Southwest Communications

ሕዝቡ ሕጋዊ ካልሆኑ ከማንኛውም ምንጮች ከሚወጡ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች በትላንትናው ዕለት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በከፍ...
02/06/2026

ሕዝቡ ሕጋዊ ካልሆኑ ከማንኛውም ምንጮች ከሚወጡ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች በትላንትናው ዕለት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በከፍተኛ ንቃት እና ትዕግሥት ድምፃቸውን ስለሰጡ አመስግኗል።

በምርጫ ሕጉ መሠረት ውጤት በቦርዱ ይፋ እስከሚሆን ድረስም በትዕግሥት እንዲጠብቁ እና ሌሎች አካላትም ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲቆጠቡ፤ ሕዝቡም ከመሰል መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ቦርዱ አሳስቧል።

ሰላማዊና ፍትሐዊ የሆነ ምርጫ ባደረግን ማግስት ወደ ስራ ተሰማርተናል፦ የቴፒ ከተማ ነዋሪዎች 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን ሰላማዊ በሆነ መልኩ አከናውነን ወደ ስራ ተሰማርተናል ሲሉ በደቡብ...
02/06/2026

ሰላማዊና ፍትሐዊ የሆነ ምርጫ ባደረግን ማግስት ወደ ስራ ተሰማርተናል፦ የቴፒ ከተማ ነዋሪዎች

7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን ሰላማዊ በሆነ መልኩ አከናውነን ወደ ስራ ተሰማርተናል ሲሉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን የቴፒ ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ እንደገለፁት ዘንድሮ የተካሄደው ምርጫ በተሻለ ሂደት መከናወኑን ገልፀው ምንም ዓይነት ተፅዕኖ ያልታየበት፣ በሰላማዊና በፍትሐዊ መንገድ ድምፃቸውን መስጠታቸውንና አሁን ላይ ደግሞ ወደ መደበኛ ሥራቸው መሰማራታቸውን ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ የዴሞክራሲ መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ ከማከናወናቸውንና ዛሬ ላይ የቴፒ ከተማ በተረጋጋና በተለመደው የንግድና የማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ እንደምትገኝ ተናግረዋል ሲል ማሻ ኤፍ ኤም ዘግቧል።

02/06/2026
“የምርጫው በሠላም መጠናቀቅ የኢትዮጵያ አሸናፊነት ነው” - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምርጫ የተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ምርጫው በሠላም ...
02/06/2026

“የምርጫው በሠላም መጠናቀቅ የኢትዮጵያ አሸናፊነት ነው” - ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምርጫ የተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ምርጫው በሠላም የተከናወነበት መንገድ ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ መሆኑን ተናገሩ።

የካፋ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢና የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የክልሉ ሊቀመንበር አቶ ናትናኤል በድሩ የምርጫው ሂደት ላይ ክትትል ሲደረግ እንደነበር ተናግረዋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ውጤቱን በፀጋ ለመቀበል መዘጋጀታቸውንና ለሀገር ያለውን ፋይዳ በአግባቡ መረዳታቸውን ጠቁመዋል።

7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዴሞክራሲዊ ስርዓት የተስተዋለበትና በተምሳሌትነት የሚጠቀስ መሆኑንና ለትውልድ እንደሚጠቅም አንስተዋል።

ለሀገረ-መንግስት ግንባታ ወሳኝ የሆነው ምርጫ በፍትሃዊ መንገድ መከናወኑን ገልጸው ፤ ኢትዮጵያውያን በነፃነት መምረጣቸው ለዚህ መልካም የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት አስተዋፅኦው ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት።

የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚና የብሔራዊ አንድነት ፓርቲ የክልሉ ስራ አስፈፃሚ መቅደስ መኮንን ህዝቡ በሠላማዊ መንገድ ይበጀኛል የሚለውን መምረጡን በሰጡን አስተያየት ተናግረዋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች አሁን ላይ ከተገኘው ልምድ በመማር ለሚቀጥሉት ምርጫዎች መዘጋጀት ያስፈልጋል ሲሉ አሳስበዋል።

ዜጎች የዴሞክራሲ ባህልን ያዳበሩበት ምርጫ መሆኑን ተናግረው ፤ በነፃነት ድምፅ የተሰጠበት ነው ብለዋል።

የሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ፓርቲ አባል አቶ ክፍሌ መሸሻ በፓርቲም ይሁን በግለሰብ ደረጃ ውጤቱን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውንና ለሠላም ቅድሚያ እንደሚሰጡ ጠቁመዋል።

የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታው በምርጫ አማካኝነት እየተጠናከረ እንደሚቀጥልና ለኢትዮጵያ ጠቃሚ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ውድድርን ተከትሎ የሚመጣውን ውጤት ለማክበርና ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ምርጫው ሠላማዊ፣ ነፃ እና ፍትሃዊ ሆኖ መኬሄዱ ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ ነው ብለዋል ሲል ቦንጋ ኤፍ ኤም ዘግቧል።

ከሰላማዊና ነፃ የምርጫ ማግስት ወደ መደበኛ ተግባራችን ተመልሰናል — የታርጫ ከተማ ነዋሪዎችበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ...
02/06/2026

ከሰላማዊና ነፃ የምርጫ ማግስት ወደ መደበኛ ተግባራችን ተመልሰናል — የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሙሉ በሙሉ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ማጠናቀቃቸውን ገለጹ።

ነዋሪዎቹ ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ በማግስቱ ያለምንም የፀጥታ ስጋት ወደ መደበኛ የዕለት ተዕለት የሥራ እንቅስቃሴያቸው መመለሳቸውን አስታውቀዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎች ለደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ (SWMN) በሰጡት አስተያየት፤ ዘንድሮ የተካሄደው ምርጫ ከዚህ ቀደም ከነበሩት ምርጫዎች እጅግ በተሻለ የዝግጅት ደረጃና ፍጹም ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ የተከናወነ መሆኑን መስክረዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡት የከተማዋ ነዋሪ አቶ ጌትነት ገበየሁ፤ ምርጫው ምንም ዓይነት ተፅዕኖ ያልታየበት፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ መሆኑን ጠቁመው፣ ምንም ዓይነት አስገዳጅ ወይም አስፈሪ ነገር ሳይገጥማቸው ድምፃቸውን መስጠታቸውንና አሁን ላይ ደግሞ ወደ መደበኛ ሥራቸው መግባታቸውን ተናግረዋል።

ሌላው የታርጫ ከተማ ነዋሪ አቶ ወንድማገኝ ኢተላ በበኩላቸው፤ ምርጫው በጥሩ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልጸው፣ "በነፃነት የሚበጀንን ፓርቲ መርጠናል" ብለዋል።

ሕዝቡ በከፍተኛ መነሳሳት እስከ ምሽቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን ሲሰጥ እንደነበርም አስታውሰዋል።

የምርጫውን የተሻለ የቅድመ-ዝግጅት ሥራ ያደነቁት አቶ ኢያሱ እሸቱ በበኩላቸው፤ ሕዝቡ በከፍተኛ ጉጉት የመረጠበት ዕለት እንደነበር ገልጸዋል።

"ከጠዋቱ 11:30 ጀምሮ ረጅም ሰልፍ ነበረ፤ የኢፌዴሪ ምርጫ ቦርድ መራጩ ሰልፍ ላይ መሆኑን አውቆ ሰዓት ማራዘሙን በመጠበቅ ሕዝቡ መብቱን ተጠቅሟል" ብለዋል።

አክለውም ሂደቱ ከዚህ ቀደም ከነበሩት ጊዜያት እጅግ የተሻለና ሰዎች በነፃነት የመረጡበት መሆኑን ገልጸው፣ በአሁኑ ወቅት የምርጫውን ውጤት በጉጉት እየጠበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

የምርጫውን ፍጹም ሰላማዊነት አስመልክቶ ኮማንደር ደስታ መገላ በሰጡት አስተያየት፤ "ዕድላችንንና የዴሞክራሲ መብታችንን በመጠቀም ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ምንም ዓይነት ኮሽታ ሳይኖር ምርጫ አካሂደናል" ብለዋል።

ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ የነበረው ሂደት እጅግ አስደሳችና የታለመለት የዴሞክራሲ ግብ ያሳካ መሆኑንም አብራርተዋል።

የአካባቢው ወጣቶችም በምርጫው ሂደት ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን፣ ወጣት አማኑኤል ደምሴ ምርጫውን በሰላም ማጠናቀቃቸውን አረጋግጧል።

ከምርጫው ማግስት ቀጥታ ወደ መደበኛ ሥራው መመለሱን የገለጸው ወጣት አማኑኤል፤ "እኛ የምንፈልገው ልማትና ሰላም ብቻ ነው" በማለት የወጣቱን የልማት ጉጉት አንስቷል።

በአጠቃላይ በታርጫ ከተማና በዙሪያዋ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች የዴሞክራሲ መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ ከተገበሩ በኋላ፣ ዛሬ ከተማዋ በተረጋጋና በተለመደው የንግድና የማኅበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ እንደምትገኝ ለመታዘብ ተችሏል ሲል የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠበት ነውሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነትና...
02/06/2026

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠበት ነው

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጩ ሕዝብ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነትና ፍላጎት በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑን የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለጸ።

ምክር ቤቱ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት መጠናቀቁን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል።

የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ማሩ ጃኔ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ምርጫው ግልጽነት እና ፍትሐዊነት ከመላበሱም ባሻገር በመራጩ የከተማዋ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን በተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ቅቡልነት ያሳየ ነው።

ምክር ቤቱ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጋር በመቀናጀት ለምርጫው ስኬታማነት መሥራቱን አስታውሰው፤ ይህም ምርጫው ዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አብራርተዋል።

የምርጫ ሂደቱም እጅግ የተረጋጋ፣የሰለጠነ እና የዴምክራሲ ሥርዓት ትግበራ ሂደትን ያጠናከረ ሆኖ ማለፉንም ጠቅሰዋል።

መገናኛ ብዙሃንም ለፓርቲዎች የሰጡት የአየር ሰዓት ፍትሐዊ፣ ግልጽና ለሁሉም ፓርቲዎች እኩል የመወዳደሪያ ሜዳ የሰጠ ነው ያሉት አቶ ማሩ፤ ይህም እያንዳንዱ የፖለቲካ ፓርቲ ያሉትን የፖሊሲ አማራጭ ሀሳቦች ያለምንም ገደብና ጫና ለሕዝቡ የሚያቀርብበት ዕድል መፍጠሩን አስረድተዋል።

የጸጥታ አካላትም ያለምንም ወገኝተኝነት ፍጹም ገለልተኛ በሆነና ሙያዊ አካሄዶችን በተከተለ መንገድ የአዲስ አበባ ምርጫ ጣቢያዎችንና የመራጩን ሕዝብ ደህንነት ሲጠብቁ መዋላቸውን ያስታወሱት ሰብሳቢው፤ የጸጥታ አካላት ያከናወኑት ተግባር ሊመሰገን የሚገባው ነው ብለዋል።

የድምጽ ቆጠራውና ውጤቱን የማደራጀት ሥራ የሚያከናወነው በሕጉ መሰረት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በመሆኑም ውጤቱ በከተማ ደረጃ በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገለጽ ድረስ በትዕግስት እንዲጠበቅ ምክር ቤቱ ጥሪውን ያቀርባል ነው ያሉት።

ማንኛውም ወገን የምርጫ ውጤቱን በጸጋ የመቀበል ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታ እንዳለበት አመልክተው፤ ቅሬታዎች ቢኖሩ እንኳን በሕጋዊ እና በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዘሪሁን ኮርሜ በበኩላቸው፤ በምርጫው አረጋዊያን፣ ሴቶች፣ ወጣቶችና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ያሳዩት ተሳትፎ እና ቁርጠኝነት ተምሳሌታዊ መሆኑን ተናግረዋል።

ለምርጫው ስኬት አስተዋጽኦ ላደረገው መራጩ ሕዝብ፣ ለምርጫ ቦርድ፣ የከተማዋ የጸጥታ አካላት ጨምሮ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በምክር ቤቱ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የምርጫ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን የሕዝብ ድምጽ ልናከበር ይገባል ያሉት ምክትል ሰብሳቢው፤ የሰለጠነና ብስለት የተሞላበት የፖለቲካ አካሄድም ይሄው መንገድ ነው ብለዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።



በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/
📌በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
📌በሊንክደን
https://www.linkedin.com/company/southwest-communications/
📌በትሬድስ
https://www.threads.com/
📌በብሉ ስካይ
https://bsky.app/profile/swc79..bsky.social
በደብልው ኤን ሶሻል
https://wnsocial.com/page/16775

ኢትዮጵያ መርጣለች! #ኢትዮጵያመርጣለች
02/06/2026

ኢትዮጵያ መርጣለች!
#ኢትዮጵያመርጣለች

02/06/2026
“ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ተደስተናል” - የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሠላማዊ መንገድ በመካሄዱ መደሰታቸውን የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ። አቶ ዮሴፍ ስለሺ፣ አቶ ታየ ...
02/06/2026

“ምርጫው በሠላም በመጠናቀቁ ተደስተናል” - የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች

7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ በሠላማዊ መንገድ በመካሄዱ መደሰታቸውን የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።

አቶ ዮሴፍ ስለሺ፣ አቶ ታየ ገብረማርያም፣
ወ/ሮ ምህረት ይስሃቅ እና አቶ ምስክር ዘለቀ
በሰጡት አስተያየት ምርጫው በሠላማዊ መንገድ መከናወኑን ተናግረዋል።

ያለምንም ችግር በመከናወኑ ደስታቸውን ለጣቢያችን በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል።

በምርጫ ቦርድ የሰዓት ጭማሪ ምክንያት እስከ እኩለ ለሊት ድረስ ሥርዓት ባለው መንገድ መምረጣቸውን አስታውቀዋል።

የምርጫ ቦርድ ሰራተኞች፣ የፀጥታ አካላት፣ የምርጫ ታዛቢዎችና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል ነው ያሉት።

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ለአቅመ-ደካሞችና ለአካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ተሰጥቶ መከናወኑን ጠቁመዋል።

በቦንጋ ከተማ አስተዳደር በአብዛኞቹ ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ ቆጠራ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ተመራጮችና መራጩ ህዝብ የምርጫው ጊዜያዊ ውጤት ይፋ እስኪሆን በትዕግስት መጠባበቅና ሲገለፅም በፀጋ መቀበል እንዳለባቸው አስተያየት ሰጠትዋል ሲል ቦንጋ ኤፍ ኤም ዘግቧል።

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የተሰጠ  የምስጋና መግለጫትናንት በመላው ሀገራችን የተካሄደውና እጅግ ወሳኝ የሆነው ጠቅላላ ምርጫ በክልላችን በስኬት ተጠናቋል። የክልላችን ...
02/06/2026

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የተሰጠ የምስጋና መግለጫ

ትናንት በመላው ሀገራችን የተካሄደውና እጅግ ወሳኝ የሆነው ጠቅላላ ምርጫ በክልላችን በስኬት ተጠናቋል። የክልላችን ህዝብ ከጠዋቱ ጀምሮ በነቂስ በመውጣት፣ ዲሞክራሲያዊ መብቱን በመጠቀምና የነገ እጣ ፈንታውን በራሱ እጅ ለመወሰን ያሳየው ከፍተኛ ተነሳሽነትና ብስለት ታሪካዊና አርአያነት ያለው ነው።

በክልላችን በሚገኙ 1,780 የምርጫ ጣቢያዎች ሁሉ ምርጫው ሙሉ በሙሉ ሰላማዊ፣ ነጻና ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ ታላቅ ሚና ለተጫወቱት፡ለተከበረውና ሰላም ወዳዱ የክልላችን ህዝብ ለዳበረው የዲሞክራሲ ባህሉ እና ለነቃ ተሳትፎው፣ለተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላሳዩት ሰላማዊና ህጋዊ የፉክክር መንፈስ፣የምርጫ አስፈጻሚዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካለት ላሳያችሁት ቁርጠኝነትና የስራ ተነሳሽነት ፣በየደረጃው ለሚገኙ የጸጥታ አካላት ሌሊት ከቀን በመትጋት አስተማማኝ ሰላም በመፍጠራቸው፣ክልላችን መንግስት ያለውን ላቅ ያለ ክብርና ልባዊ ምስጋና ያቀርባል።

ይህበሰላም የተጠናቀቀው ምርጫ የሀገራችንና የክልላችንን አንድነት፣ ልማትና ዲሞክራሲያዊ ጉዞ ይበልጥ የሚያጠናክር ትልቅ ድል ነው

Address

Bonga

Telephone

+251913241234

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Southwest Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Southwest Communications:

Share