የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication This is The official Butajira City Gov't COMM.fb page-ይህ ትክክለኛው የቡታጅራ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን (fb)ፔጅ ነው፦
(1)

የሰላም ሚኒስቴር ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር “በጎነት ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች ደም ለገሱነሐሴ 19/2018 ዓ.ም ቡታጅራየሰላም ሚኒስቴር ከቡታጅራ...
25/08/2026

የሰላም ሚኒስቴር ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር “በጎነት ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች ደም ለገሱ

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም ቡታጅራ

የሰላም ሚኒስቴር ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር “በጎነት ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በክረምት ወራት ውስጥ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

እየተካሄደ በሚገኘው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚሳተፉ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም የደም ልገሳ ያደረጉ ሲሆን፤ ባለፉት ቀናትም በማህበራዊ ድጋፍ፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በአከባቢ ፅዳት፣ የትራፊክ ደንብ ማስከበር ስራዎች ላይ በበጎ ስራዎች መሳተፋቸውን በመግለፅ የከተማው ነዋሪዎችም ላደረጉት ቀና ትብብር ከሰላምና ሚኒስቴር የመጡ አካላት ምስጋናቸውን አስተላልፈዋል።

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አማን ጀማል በከተማዋ ባለፉት ግዚያትም ድንበር ተሻጋሪ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አካላት ሰጪዎች, ዩኒቨርስቲዎች ሌሎችም ከተማ አስተዳደሩ ተቀብሎ ወጣቶችን በማስተባበር ሰፊ ሰራ መሰራቱን በመጠቆም ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይም ግዚያት እንደዚ ድጋፍ ሰጪ አካላት ተቋማት ድርጅቶች በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
በጎነት ለአብሮነት!!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ያለፉት ሶስት አመታት የጤናው ዘርፍ እምርታዎችበክልል ባለፉት ሶስት አመታት የህዝብ ተሳትፎ ን በማሳደግ ጥራት ያለው እና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ ከፍተኛ...
25/08/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ያለፉት ሶስት አመታት የጤናው ዘርፍ እምርታዎች

በክልል ባለፉት ሶስት አመታት የህዝብ ተሳትፎ ን በማሳደግ ጥራት ያለው እና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ ከፍተኛ ርብርብ ሲደረግ ቆይቷል።

ዘርፉ ከአዲሱ የጤና ኤክስቴንሽን ፍኖተ ካርታ ትግበራ መነሻ፣ የኤክስቴንሽን ፕሮግራሙን አጠናክሮ ከመተግበር ጎን ለጎን የጤና አገልግሎቶች አቅርቦትና ጥራት እንዲሻሻል ባደረገው ቅንጅታዊ ጥረት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል።

ህብረተሰቡ አገልግሎቶችን በአቅራቢያው ማግኘት እንዲችል የጤና ኬላዎችን ደረጃ በማሻሻል አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል። በሶስት አመታት ውስጥ የአጠቃላይ ጤና ኬላዎችን ግንባታ በማጠናከር 18 አዳዲስ ጤና ኬላዎች አገልግሎት በማስጀመር ብዛታቸውን ከ7 ወደ 25 ማሳደግ ተችሏል። የመሠረታዊ ጤና ኬላዎችን ብዛት በ2016 ሁለት ብቻ ከነበረበት ወደ 50 ማሳደግ ተችሏል።

በሶስት ዓመቱ 34 አዲስ ሞዴል የማህበረሰብ መድኃኒት ቤቶች ስራ በማስጀመር ቁጥራቸውን በ2015 በጀት ዓመት 5 ብቻ ከነበረበት ወደ 39 ማሳደግ ተችሏል። በ2018 በጀት ዓመት ብቻ 21 ስራ በማስጀመር የተደረገው ከፍተኛ መሻሻል ተግባሩ ከዓመት ወደ ዓመት እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያመለክት ነው። በአሁኑ ወቅትም 26 ሞዴል የማህበረሰብ መድኃኒት ቤቶች በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛሉ።

ለጤና ተቋማት የግብዓት አቅርቦት ከማሻሻል አንጻር በሶስት ዓመት 2 ቢሊየን ብር የሚጠጋ ግምት ያለው የህክምና መሳሪያዎችና መድኃኒቶች ከህብረተሰቡ፣ ከባለሀብቶች፣ ከመንግስት እና ከአጋሮች ድጋፍ በማሰባሰብ እንዲሰራጭ ተደርጓል።

ለ18 ሁሉአቀፍ ጤና ኬላዎችና ለ6 መሠረታዊ ጤና ኬላዎች ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓት ሀብት ማሟላት ተችሏል።ማህበረሰቡን ጨምሮ ከተለያዩ አካላት የመድሃኒቶች እና የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ የማሰባሰብ ስራ ከዓመት ወደ ዓመት ትልቅ እድገት ያሳየ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት ብቻ ብር 1ቢሊዮን 590 ሚሊዮን ብር የሚገመት የህክምና መሳሪያዎችና መድኃኒቶች ድጋፍ መሰብሰብ ተችሏል። ከዚህም መካከል 416 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆነው ከህብረተሰቡና ከባለሀብቶች ድጋፍ የተሰበሰበ ነው።

እንደ ክልል ከፍተኛ ስኬት እየተገኘባቸው ያሉ የእናቶች ማቆያዎችን ቁጥ 221 በማድረስ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጡ ሆኗል።የእናቶች ጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን ለማስፋት ባለፉት ሶስት አመታት ውስጥ 112 የአልትራሳውንድ መሳሪያዎች ተገዝተው አግልግሎት እንዲሰጡ ተድርጓል።

የህዝብ ተሳትፎ ንቅናቄ በመፍጠር ከመንግስትና ከማህበረሰብ በተሰበሰበ ከ524 ሚሊዮን ብር በላይ በሚገመት ሀብት 42 አዳዲስ ሁሉአቀፍ እና 6 መሠረታዊ ጤና ኬላዎችን ማስገንባት ተችሏል። የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም አገልግሎት አሰጣጥን ከማዘመን አንጻር በ36 ወረዳዎች በዲጃታል ስርዓት የታገዘ አገልግሎት እንዲሰጥ እየተደረገ ይገኛል።

ከጽዱ ኢትዮጵያ ኢንሼቲቭ ትግበራ ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የንጽህና ግብዓቶች ስርጭት የተካሄደ ሲሆን ፣ወደ ጽዱ ኢትዮጵያ ትግበራ የገቡ ወረዳዎችን ብዛት ከ8 ወደ 10 አድጓል። አሁን ላይ እንደ ክልል የሳኒቴሽን አገልግሎት ያላቸው አባ/እማወራዎች ሽፋን 31% የነበረው ወደ 51.6% ማድረስ ተችሏል። ይህ ብቻ ሳይሆን ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነጻ የሆኑ ቀበሌዎችን ብዛት ከ432 ወደ 755 በማሳደግ ሽፋኑን ወደ 63% ማሳደግ ተችሏል።

በክልሉ በተሰሩ የወረርሽኝ ቁጥጥር ስራዎች የወባ በሽታ ጫና ካለፉት ዓመታት አንጻር በ2018 በጀት ዓመት በ20% ቅናሽ አሳይቷል።

ከአገልግሎት ዲጅታላይዜሽን ጋር ተያይዞ በሶስት ዓመታት ዘጠኝ ሆስፒታሎች ከወረቀት ነፃ የሆነ የጤና አገልግሎት በማስጀመር ቁጥራቸውን ከ3 ወደ 12 ማሳደግ ተችሏል። በአምስት ጤና ጣቢያዎች የድንገተኛ ቀዶ ጥገና ህክምና አገልግሎት እንዲጀምር ተደርጓል። ከዚህ በተጨማሪም ሰባት ጤና ጣቢያዎች ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ግብዓት በማሟላት የድንገተኛ ቀዶ ጥገና ህክምና አገልግሎት እንዲጀምሩ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።

በጥቅሉም ክልሉ ሲቋቋም አገልግሎት በሚሰጡ የጤና ተቋማት ቁጥርና ደረጃ አኳያ በ2015 በጀት ዓመት መጨረሻ ላይ ከነበረው አንጻር እድገት የተመዘገበ ሲሆን በዚህም የኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሎች ቁጥር ከአንድ ወደ ሶስት፥ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች ቁጥር ከ19 ወደ 25፥ የጤና ጣቢያዎች ቁጥር ከ219 ወደ 244 እንዲሁም የኮምፕሬሄንሲቭ ጤና ኬላዎች ቁጥርን ከ6 ወደ 25፥ ሞዴል የማህበረሰብ መድሃኒት ቤቶች ቁጥር ከ5 ወደ 39 ማሳደግ ተችሏል።

በዚህም ለህብረተሰቡ የጤና አገልግሎቶችን ተደራሽነት፥ የተሻለ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎቶችን አቅርቦትን እና የመድሃኒትና የህክምና ግብዓቶች አቅርቦትን ማሳደግ ተችሏል።
(የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን)

የምህረት፣ የሰላም እና የመተሳሰብ ብርሃን፤ ታላቁ የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) 1501ኛው መውሊድ በድምቀት***************​በየዓመቱ በረቢዑል አወል ወር በታላቅ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ...
25/08/2026

የምህረት፣ የሰላም እና የመተሳሰብ ብርሃን፤ ታላቁ የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) 1501ኛው መውሊድ በድምቀት
***************

​በየዓመቱ በረቢዑል አወል ወር በታላቅ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥነ-ሥርዓት የሚከበረው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት ቀን (መውሊድ)፣ የነቢዩን መወለድ ከመዘከር ባሻገር የሕይወት ጉዟቸውን፣ ሰብአዊ እሴቶቻቸውን እንዲሁም የመተሳሰብና የሰላም አስተምህሮዎቻቸውን በመዘከር በድምቀት የሚከበር ታላቅ በዓል ነው።

​በዚህ የተባረከ በዓል የእምነቱ ተከታዮች ከታላቁ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ያላቸውን መንፈሳዊ ቅርበት ያድሳሉ፤ የፍቅርና የርህራሔ ታሪካቸውንም ለተተኪው ትውልድ ያስተላልፋሉ።

​"መውሊድ" የሚለው የአረብኛ ቃል በቀጥታ "ልደት" የሚል ትርጉም ያለው ሲሆን፣ በሒጅራ አቆጣጠር በረቢዑል አወል ወር 12ኛው ቀን የተወለዱበትን ዕለት ለማሰብ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በጋራ የሚያከብረው በዓል ነው።

መውሊድ በዓለም አቀፍ ደረጃም ሆነ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሲከበር የምህረት፣ የፍቅር፣ የርህራሔ፣ የለጋስነት፣ የፍትሕና የሰላም እሴቶችን ለማጠናከር እንደ ታላቅ መልካም አጋጣሚ ይወሰዳል።

​በዕለቱም በመስጂዶችና በማኅበረሰብ ስብሰባዎች የጋራ ዱዓዕ ይደረጋል፤ የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ሕይወትና መልካም ሥነ-ምግባር የሚያስታውሱ ድርሳናትና ኪታቦች ይቀርባሉ።

የሐዲስ ትምህርቶች እየተነበቡ፣ በሕብረት ዜማና በመንዙማ በደመቀ ሁኔታ የሚከበር ሲሆን፤ የእምነቱ አባቶችና ምዕመናንም ስለ ሀገራችን ሰላም፣ ፍቅርና አንድነት በጋራ ይጸልያሉ።

​ኢትዮጵያ ከቀደምት የእስልምና ታሪክና ከታላቁ ነቢይ ባልደረቦች (ሶሐቦች) ጋር ጥልቅ ትስስር ያላት ሀገር እንደመሆኗ፣ መውሊድ ከሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓትነቱ ባሻገር ከማኅበራዊና ባህላዊ እሴቶቻችን ጋር አብሮ የሰረፀ ታሪካዊ በዓል ነው።

በተለይም በሐረርና በምሥራቅ የኢትዮጵያ ክፍሎች ያሉ የእስልምና ቅርሶች ከመውሊድ ትውፊት ጋር የተገናኙ ጥንታዊ የጽሑፍና የሥነ-ሥርዓት ሀብቶችን የያዙ ሲሆኑ፣ የበዓሉ አከባበርም የሀገራችንን ረጅም የጋራ የመኖርና የብዝኃነት ባህል አጉልቶ ያሳያል።

​በዓሉ ማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ በርካታ ሰብአዊ ተግባራት የሚከናወኑበት በመሆኑ፣ አቅመ ደካሞችን ማገዝ፣ የየቲሞችንና ምስኪኖችን ቀልብ መደሰት፣ ዘመድ አዝማድን መጠየቅ፣ እንግዶችን ማስተናገድና መልካም ምኞትን መለዋወጥ የበዓሉ ውብ ገጽታዎች ናቸው።

​የዘንድሮው 1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል እንደ ወትሮው ሁሉ የእስልምና እምነት ተከታዮችንና የመላው ሕዝቦቻችንን አንድነት በሚያጠናክር፣ ፍቅርና መፈቃቀር በሚጎለብትበት እንዲሁም በመረዳዳትና በመተሳሰብ መንፈስ የሚከበር ይሁን።
​መልካም የ1501ኛው የመውሊድ በዓል!
(EBC )

25/08/2026
በከተሞች የህዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡ የልማት ፕሮጀክቶች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ሶስት ዓመታት የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች ውጤታማ ናቸው። ​በክልሉ የህዝቡን...
25/08/2026

በከተሞች የህዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡ የልማት ፕሮጀክቶች

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለፉት ሶስት ዓመታት የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች ውጤታማ ናቸው።

​በክልሉ የህዝቡን አኗኗር ለማሻሻል፣ ኢኮኖሚውን ለማጠናከር በየዘርፉ የተጀመሩት የልማት ስራዎች ፍሬ እያፈሩ ይገኛሉ።

​ዛሬ በበርካታ የልማት መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጡ ናቸው።

እያደገ የመጣውን የህብረተሰብ ፍላጎት እውን ለማድረግ ዘመናዊ አሰራርን መርህ ያደረጉ የልማት ፕሮጀክቶች በየጊዜው እድገት እያሳየ ነው።

ባለፉት ዓመታት ከተሞቻችንን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ የማድረግ ስራ በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል። የኮሪደር ልማቱ የከተሞቻችንን ገፅታ ከመቀየሩ ባሻገር ለንግድና ለኢንቨስትመንት ዘርፎች አዲስ እይታን ፈጥሯል።

የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተሞችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና መዋቅራዊ ገጽታ በመቀየር ለዘላቂ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።

የኮሪደር ልማትን ተከትሎ የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ዝርጋታዎች የእግረኛ እና የብስክሌት መስመሮችን በማስፋፋት የትራንስፖርት መጨናነቅን በእጅጉ መቅረፍ የሚያስችሉ ናቸው።

ለንግድ ስራዎች ምቹ መደላድል በመፍጠር ረገድ የኮሪደር ልማት ስራ የላቀ አበርክቶ አለው።፣ የስራ እድል በመፍጠር እና የከተሞችን ኢኮኖሚ ማነቃቃት ያስችላል።

የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ዳር መብራት፣ የጠጠርና የአስፋልት መንገድ፣የጌጠኛ ድንጋይ መንገዶች ዝርጋታ የከተሞችን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አፋጥኖታል።

የከተማ አስተዳደሮች አገልግሎትን ወደ ዲጂታል በማሸጋገር ቀልጣፋ አሰራር እንዲሰፍን እያደረጉ ነው።በዚህም በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋለውን ችግር መቅረፍ አስችሏል።
በክልሉ የተጀመሩት የልማት ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና የክልሉን ሁለንተናዊ እድገት ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

በክልሉ በአንድ ከተማ የአንድ ፕሮጀክት ኢኒሼቲቭ የህብረተሰቡን የጤና እንክብካቤ ተዳራሽነት ለማረጋገጥ የማህበረሰብ መድሀኒት ቤቶች፣የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና መሰል ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።

የተፈጥሮ ሀብታችንን ለአካባቢ ውበትና ለኢኮኖሚ ጥቅም ማዋል የሚያስችሉ የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎች ከተሞቻችንን የማረፊያ፣ የመዝናኛ እና የቱሪዝም ሳቢ ስፍራዎች እያደረጓቸው ይገኛሉ።

እነዚህ ስኬቶች የህዝቡን ሁለንተናዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስቻሉ እና ዘመን ተሻጋሪ የልማት አብነት ናቸው።
(የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን)

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )ለታላቁ ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) 1501ኛ የልደት በዓል /  መውሊድ    የእንኳን  አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉየመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለ...
24/08/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )ለታላቁ ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) 1501ኛ የልደት በዓል / መውሊድ
የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል

ለታላቁ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) 1501ኛ የልደት በዓል / መውሊድ በዓል እንኳን አደረሳችሁ!

ለእስልምና እምነት ተከታዮች ! እንኳን ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) 1501ኛ የልደት በዓል / መውሊድ በዓል አደረሳችሁ! እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ።

ኢትዮጵያዉያን ሀገራዊ የምከክር ጉባኤያቸዉን በተሳካ ሁኔታ ባጠናቀቁበት እና ሀገራችን ኢትዮጵያም አብሮነትን፣አንድነትን እና ብሔራዊ መግባባትን ወደሚያፀና፣ አዲስ ምዕራፍ እየተሸጋገረች በምትገኝበት በአሁኑ ወቅት እየተከበረ የሚገኘው የዘንድሮዉ የነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) የልደት በዓል / የመውሊድ በዓል የወንድማማችነት /የእህትማማችነት እሴቶችን ከፍ ለማድረግ መልካም አጋጣሚ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።

መልካም የመዉሊድ በዓል!

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ውይይት አደረገ።(ነሐሴ 18/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ ቴክኒክ ኮማቴ መደበኛ ውይይት ...
24/08/2026

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፍቃድ ቴክኒክ ኮሚቴ መደበኛ ውይይት አደረገ።

(ነሐሴ 18/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ ቴክኒክ ኮማቴ መደበኛ ውይይት ስራ አፈፃፀም ሪፖርት ገምግሟል።

በውይይት መድረኩ የ2018/19 በክረምት ወራት የተሰሩ የበጎ ፍቃድ ስራዎችን አጠቃላይ ሪፖርት ቀርቦ በጠንካራና መሻሻል ባለባቸው ነጥቦች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

የ2018/19 የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ እቅድ አፈፃፀም ለኮሚቴ አባላቱ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱ በክረምት ወራት በ16 የስምሪት መስኮች በርካታ የበጎ ፍቃድ ተግባራቶች ሲሰሩ የቆዩ ሲሆን በቀጣይም ስራዎች የበለጠ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በተግባር ሂደቱም የባለድርሻ አካላት የቅንጅት ስራዎች መጠናከርና የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ተደራሽ መሆን ላለባቸው ወገኖች መድረስ እንደሚገባ ተገልጿል።

በቀጣይ የበጎ ፍቃድ ተግባራቶች ውስንነቶች በመቅረፍ በተሻለ መልኩ መፈፀም እንዳለባቸው በአባላቱ ተመላክቷል።

በተቋማት የሚስተዋሉ የብልሹ አስራርና አመራር ላይ የሚደርገው  የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የዕርምት ዕርምጃ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተመላከተ! #ቡታጅራ ነሀሴ 18/2018 የምስራቅ ጉ...
24/08/2026

በተቋማት የሚስተዋሉ የብልሹ አስራርና አመራር ላይ የሚደርገው የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የዕርምት ዕርምጃ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተመላከተ!

#ቡታጅራ ነሀሴ 18/2018

የምስራቅ ጉራጌ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት "ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀተ ዓመት ሪፖርት ግምገማና የ2019 ዕቅድ ላይ የምክክር መድረክ አካሄዷል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን የብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ አዳነ ተሰማ እንደገለፁት በብልሹ አስራርና አመራር ላይ የምናደርገው የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የዕርምት ዕርምጃ የመውሰድ ተልዕኮ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

የዞኑ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ የፈፀማቸው ተግባራት በጥሩ ደረጃ እንዳለ ከግምገማ ሪፖርቱ ማረጋገጥ እንደቻሉ የተናገሩት አቶ አዳነ በቀጣይ የኮሚሽኑ ተግባራት እስከ ወረዳ፣ ከተማና ቀበሌ ድረስ የአደረጃጀትና የአሰራር ስርዓታችን እንዲጎለብት መትጋት አለብን ብለዋል።

በየመዋቅሩ ያሉ የህብረት ኮሚሽኖች ቢያንስ በየሩብ ዓመት የክትትልና ድጋፍ በማድረግ ክፍተቶች በማመላከት እንዲታረሙ ማድረግ፣ የኮሚሽን አመራሩና አባላቱ ኃላፊነታቸው በመወጣት የድርሻቸው ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሙንታሃ ሽሁር በማጠቃለያ መድረኩ ላይ እንደተናገሩት በተቋማት ደረጃ የሚስተዋሉ የአሰራር ግድፈቶች ማስቆም የሚችል ተቋማዊ አሰራርና አመራር መግንባት እንደሚገባ አመላክተዋል።

በዞኑ ኮሚሽንና በመዋቅሮች የኮሚሽን ተቋማት መካከል ያለው የግንኙነት ሥርዓት ይበልጥ በማሳደግ ድክመቶች በየጊዜው እየገመገሙ የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዲስተካከሉ በማስቻል የኢንስፔክሽን ሥራውው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀዋል።

ኃላፊዋ አክለውም በቀጣይ የ2019 በጀት ዓመት ሁሉም የኮሚሽን ተቋማት ያለቸው የመፈፀም አቅም በማሳደግ እንዲተጉ አሳስበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አሰፋ ፈይሳ በበኩላቸው በአሰራር ብልሹነት ምክንያት የሚፈጠሩ ህዝባዊ ቅሬታዎች ምላሽ መስጠት የሚችል ጠንካራ የኢንስፕክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ተቋም መገንባት እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

የክትትልና ድጋፍ ሥራችን በትክክል ክፍተቶች ለይቶ መፍትሔ እንዲያገኙ ማመላከት የሚችሉ መሆን አለባቸው ብለዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊ አካላትም የኮሚሽኑ አሰራሮች ደንቦችና የዲስፕሊን አመራር ሥርዓት ለህዝብ ለማድረስ ተቋሙ የሚዲያ ፕላትፎርሞች በሚገባ ጥቅም ላይ በማዋል በነቃ ተሳትፎ የመረጃ ተደራሽነቱ ማሳደግ እንደሚገባ ምክረ-ሀሳብ ተስጥቷል።

በየመዋቅሩ ያሉ አደረጃጀቶችና የመረጃ ሥርዓት ጥንካሬዎቹ በማስቀጠል ያሉባቸው ጉድለቶች ፈጥነው በማስተካከል ለኮሚሽኑ ጥቅል ውጤታማነት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ከመደረክ ተሳታፊ አካል ተመላክቷል።

በመድረኩ መጨረሻ የዞኑ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት ከየመዋቅሩ ኮሚሽን ቅ/ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የግብ ስምምነት በመፈራረምና ለባለ ድርሻ ተቋማትና የምስክር ወረቀትና በ2018 በጀት ዓመት የላቀ የአፈፃፀም ውጤት ላስመዘገቡ የኮሚሸን ጽ/ቤቶች ዕውቅና የዋንጫ፣ የገንዘብና ምስክር ወረቀት ሽልማት ሰጥቷል። በዚሁ መሠረት፦

1ኛ የሶዶ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት፦ የዋንጫ የ40 ሺ ብር እና የምስክር ወረቀት2ኛ የደቡብ ሶዶ ወረዳ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት፦ የዋንጫ የ30ሺ ብር እና የምስክር ወረቀት

3ኛ የመስቃን ወረዳ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት፦ የዋንጫ፣ የ20ሺ ብር እና የምስክር ወረከት ተበርክቶላቸዋል።

በኮሚሽኑ ህበረት ደረጃ የኢኮኖሚ ዘርፍ ህብረት 1ኛ በመውጣቱ የዕውቅና ሠርተፍኬት በመስጠት የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉእንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁየነቢዩ መሐመድ ታሪክ ት...
24/08/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ
የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡

ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡

ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡

ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡

የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡
በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም

በቡታጅራ ከተማ ኤም ኤስ ትምህርት ቤት የኢኮኖሚ ውስንነት ላላቸው ወገኖች የመሪያ ቤት መልሶ ግንባታ ስራ አስጀመረ።(ነሐሴ 18/2018) በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የኤም ኤስ ትምህርት ቤት ...
24/08/2026

በቡታጅራ ከተማ ኤም ኤስ ትምህርት ቤት የኢኮኖሚ ውስንነት ላላቸው ወገኖች የመሪያ ቤት መልሶ ግንባታ ስራ አስጀመረ።

(ነሐሴ 18/2018) በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የኤም ኤስ ትምህርት ቤት የኢኮኖሚ ውስንነት ላላቸው ወገኖች የመኖሪያ ቤት በበጎ ፈቃድ የመልሶ ግንባታ ስራ አስጀምሯል።

ትምህርት ቤት ከመደበኛው የመማር ማስተማር ስራ በተጨማሪ በበጎ ፈቃድ በየዓመቱ በማከናወን ማህበራዊ ኃላፊየቱን በተገቢው እየተወጣ ይገኛል።

ትምህርት ቤት በባለፈው የበጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር በተመሳሳይ በከተማው ድጋፍ የሚሹ ቤተሰብ ከከተማ አስተዳደሩ የበጎ ፈቃድ አስተባባሪዎች በመቀበል የመኖሪያ ቤት የመልሶ ግንባታና በሌሎችም መስኮች እየተሳተፈ ይገኛል።

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication:

Shortcuts

Share