት ሽፋንን በተመለከተም 82.5% መድረሱን አቶ ጥላየ ጠቅሰዉ ከ336 ሚሊየን በላይ ብር አመታዊ ገቢ መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል፡፡ በድርጅቱ አጠቃላይ ስራዎች አፈፃፀም ደግሞ 78.8 በመቶ መፈፀም ተችሏል ያሉት ስራ ሂደት መሪዉ በበጀት ዓመቱ በጥንካሬና በድክመት እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

ከአጋጠሙ ችግሮች መካከል በተለይ የመብራት፣ የነዳጅና የመገጣጠሚያ እቃዎች የዋጋ ንረት፣ የዉኃ ምርትና ስርጭቱን የሚያዉኩ ህገ ወጥ ተግባራት መበራከት፣ የዉኃ አቅርቦትና ፍላጎት አለመጣጣም፣ በቂ ገቢ ባለመሰብሰቡ ምክንያት የፋይናንስ እጥረት ከተከሰቱ ችግሮች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ ብለዋል፡፡

የድርጅቱ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅና የመጠ/ዉ/አቅ/ተቋ/ አስተ/ የስራ ሂደት መሪ አቶ ድረስ አስማረ በበኩላቸዉ የግምገማ መድረኩ አላማ በጥንካሬ የሰራናቸዉን ተግባራት ይበልጥ አጠናክረን አንድንቀጥልበትና በድክመት በቀረቡ ተግባራት ላይ ደግሞ በስፋት በመወያየት ችግሮቹን ቀርፈን በያዝነዉ በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ነዉ ብለዋል፡፡

አነስተኛ አፈፃፀም ላሳየንባቸዉ ተግባራት በተለይ ደግሞ ገቢ አሰባሰብ ላይ ለታየዉ መቀነስ ሁሉም ኃላፊነት ሊወስድ ይገባል ያሉት ምክትል ስራ አስኪያጁ በችግሮች ዉስጥ ሁነን በርካታ ተግባራትን ስንሰራ ቆይተናል ወደ ፊትም የመስራት አቅምና እድሉ ስላለን ችግሮቻችንን አስተካከለን ወደ ስራ እንግባ ሲሉ አሳስበዋል፡፡

ሌላዉ የድርጅቱ ምክትል ስራ አስኪያጅና የገ/ግ/ፋይ/ንብ/አስተ/ የስራ ሂደት መሪ አቶ በሪሁን አለሙ ደግሞ የድርጅቱ ሰራተኛና አመራር ባለፈዉ በጀት ዓመት በተለይ በቆጣሪ ንባብና ዉዝፍ አሰባሰብ ላይ በርካታ ስራዎችን ማከናወናቸዉን ጠቅሰዉ በያዝነዉ በጀት ዓመት ተቆራርጦ በመስራትና የአስተሳሰብና የአመለካከት ለዉጥ በማምጣት የተሻለ ዉጤት መሳመዘገብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

አሮጌ ቆጣሪዎችን መቀየር፣ ህገ ወጥ የዉኃ ስርቆትን ለማስቀረት የፍተሻ ስራዎችን መስራት፣ ቆጣሪ ንባብ ላይ በትኩረት መስራት፣ የድርጅቱን የገቢ አቅም ማሳደግና አዲሱን የአገልግሎት አስጣጥ መመሪያ ወደ ተግባር ማስገባት በዉይይቱ ወቅት በስፋት የተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ነበሩ፡፡

በግምገማ መድረኩ ሁሉም የማኔጅመንት አባላት ንዑስ የስራ ሂደት መሪዎች፣ ኬዝ ቲም አስተባባሪዎችና ጉዳዩ የሚመለከታቸዉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

Address

Bahir Dar
088

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Water Development Fund posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share