Saylem Woreda Communications

Saylem Woreda Communications saylem woreda communication

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ ባሉት ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምፃቸውን በነቅስ ወጥተው በይፋ መሰጠት ጀምረዋል ።‎‎
01/06/2026

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ ባሉት ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምፃቸውን በነቅስ ወጥተው በይፋ መሰጠት ጀምረዋል ።

ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ👉 የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር አለበት፣👉 የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣👉 አግባብ ባለው አካል ሲጠየ...
28/05/2026

ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ

👉 የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር አለበት፣

👉 የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣

👉 አግባብ ባለው አካል ሲጠየቅ መታወቂያውን ማሳየት አለበት፣

👉 የምርጫ ሕጉን ማክበር አለበት፣

👉 የምርጫውን ሂደት የመከታተል ተግባሩን ሲያከናውን መራጮች ማንን መምረጥ እንዳለባቸው አስተያየት ከመስጠት ወይም ተጽዕኖ ለማሳደር መሞከር የለበትም፣

👉 የምርጫ ቁሳቁሶችን መያዝ፥ ማንሳት፤ መነካካት ወይም በቁሳቁሶቹ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ተግባራትን መፈጸም የለበትም፣

👉 የምርጫ ጣቢያውን ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ከማስፈራራት ወይም ሥራውን ከሚያደናቅፉ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣

👉 ወደ ድምፅ መስጫ ክፍሎች መግባት የለበትም፣

👉 ቦርዱ የሚያወጣውን የሥነ ምግባር ደንብ መፈረም እና ማክበር ይገባዋል፡፡

ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 121

የቀደምት አባቶቻችን አብሮነትና የመቻቻል እሴቶች ይበልጥ እንድጠናከሩ የኃይማኖት አስተምህሮ ወሳኝ ነው፦ የሳይለም ወረዳ ም/ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል አየለ።‎ያዶታ ግንቦት 19/2018 ዓ...
27/05/2026

የቀደምት አባቶቻችን አብሮነትና የመቻቻል እሴቶች ይበልጥ እንድጠናከሩ የኃይማኖት አስተምህሮ ወሳኝ ነው፦ የሳይለም ወረዳ ም/ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል አየለ።
‎ያዶታ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም (የሳይ/ ወ/ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት)

‎በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ ለ1ሽህ 4መቶ 47ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ ) በዓል በተለያዩ ዓይማኖታዊ ሥነሥርዓትና ያለምንም ፀጥታ ችግር በድምቀት ተከብረዋል ውለዋል ።

‎የወረዳው ም/ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማኑኤል አየለ በዓሉ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክትህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ስያከብር ሃይማኖቱ በምያዘው መሠረት ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት መሆን እዳለበት አሳስበዋል።

‎አስተዳዳሪው አክሎም ወጣቶች የሠላም አምባሳደር እንደመሆናቸው መጠን ከጥላቻም ንግግር ፣ከአሉባልታና ከፋፋይ ፓለቲካ ራሳቸው በማራቅ እንደተለመደው ለሀገራቸው ሠላምና ዕድገት በጋራ መሥራት አለባቸው በማለት በጎ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

‎ለወረዳችን ልማትና ሰላም አስተዋጽኦ ለሚያደርጉት ለሃይማኖት አባቶች፣ ለፀጥታ ኃይሎች፣ ለወጣቶች፣ ለሴቶች ፣ለሚዲያ አካላት ፣ ለነጋዴዎችና ለመላው ማህበረሰብ በወረዳው ህዝብና መንግሥት ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አስተዳዳሪው አቀርባለሁ።

‎በመጨረሻ፣ ይህ የአረፋ በዓል ለአገራችን ሰላም፣ ለህዝባችን አንድነት፣
‎ለወጣቶቻችን ብሩህ ተስፋ፣
‎ለቤተሰቦቻችን ፍቅርና በረከት፣
‎ለተቸገሩ ወገኖች መጽናኛ፣
‎ለሁላችንም ጤናና ደስታ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

‎የሳይለም ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕረዚዳንት ሸክ ጣሀ ኢብራህም በበኩላቸው
‎በበዓሉ ወቅት ለአላህ ያለንን ታማኝነትና ፍቅር ለመግለጽና መስዋዕትነትን በሃይማኖቱ አስተምህሮ መሠረት ለመፈጸም የተለመደውን የመረዳዳት፣ የመጠያየቅ እንድሁም አቅመ ደካሞችን የማገዝ እና የመዘየር መልካም ተግባራትን አጠናክሮ በማስቀጠል ኃይማኖታዊ ግዴታችንን መወጣት አለብን ስሉ አሳስበዋል ።
‎በዕለቱ የሰላት እና የዱአ ኘሮግራም በኡስታስ ሃጂ አብዱልከሪም ጅብርል የተካሄደ ስሆን ከሰላት መልስ ለአቅመ ደካሞችና ለድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የአብሮነትና የመረዳዳት መገለጫ የሆነው የዕርድ ሥነሥርዓት ተካሂደዋል ።

‎ለወቅታዊ፤ ትኩስና የተሟላ
‎ፌስቡክ፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100079727967214
‎ቴሌግራም፡-
https://t.me/saylemworedagovernment


‎ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍተሐዊና ስኬተማ የፔብልክ ሰርቫንት አባላት ሚና ወሳኝ  መሆኑን የሳይለም ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ገለጸ።‎‎ያዶታ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም ...
27/05/2026

‎ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍተሐዊና ስኬተማ የፔብልክ ሰርቫንት አባላት ሚና ወሳኝ መሆኑን የሳይለም ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ገለጸ።

‎ያዶታ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም (የሳይ/ ወ/ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት)

‎ጽ/ቤቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ከአጠቃላይ የፔብሊክ ሰርቫን አባላት ጋር ምክክር አደርገዋል ።

‎የሳይለም ወረዳ የመንግሥት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ግርማ ሽፈራው በዕለቱ እንደገለጹት ፓርቲው በምርጫ ተወዳድሮ ማሸነፍ ብቻ
‎ ሳይሆን ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሀዊ ሆኖ እንድጠናቀቅና ለምሳሌነት እንድጠቀስ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል ።

‎አቶ ግርማ አክሎም ቀድም ስል የሰራቸውን ተዓምራዊ ተግባራትን በማስከተል ለህዝብ የሚጠቅም አጀንዳዎች
‎በጽኑ ለማረጋገጥ የሚተጋና የሃሳብ የበላይነት የሚያምን ስለሆነ ፓርቲውን ለማሻገርና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመገንባት የሁሉም አባላት እገዛ ያስፈልጋል ብለዋል ።

‎በአጠቃላይ ከሁሉም ማህበራዊ መሠረቶች የቀረቡ የቀጣይ ተግባራቶችን ጥያቄ በግብዓትነት ተቀብሎ እንደየቅደም ተከተላቸው ለማስፈጸም ፓርቲው ቁርጠኛ መሆኑን አቶ ግርማ አስገንዝበዋል ።

‎የሳ/ወ/አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ አካሉ ቆጭቶ በበኩላቸው ሰባተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ እንድሁም ፍትሀዊ እና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች የምርጫ ስነምግባሮችን በመከተል የመጠበቅና ማስጠበቅ ኃላፍነታቸውን በተገቢው እንድወጡ ጠይቀዋል ።

‎ታሪክን እያደስን የለማችንና የበለጸገች ሀገርን ለመገንባት የምጠበቅባቸውን ኃላፍነትና ተግባር ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ከአባላቹ መካከል አንዳንዶቹ ተናግረዋል።

‎ የነበሩት የልማት ክፍተቶችን ከምርጫ ጋራ ማገናኘት ተገቢነት የሌላቸው መሆኑን የገለጹት አባላቶቹ በቀጣይ የብልጽግና ፓርቲ ለጥያቄዎቻቸው ተገቢውን ምላሽ እንደሚጠብቁ ስለመሆናቸው አንስተዋል ።

‎ለወቅታዊ፤ትኩስና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፦
‎ፌስቡክ፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100079727967214
‎ቴሌግራም፡-
https://t.me/saylemworedagovernment

ለ1ሽህ 4መቶ 47ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ ) በዓል አስመለክቶ የሳይለም ወረዳ  ም/ዋና  አስተዳዳሪ አቶ አማኑል አየለ ለመላው እስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አ...
26/05/2026

ለ1ሽህ 4መቶ 47ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ ) በዓል አስመለክቶ የሳይለም ወረዳ ም/ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማኑል አየለ ለመላው እስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

‎ያዶታ ግንቦት 18/2018ዓ.ም (የሳይለም ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት)

‎በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚከበሩት የአደባባይ በዓላት መካከል አንዱ የኢድ አል አደሃ (አረፋ ) በዓል ስሆን ህዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ስያከብር ካሁን በፊት የነበረውን የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህልን ይበልጥ በማጠናከር በዓሉን ማክበር አለበት ብለዋል ።

‎ በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ የሚከበረው ይህ በዓል
‎ነቢዩ ኢብራህም ለፈጣሪያቸው ያሳዩት ፍጹም ታዛዥነት እና መስዋእትነት በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ የሚታወስ ታላቅ ቀን እደሆነ ም/ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል ።

‎በዓሉ በሰዎች መካከል ያለውን ፍቅርና አንድነትን ከማጎልበት በተጨማሪ የተቸገሩት የሚረዱበት እንድሁም ተራርቀው የነበሩት ዘመድ አዝማድና ጎረበት የሚጠየቁበት የትስስር ማጠናከሪያ በዓል መሆኑን አቶ አማኑኤል አንስተዋል ።

‎አቶ አማኑኤል በመልዕክታቸው ሁሉም የሙስልሙ ማህበረሰብ የአባቶቻችን የወረስነውን የይቅርታና የመረዳዳት እሴቶችን አጠናክሮ ለመጭው ትውልድ ማስረከብ ከሁላችን ይጠበቃል ስሉ አሳስበዋል ደ

‎በመጨረሻም ም/ዋና አስተዳዳሪው ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1ሽህ 4መቶ 47ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ) በዓል የሠላም ፣የፍቅር ፣የጤና፣የደስታ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በወረዳው ህዝብና መንግስት ስም ገልጸዋል ።

‎ ኢድ ሙባረክ ብለዋል።

‎ ለወቅታዊ፤ ትኩስና የተሟላ
‎ፌስቡክ፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100079727967214
‎ቴሌግራም፡-
https://t.me/saylemworedagovernment



25/05/2026
25/05/2026

የብልጽግና ፓርቲ ደማቅ የድጋፍ ሰልፍ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ እንደሚካሄድ ተገለጸ::
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ምክንያት በማድረግ የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ ግንቦት 18/2018 ዓ/ም በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ የሚካሄድ መሆኑን የካፋ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አስታውቋል።

የካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ ኃይሌ 7ኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ግንቦት 18/2018 ዓ/ም በቦንጋ ከተማ በሚደረገው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል ።

የብልጽግና ፓርቲ የከተማና ገጠሩን ገጽታ በመቀየር ለነዋሪዎች ምቹ እንዲሆን ከማስቻል ባለፈ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪን ተፈላጊነት ከማሳደግ ረገድ አመረቂ ውጤት አስመዝግቧል ብለዋል ።

የብልጽግና ፓርቲ አዳዲስ ኢንሼቲቮችን ፈጥሮ በመተግበር እና በርካታ የልማት ሥራዎችን በመስራት ውጤታማ የሆነ ፓርቲ መሆኑን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊው አመላክተዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ከፋፋይ አጀንዳዎችን አስወግዶ ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክርና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት መዘርጋት ላይ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑንም ኃላፊ ጠቁመዋል ።

በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው የለውጡ መንግስት ለብዘኃ- ኢኮኖሚ ትኩረት በመስጠት እምቅ የሆኑ የተፈጥሮ ሀብቶቻችንን ወደ ፀጋ በመቀየር ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስቻለ ድንቅ ፓርቲ ነውም ብለዋል ።

ፓርቲው የጀመራቸውን የዳበረ ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የልማት ቀጣይነት እና ዘላቂ ሰላም የማስፈን አጀንዳዎችን በሁሉም መስኮች አጠናክሮ ያስቀጥላልም ብለዋል።

ፓርቲያችን ጀምሮ የመጨረስ ብሎም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ቃል በተግባር የሚፈጽም ፓርቲ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል የሚለውን አስምሯል ።

ምርጫው ነፃ ፍፁም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ብልጽግና ፓርቲ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል ።

‎የብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ለህዝቡ ቃል በገባው መሰረት የልማት ስራዎችን በመስራት የህዝብ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ በፖለቲካው በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የወሰዳቸው ታርካዊ እርምጃዎች የላቀ ውጤት እያመጡ መሆናቸውን የመንግስት ዋና ተጠሪው ገልጸዋል ።

በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ ልዩ የድጋፍ ሰልፍ እና የምረጡኝ ቅስቀሳ ግንቦት 18/2018 በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ እንደሚደረግ የገለጹት አቶ አጥናፉ በዚህም የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን፣ የከተማ አስተዳደርና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ አባላትና ድጋፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ወጣቶችና ሴቶች እንዲሁም የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት እንደሚሳተፉ ገልጸዋል ።
በመጨረሻም ጥሪ የተደረገላቸው አካላት በተባለው ቀንና ሰዓት በቦንጋ ከተማ በመገኘት ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍ እንዲገልፁ አቶ አጥናፉ ጥሪ አስተላልፈዋል::

በመሸሻ መኩሪያ
ምስል በሠለሞን ተስፋዬ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፦

👇ፌስቡክ ገፃችንን
https://www.facebook.com/kfzgca
👇የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/ahkafaZGCAffairs
👇ኢንስታግራም ቻናላችን
https://www.facebook.com/share/p/1Dx8QSTzTK
👇ዩቲዩብ ቻናላችየሐነንን

👇የቲክቶኮ ቻናላችን
https://vm.tiktok.com/ZMrxuoNNLp/

በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ የክልል ጸጥታ ም/ቢሮ ሃላፍ አቶ ሀብታሙ አለሙ፣ የዞኑ ፐብሊክ ሰርቭስ እና የሰው ሀብት ቢሮ ሃላፊ አቶ ነፃነት ብርሃኑ እና የሳ/ወ/ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ሀላፍ  አቶ ግ...
25/05/2026

በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ የክልል ጸጥታ ም/ቢሮ ሃላፍ አቶ ሀብታሙ አለሙ፣ የዞኑ ፐብሊክ ሰርቭስ እና የሰው ሀብት ቢሮ ሃላፊ አቶ ነፃነት ብርሃኑ እና የሳ/ወ/ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ሀላፍ አቶ ግርማ ሽፈራው መሪነት በወቅታዊ ጉዳዮች እና የቀጣይ ስራ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሂዷል ።

የክልል ወጥታ ም/ቢሮ ሃላፍ አቶ ሀብታሙ አለሙ በበኩላቸው ከ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አኳያ ምርጫው በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሰረት ዜጎች ተወካዮቻቸውን በነፃነት በመምረጥ የሀገርን አስተዳደር እንዲወስኑ የሚያደርግ በመሆኑ ተጠያቂነትን እንዲያሰፍኑ እና ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲያረጋግጡ የሚያስችል ቁልፍ ሂደት ስለሆነ ምናችንን ልንወጣ ይገባልም ሲሉ አሳስበዋል።

መድረኩን በጋራ የመሩት የካፋ ዞን የዞኑ ፐብሊክ ሰርቭስ እና የሰው ሀብት ቢሮ ሃላፊ አቶ ነፃነት ብርሃኑ በበኩላቸው ለህዝባችን ሁለንተናዊ ልማትና እድገት ቅድሚያ በመስጠት የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠል የሚስተዋሉ ውስንነቶችን እየለዩ በሀላፊነት መስራት ይገባል ብለዋል።

አክለውም የለውጡ መንግስት ውስጣዊ እና ውጫዊ ፈተናዎችና ተግዳሮቶችን በፅናት በማለፍ ለህዝቡ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት በብስለት በመምራት በብቃት መወጣት መቻሉንም ነው የገለፁት።

የሳ/ወ/ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ሀላፍ አቶ ግርማ ሽፈራው በበኩላቸው ተመሳሳይ ዓላማ አንግበን ለህዝባችን ጥቅም በጋራ መስራት የሁላችን ሃላፊነት በመሆኑ ተቀራርበን ልንሰራ ይገባል በብልፅግና እሳቤ ፈተናዎችን እንደ እድል እየተጠቀምን አደረጃጀቶቻችን እያሰፋንና ማህበረሰባችንን እያሳተፍን የሚታይ ለውጥ በማምጣት ህዝባችን የሚመሰክረው ስራ በመስራት ወረዳችንን አልፎ ዞናችንን የሚመጥን ስራ እየሰራን እንገኛለን ይህንንም እናስቀጥላለን ብለዋል።

በመድረኩ ሀገራዊ ፤ክልላዊ ፤ዞናዊ እና ወረዳዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት በተለያዩ የማሀበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉን!👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100079727967214
ቴሌግራም፡-
https://t.me/saylemworedagovernment

ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ  ይበልጥ ተደራሽ እና ሕዝባዊ ለማድረግ የወጣቶችን  አደረጃጀት ያሳተፈ የ"ቡና ጠጡ" መርሀግብር በሳይለም /ወ/ዋና ከተማ ያዶታ በድምቀት ተካሂደዋል ።‎‎ያዶታ...
25/05/2026

ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ይበልጥ ተደራሽ እና ሕዝባዊ ለማድረግ የወጣቶችን አደረጃጀት ያሳተፈ የ"ቡና ጠጡ" መርሀግብር በሳይለም /ወ/ዋና ከተማ ያዶታ በድምቀት ተካሂደዋል ።

‎ያዶታ፣ ግንቦት 16/2018 ዓ.ም የሳ/ወ/መን/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

‎በመርሀግብሩ ለይ የተገኙት የደ/ምዕ/ኢት/ህ/ክል/መን/ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል የቢሮ ኃላፍ አቶ ሀብታሙ ዓለሙ ባስተላለፉት መልዕክት ግንቦት 24/2018 ዓም ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍጹም ሠላማዊ ፣ተዓማኒና ፍተሐዊ በሆነ መንገድ እንድጠናቀቅ በተለይ የወረዳ ህዝብ የራሱን ተወካይ የሚመርጥበት ዕለት ስለሆነ ዕድሉን ተጠቅመው አጋርነቸውን በግልጽ ባሳየነው ልክ ድምፃቸውን በትክክል መስጠት አለባቸው ብለዋል ።
‎አቶ ሀብታሙ አክሎም የወረዳ ወጣቶችና አጠቃላይ ማህበረሰቡ እያሳዩት ያለው ንቁ ተሳትፎና አጋርነት በህዝብና በፓርቲ መካከል ያለውን ጥብቅ ቁርኝነትና ጠንካራ ውህደትን በግላጭ አሳይተዋል ብለዋል ።

‎ የካፋ ዞን ፔብ/ሰር/የሰው/ሀ/ል/መምሪያ ኃላፍና የወረዳ ደጋፍ አቶ ነፃነት ብርሃኑ በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ ለህዝብ ተጠቃሚነት ሌት ከቀን የሚተጋ ፓርቲ መሆኑን ገልጸው ማህበረሰቡ ለሚጠይቁት ጥያቄ ተገቢው ምላሽ እንድያገኝ ዘንድ ለምርጫው ስኬታማነት ሁሉም የራሱን አሻራ ማስቀመጥ አለበት ስሉ አስገንዝበዋል ።

‎ቀጥሎም አቶ ነፃነት የምርጫ ቅስቀሳ ንቅናቄ የፓርቲውን ሰፊ የሕዝብ መሠረትና አጋርነት ይበልጥ ከማጠናከር ባሻገር የማህበረሰቡን ትስስርና አብሮነትን ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው ብለዋል።

‎የሳ/ ወ/ም/ዋና አስተዳደሪ አቶ አማኑኤል አየለ በበኩላቸው በየደረጃው ያለው የአበላቶች ቁርጠኝነት ለፓርቲው ስኬት ቁልፍ ሚና የሚጫወት መሆኑን በመግለጽ የብልፅግና ፓርቲ በ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍጹም አሸናፊ እንድሆን በሚያደርገው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ እንደሆ አንስተዋል ።

‎በዚሁ መሠረት በወረዳው ስር በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች መርሀ ግብሩ አየተከናወነ መቆየቱን የገለጹት አቶ አማኑል ሥነ-ሥርዓቱን ደማቅና ስኬታማ የምርጫ ቅስቀሳ መድረክ እንደሆነ አመላክተዋል ።

‎ የሳ/ወ/የመንግሥት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ኃላፍ እንደገለጹት አቶ ግርማ ሽፈራው ይህንን ሕዝባዊ ንቅናቄ አጠናክሮ በማስቀጠል መላው የወረዳው ነዋሪ በምርጫው ዕለት የፓርቲው ምልክት በሆነው "ስንዴ ነዶ" ላይ ለብልጽግና ፓርቲ ድምጹን በመስጠት የጀመረውን የብልፅግናና የልማት ጉዞ እንዲያስቀጥልም ጥሪ አቅርቧል።

‎በወረዳው በሁሉም ቀበሌዎች በተለይም ወጣቶችን ጨምሮ ማህበረሰቡ በየማህበራዊ መሠረቱ እያሳየ ያለው ቁርጠኝነትና ንቁ ተሳትፎ ፓርቲው በምርጫው አስተማማኝ ድል እንዲቀዳጅ ማረጋገጥ የሚችልበት ኩነቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን አቶ ግርማ ተናግረዋል ።
‎የሳ/ወ/ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ እንዳየሁ ገዝኻኝ በመድረኩ እንደገለጹት የቡና ጠጡ" ቅስቀሳ ስትራቴጂ ዋነኛ ዓለማ ፓርቲው የሰራቻቸውንና የልማት ተግባራትንና በቀጣይ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋጥ የሚችሉ የሰላምና የልማት አማራጮችን ለአባላትና ለደጋፊዎች በቀላሉና በቅርበት ለማስረጽ ያለመ መሆኑን አስገንዝበዋል ።

‎​በብልፅግና ፓርቲ የተጀመሩ የልማት ጉዞዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያላቸውን ፍላጎትና ጽኑ እምነት የገለጹት ወጣቶቹ ድምፃቸውን ለተግባራዊ ለውጥና ለፓርቲያቸው ድል ማረጋገጫ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ።

‎ለወቅታዊ፤ ትኩስና የተሟላ ፌስቡክ፦
https://www.facebook.com/profi

24/05/2026

ጋዜጠኛ ፍቅሩ በላይ በስራ ባልደረቦቹ አንደበት

Address

Kafa Zone Saylem Woreda
Bonga

Telephone

+251910095551

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Saylem Woreda Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share