Southwest Communications

እንደ ቶኪ ቤዓ ያሉ ባህላዊ ዕሴቶቻችን የአብሮነታችን መሰናሰኛ ከመሆን ባሻገር ለዘላቂ ሰላምና ልማት ጽኑ መሠረት ናቸው ፦ አቶ ፍቅሬ አማን​በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የብልጽግና...
04/09/2026

እንደ ቶኪ ቤዓ ያሉ ባህላዊ ዕሴቶቻችን የአብሮነታችን መሰናሰኛ ከመሆን ባሻገር ለዘላቂ ሰላምና ልማት ጽኑ መሠረት ናቸው ፦ አቶ ፍቅሬ አማን

​በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፣ ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ "ቶኪ ቤዓ" በዓል እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ መልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ።

በመልዕክታቸው በዓሉ የቀደሙ አባቶች የነበራቸውን ጥንታዊ የከዋክብትና የጨረቃ ዑደት መነሻ ያደረገ የዘመን አቆጣጠር እውቀት፣ ባሕላዊ ዕሴቶችና ትውፊታዊ ክዋኔዎችን አጣጥሞ የያዘ ውብ በዓል ነው ብለዋል።

አሮጌውን ዓመት በሰላም፣ በጤናና በደስታ ላሳለፈው ፈጣሪ ምስጋና የሚቀርብበት፤ መጪው አዲስ ዓመት ደግሞ የሰላም፣ የፍቅር፣ የምርታማነትና የብልጽግና ዘመን እንዲሆን የጋራ መልካም ምኞትና ጸሎት የሚደረግበት ነውም ብለዋል።

ቶኪ ቤዓ የሥራ ባሕልን የሚያበረታታ፣ አትረፍርፎ ማምረትና ጠግቦ መብላትን፣ የማካፈል ባህልን የሚያላምድ እንዲሁም የሀገረሰብ ጥበባትንና አብሮነትን ያቀናጀ በዓል እንደሆነም ገልጸዋል።

​እነዚህ ባሕላዊ ዕሴቶች የወንድማማችነትና የእህትማማችነት ትስስርን በማጠናከር ለዴሞክራሲ ሥርዓትና ለሰላም ባህል ግንባታ አይተኬ ሚና እንዳላቸው የጠቆሙት ኃላፊው፤ ወጣቱ ትውልድ እነዚህን ዕሴቶች ሳይበረዙ ጠብቆ ለቀጣይ ትውልድ የማስተላለፍ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ብልጽግና ፓርቲ የሀገራችን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ባሕላቸውንና ዕሴቶቻቸውን በአደባባይ እንዲያከብሩ፣ ቋንቋቸውን እንዲያሳድጉና ታሪካቸውን እንዲጠብቁ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንና ለዚህም በልዩ ትኩረት እየሠራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የዳውሮ ብሔረሰብ የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ነው።የዳውሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል (ቶኪ በአ) አከባበር አካል የሆነው የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም በታርጫ ከተማ...
04/09/2026

የዳውሮ ብሔረሰብ የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የዳውሮ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል (ቶኪ በአ) አከባበር አካል የሆነው የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም በታርጫ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ የብሔረሰቡ መገለጫ ስለሆነው የቶኪ በአ በዓል አከባበር ጥናታዊ ጽሑፍ የሚቀርብ ሲሆን፤ በዓሉን በዩኔስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ላይም ገለጻ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

የቶኪ በአ በዓል በብሔረሰቡ ዘንድ የሠላም፣ የእርቅ፣ የጥጋብና የአንድነት መገለጫ ሆኖ የሚከበር ሲሆን በሲምፖዚየሙ የባህሉን ይዘት ሳይለቅ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት ይደረጋል።

በሲምፖዚየሙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የብሄረሰቡ ተወላጆች እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል።

የዘመን መለወጫ በዓሉ በነገው ዕለትም በታርጫ ከተማ በአደባባይ በድምቀት ይከበራል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌Southwest Communicationsnsnsn/
📌በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/
📌በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
📌በሊንክደን
https://www.linkedin.com/company/southwest-communications/
📌በትሬድስ
https://www.threads.com/
📌በብሉ ስካይ
https://bsky.app/profile/swc79..bsky.social
በደብልው ኤን ሶሻል
https://wnsocial.com/page/16775

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳ...
04/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ለክልሉ ሕዝቦችና ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ ለዳውሮ ብሔር የዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል እንኳን አደረሳችሁ፣ አደረሰን! ብለዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው እንደገለጹት፤ "ቶኪ በዓ" የዳውሮ ብሔር ዘመን ተሻጋሪ የምስጋና፣ የአሮጌውን ዓመት በሠላም ሽኝቶ አዲሱን ዓመት በአዲስ በተስፋ የመቀበያ የሰላምና የአንድነት መገለጫ በዓል ነው።

በዓሉ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ ወዳጅና ዘመድ በፍቅር የሚመራረቁበት፣ አባቶች መጪው ዓመት የሰላም፣ የፍቅርና የጥጋብ እንዲሆን የሚመርቁበት እንዲሁም ልጆች በከፍተኛ ናፍቆት የሚጠብቁት የብሔሩ ታላቅ ባህላዊ ዕሴት መሆኑንም አብራርተዋል።

አክለውም ይህንን ድንቅ ባህላዊና ታሪካዊ በዓል ጠብቆ፣ አልምቶና ማኅበራዊ ዕሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በመጨረሻም ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የአብሮነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/
📌በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
📌በሊንክደን
https://www.linkedin.com/company/southwest-communications/
📌በትሬድስ
https://www.threads.com/
📌በብሉ ስካይ
https://bsky.app/profile/swc79..bsky.social
በደብልው ኤን ሶሻል
https://wnsocial.com/page/16775

03/09/2026

እንኳን ለኮንታ ብሔር ዘመን መለወጫ #ህንግጫ በዓል በሠላም አደረሳችሁ
ህዩዋ..ባላ ህዩዋ..!

03/09/2026
በቡና ምርት ዙሪያ አርሶ አደሩ ያለውን ጠንካራ የሥራ ባህል  በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀበNABU ኢትዮጵያ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ማስተባበሪያ ጽህ...
03/09/2026

በቡና ምርት ዙሪያ አርሶ አደሩ ያለውን ጠንካራ የሥራ ባህል በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ

በNABU ኢትዮጵያ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት በቡና መረጃ መሰብሰቢያ መተግበሪያ (Ethiopian Coffee Traceability Management System) ላይ ሲሰጥ የነበረው የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቋል።

በማጠቃለያ ላይ የአተገባበር መርህዎች ላይ አቅጣጫ ያስቀመጡት የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ባለስልጣን ተወካይ አቶ ሽመልስ አራጋው፣ የስልጠናውን ግብ ለማሳካት በየደረጃ ያሉ የግብርና ሴክተር ተዋናዮችን በቁርጠኝነት መደገፍና ማብቃት ያስፈልጋል ብሏል።

NABU ኢትዮጵያ የEUDR መስፈርትን ለሟሟላት ከፍተኛ አማካሪዎችን ቀጥሮ መሰል ድጋፎችን መስጠቱ ለክልሉ ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለው በቀጣይ የክትትል ስርዓትን በመዘርጋት ከክልሉም አልፎ ሀገሪቱ ከቡና ኤክስፖርት የሚታገኘውን ጥቅም ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።

በNABU ኢትዮጵያ የገበያ ልማትና እሴት ሰንሰለት ኢፊሰር አቶ ልሳኑ ተሾመ፤ በስልጠናው የተነሱ ማሻሻያዎች ተካተው ሲመጣ ለአጠቃቀም ምቹ ያደርገዋል ብለው የ EUDR መስፈርቶች ከዚህ ቀደም ብዙ ዕድሎችን ስለሰጠ እና ከቀጣይ ጥር ጀምሮ ወደ ትግበራ ስለምገባ ከወድሁ መሰናዳት አለብን ብለዋል።

ዩኒዬኖችና አርሶ አደሮችን ጨምሮ በቡና ምርት ሂደት ላይ ያሉ ተዋናዮችን መደገፍ የእናንተ ኃላፊነት ነው ብለው ፕሮጀክታቸው በጊዜና ገንዘብ የተገደበ ቢሆንም በቀጣይ በክልሉ ከፍተኛ ቡና አምራች ዞኖችን እንደሚደግፉ አቶ ልሳኑ ገልጿል።

የመረጃ ስርዓቱን ለማስረጽ የሚንቀሳቀሰው አማካሪ ቡድን ሰብሳቢና አሰልጣኝ ዶ/ር ክፍሌ በላቸው፤ ፕሮጀክቱ ከዓለም ዐቀፍና ሀገራዊ ተቋማት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኝ ተደርገው የተሻለ ቁመና ላይ መሆኑን ጠቅሰው በዓለም ገበያ ተመራጭ ከመሆን የሚያግደን ነገር አይኖርም ብሏል።

ስልጠናው ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ላይ ከፍተኛ መነቃቃትን የፈጠረ መሆኑን የገለጹት ተሳታፊዎች በቡና አምራችነት ፈር ቀዳጅ የሆነው ህብረተሰብ ከቡና ጋር የነበረውን ጠንካራ ባህል ወደ ቴክኖሎጂ በማሸጋገር የኢኮኖሚው ተጠቃሚ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።

የ EUDR መስፈርትን ለሟሟላት የበለፀገው አዲሱ መተግበሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግና ለፈፃሚዎች ያልተቋረጠ ድጋፍ መስጠት የሚጠይቅ ስለሆነ በከፍተኛ ኃላፊነት ወደ ትግበራ እንደሚገቡ ተናግረዋል።

የአሰራር ስርዓቱ ወጥነትን የሚጠይቅ በመሆኑ የልምድ ልውውጥ ያስፈልጋል ያሉት ሰልጣኞች፤ የቴክኖሎጂ እና ኢንተርኔት መሠረተ ልማት ተግዳሮት እንዳይሆን የሚመለከተው አካል ከወድሁ እንዲሰራበት ጠይቀዋል።

በአሻግሬ ገብረወልድ

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/
📌በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
📌በሊንክደን
https://www.linkedin.com/company/southwest-communications/
📌በትሬድስ
https://www.threads.com/
📌በብሉ ስካይ
https://bsky.app/profile/swc79..bsky.social
በደብልው ኤን ሶሻል
https://wnsocial.com/page/16775

መንግሥት የዜጎችን ኑሮ ማሻሻልና ዘላቂ ብልጽግናን ማረጋገጥ ቀዳሚ አጀንዳው አድርጓል - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎትመንግሥት ሀገራዊ ሪፎርሞችን በመተግበር የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት...
03/09/2026

መንግሥት የዜጎችን ኑሮ ማሻሻልና ዘላቂ ብልጽግናን ማረጋገጥ ቀዳሚ አጀንዳው አድርጓል - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

መንግሥት ሀገራዊ ሪፎርሞችን በመተግበር የሕዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የገባውን ቃል ወደ ተግባር እየለወጠ ይገኛል።

ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥና የዜጎቿን ሕይወት ከፍ ለማድረግ በምታደርገው ያልተቋረጠ ርብርብ፣ የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ የሚያበስሩ ታሪካዊ ምዕራፎች እውን እየሆኑ ይገኛሉ።

መንግሥት ሕዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስልታዊ ፖሊሲዎችን በመንደፍና በመተግበር በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጦችን በማስመዝገብ ላይ ይገኛል።

በዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ይፋ የተደረገው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል የተደረሰው ታሪካዊ ስምምነት የዚህ አበይት ርዕይ አንዱ ማሳያ ነው።

በ100 ቢሊዮን ብር ካፒታል የሚቋቋመውና ዓለም አቀፍ አጋርነትን ያካተተው የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ፣ በባንክ ዘርፍ ያለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን በመቅረፍ ለዜጎች አስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት ይፈጥራል።

ይህ ታሪካዊ ስምምነት መንግሥት በተመጣጣኝ ዋጋ የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ ያስቀመጠውን ግብ በግንባር ቀደምትነት የሚያሳካ ነው።

ስምምነቱ የዜጎችን የቤት ባለቤትነት ፍላጎት እውን በማድረግ ረገድ የሚታዩ ማነቆዎችን በመስበር፣ የበርካቶችን የዕለት ተዕለት ሕይወትና ማኅበራዊ ደኅንነት በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያሻሽል የመንግሥት ቁርጠኝነትን ያረጋገጠ ቁልፍ እርምጃ ነው።

ይህ ስኬት ብቻውን የቆመ አይደለም፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በሜጋ ፕሮጀክቶች የተመዘገቡት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ድሎች ቀጣይ ምዕራፍ አካል ነው።

የመደመር መንግሥት የግል ዘርፉን ተሳትፎ በስፋት በማካተትና የገበያ ሥርዓቱን በማዘመን ሀገራዊ የኢኮኖሚ አቅምን ማጠናከር የልማት ጉዞው መሠረት አድርጎ ቀጥሏል።

እንደ ሀገር እየተመዘገበ ካለው ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ጋር ተያይዞ በሚፈጠር የዋጋ ግሽበት አነስተኛ ገቢ ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ላይ የሚደርሰውን ተጋላጭነት ለመቀነስ፣ መንግሥት በቢሊዮኖች የሚቆጠር በጀት በመመደብ በነዳጅ፣ በመሠረታዊ ፍጆታዎች እና በግብርና ግብዓቶች ላይ ከፍተኛ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል።

ከዚህ የዕለት ኑሮ ማቃለያ ሥራ ባሻገር የዜጎችን ኑሮ በዘላቂነት ማሻሻልና ብልጽግናን ማረጋገጥ ቀዳሚ አጀንዳው አድርጓል።

በዚህም ቃል በተግባር እየተለወጠ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ የመገንባት ጽኑ ፍላጎቱ በሁሉም መስክ በተግባር እየተፈጸመ ቀጥሏል።

"የኢትዮጵያ ማንሰራራት"
03/09/2026

"የኢትዮጵያ ማንሰራራት"

‎የዳኝነት አገልግሎትን ወደ ተገልጋይ ለማቅረብና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ የባህል ፍርድ ቤት አገልግሎት ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑ ተገለፀ።‎‎የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ20...
03/09/2026

‎የዳኝነት አገልግሎትን ወደ ተገልጋይ ለማቅረብና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ የባህል ፍርድ ቤት አገልግሎት ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑ ተገለፀ።

‎የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና የ2019 ዕቅድ ዙሪያ በሚዛን አማን ከተማ የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

‎የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን የ2018 በጀት ዓመት ሪፖርት በጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት በክቡር አቶ ጥላሁን ታደመ በቀረበበት ወቅት እንደተገለፀው የዳኝነት አገልግሎቱን ነፃ ፍትሃዊና ተደራሽ ከማድረግ ባሻገር አገልግሎትን ለተገልጋይ ለማቅረብና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመቀነስ አንፃር የባህል ፍርድ ቤቶችና የማህበራዊ ፍርድ ቤቶች ከፍተኛ ድርሻ እየተወጡ መሆኑ ተመላክተዋል።

‎በክልሉ በ758 ቀበሌዎች ባህላዊ ፍርድ ቤቶች ተደራጅተው የዳኝነት አገልግሎት እየሰጡ ስሆን በዚህም በ2018 በጀት ዓመት 2693 መዝገቦች ቀርበው ለ2424 መዝገቦች ውሳኔ መሰጠቱንም ተገልፀዋል።

‎በ2018 በጀት ዓመት 506 አድስ ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ማደራጀት የተቻለ ስሆን በቀጣይ በሁሉም ቀበሌዎች ተደራሽ በማድረግ የፍትህ አገልግሎትን ወደማህበረሰቡ የማቅረብ ስራ ተጠናክሮ እንደምቀጥል ተገልጿል ።

‎ከባህል ፍርድ ቤት ባሻገር የማህበራዊ ፍርድ ቤቶች አደረጃጀት በአዋጅ ከተሻሻለ ወዲህ የአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍናን ማሳደግ እንደተቻለውም ተጠቁመዋል። በ2018 በጀት ዓመት በክልሉ ሁሉም ቀበሌ ማህበራዊ ፍርድ ቤቶች 16,816 መዝገቦች ቀርበው 15,109 መዝገቦች ውሳኔ እንዳገኙ ተገልጿል።

‎የባህል ፍርድ ቤቶችና ማህበራዊ ፍርድ ቤቶች የማህበረሰቡን እሴት የጠበቁ በመሆናቸው ውጤታማነታቸው የተመሰከረ ስሆን የመደበኛ ፍርድ ቤት አገልግሎት ጫናን በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሱ መሆናቸውም ተመላክተዋል።

‎በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ቀርቦ ውሳኔ ካገኙ 61 ሺህ 20 መዝገቦች ውስጥ 9878 መዝገቦች በኮንትሮባንድና ንግድ ጉዳዮች፣ግብርና ታክስ ማጭበርበር፣ህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ደንና ሌሎች ተፈጥሮ ሀብት ውድመትና መሰል ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ ውሳኔ እንደሆነም ተገልጿል።

‎በቀረበው ሪፖርት መነሻ የጉባኤ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየትም የታዩ ክፍተቶችን በማረምና መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋፋት የዜጎችን የፍትህ የማግኘት መብት በአግባቡ ለመመለስ እንደሚሰሩ ገልጿል።

‎የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ቆጭቶ ገብረማርያም በሰጡት ማጠቃለያ መልዕክት የፍትህ አገልግሎት ተደራሽነት ጥራትና ቅልጥፍናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ የቴክኖሎጂ ስርፀትን ተደራሽ ማድረግና ጥራታቸውን ከማስጠበቅ አንፃር ትኩረት ተደርጎ ይሰራል ብለዋል።

‎የፍትህ ዘርፉን አመኔታ ለማትረፍ የስነምግባር ጥሰቶች ላይ ጥብቅ ክትትልና እርምጃ እንደምኖር ያብራሩት ፕሬዝዳንቱ ጥሰት ውስጥ የሚሳተፉ የፍትህ አካላት ስገኙ ማህበረሰቡ በተለያየ መንገድ ጥቆማውን ልያደርስ ይገባል ብለዋል።

‎በ2019 በጀት ዓመት 68,279 መዝገቦች ቀርቦ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ የታቀደ ስሆን ለዕቅዱ ተፈፃሚነት የፍትህ አካላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጠንካራ ቅንጅት ልኖራቸው እንደሚገባም ተገልጿል።

‎በመጨረሻም በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች እውቅና የተበረከተ ስሆን በዚህም ካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ፤ ኮንታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ እንድሁም ቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሶስተኛ በመሆን እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

‎በንጉሴ ወልደየስ

‎በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
‎📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
‎📌በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
‎📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
‎📌በትዊተር twitter.com/sweprs
‎📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/.communi
‎📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
‎📌በዩቲዩብ youtube.com/
‎📌በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
‎📌በሊንክደን
https://www.linkedin.com/company/southwest-communications/
‎📌በትሬድስ
https://www.threads.com/
‎📌በብሉ ስካይ
https://bsky.app/profile/swc79.. bsky.social
‎በደብልው ኤን ሶሻል
https://wnsocial.com/page/16775

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)  የዳውሮ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል ለመታደም ታርጫ ከተማ ገቡ‎‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢን...
03/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የዳውሮ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል ለመታደም ታርጫ ከተማ ገቡ

‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የዳውሮ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ "ቶኪ በዓ" በዓል ለመታደም ዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ገብተዋል።

‎በዳውሮ ብሔረሰብ ዘንድ ታላቅ ስፍራ የሚሰጠው የብሔረሰቡ ዘመን መለወጫ የሆነው "ቶኪ በዓ" በዓል ነሐሴ 29 እና 30/2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት በታርጫ ከተማ ይከበራል።

‎ይህንን ታላቅ በዓል ለመታደም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ታርጫ ከተማ ሲገቡ የታርጫ ከተማ አስ/ር አመራሮች፣ የአከባቢ ሽማግሌዎች፣ በዞኑ አመራሮች እና በሌሎች ማህበረሰብ ክፍሎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

‎የሠላም፤ የእርቅ እና የአንድነት መገለጫ የሆነው የቶኪ- በዓ በዓል የብሔረሰቡ ተወላጆች፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በፓናል ውይይት እና በተለያዩ ባህላዊ ኩነቶች ይከበራል ሲል የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።

Address

Bonga

Telephone

+251913241234

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Southwest Communications posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Southwest Communications:

Shortcuts

Share