በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት, Government Organization, ምስራቅ ጉራጌ ዞን/መስቃን ወረዳ/ቡታጅራ, Butajira.

This is our official real Meskan District page, follow and like it to get updated information.
ይህ ትክክለኛ የመስቃን ወረዳ የፌስ ቡክ ፔጃችን ነው ፎሎና ላይክ በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን እንዲደርሶ ያድርጉ።

‎“ሰላማችን ለዘላቂ ብልፅግናችን” በሚል መሪ ቃል የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ  የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋ...
03/09/2026

‎“ሰላማችን ለዘላቂ ብልፅግናችን” በሚል መሪ ቃል የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ።

‎ #ቡታጅራ ነሐሴ 28/2018
‎የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ “ሰላማችን ለዘላቂ ብልፅግናችን” በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የገመገመና የ2019 ዓ.ም ዕቅድን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል።

‎መድረኩ በባለፈው ዓመት በሰላምና ፀጥታ ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎችን መገምገም የታዩ ክፍተቶችን መለየትና በ2019 ዓ.ም በተሻለ መልኩ ለመሥራት እገዛ እንደነበረው ተመላክቷል።

‎የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተካልኝ ንጉሴ በዞኑ ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን ህብረተሰቡን በሰላም ግንባታ ሥራዎች ጠንካራ ተሳትፎ አንዲኖረው ማድረግና ማሳተፍ እንደሚገባ ገልጸዋል።

‎ሰላምን በዘላቂነት ለማስጠበቅ የራስን አቅም ማጠናከር፣ በተቋማትና በህብረተሰቡ መካከል ትብብርን ማጎልበትና የሰላም ግንባታ ሥራዎችን በቀጣይነት ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል።

‎በየአካባቢው የሚከሰቱ የመልካም አስተዳደር፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የቅሬታ ጉዳዮች በጊዜ ተለይተው በአግባቡ ካልተፈቱ ለግጭት መንስኤ ሊሆኑ ስለሚችሉ በቅድሚያ መለየትና መፍትሔ መስጠት አስፈላጊ መሆኑንም አስረድተዋል።

‎በዞኑ በሶዶ ወረዳ ኦሮሚያ አጎራባች ቀበሌዎች አካባቢ የሚንቀሳቀሰው የሽብር ቡድን በህብረተሰቡ ላይ የሰላም መደፍረስና የህይወትና የንብረት ጉዳት እያደረሰ የሚገኘውን ጥቃት ለመመከት የፀጥታ መዋቅሩ ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር እየሰራ ነው ብለዋል።

‎ህብረተሰቡ በሚያደርገው ተሳትፎና በፀጥታ አካላት በሚከፈለው መስዋዕትነት የሽብር ቡድኑን እንቅስቃሴ በመመከት አካባቢዎቹን ሰላማዊ ለማድረግ ተግባራዊ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አቶ ተካልኝ ገልጸዋል።

‎እንዲሁም በዞኑ በምስራቅ መስቃን ወረዳና እንሴኖ ከተማ አካባቢዎችም ከፀጥታ ጋር የተያያዙ ችግሮች መኖራቸው አንስተው ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም መንግስት በየደረጃው የሰላምና ፀጥታ መዋቅሩን በማጠናከር የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎችን በማሳደግና ከህብረተሰቡ ጋር ትብብሩን በማጠናከር እየሰራ መሆኑ ገልፀዋል።

‎የፀጥታ መረጃ ጥራትና ተደራሽነትን ማሻሻል፣ የሚገኘውን መረጃ በተገቢው መጠቀምና በመረጃ ላይ የተመሠረተ የቅድመ ጥንቃቄ ሥርዓት በማጠናከር የፀጥታ ክስተቶችን ቀድሞ ለመከላከልና ከተከሰቱም በፍጥነት ለማረም ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎በተለይም ሀሰተኛ መረጃን በማሰራጨት ነጠላ ትርክቶችን በመዝራት ህብረተሰቡን ለመከፋፈል የሚጠቀሙ የማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶችን በመከታተል፣ ትክክለኛ መረጃን በፍጥነት በማቅረብና የህዝብ የመረጃ ግንዛቤን በማሳደግ ላይ መሥራት እንደሚገባ ያመላከቱ ሲሆን የፀጥታ ምክር ቤት የሚያስቀምጣቸውን አቅጣጫዎች በየደረጃው ወደ ተግባር ማስገባት እንደሚገባ አንስተው በየደረጃው የወሳኝ ኩነቶችን በትክክለኛ መረጃ ላይ መደገፍና መረጃዎችን ዲጂታላይዝድ በማድረግ አገልግሎቱን በተቀመጠው አግባብ ማድረስ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ሙሰማ ጀማል ባለፈው በጀት ዓመት የፀጥታ መዋቅር በቅንጅት በተሰሩት ስራዎች በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።

‎የሰላም ከማስጠበቅ አንፃር በተሰሩ ጠንካራ ተግባራት የፀጥታ መዋቅሩና ህብረተሰብ በጀግንነት ተላላኪ የሆነው ሼኔ የሽብር ቡድን መመከት መቻሉን አንስተዋል።

‎የፀጥታ ሃይሉ ምስራቅ መስቃንና እንሴኖ አካባቢ የሚፈጠሩ ችግሮችን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመስራት እንደሚገኝ ገልፀው በቀጣይ ይበልጥ ተጠናክሮ የዞኑን ህብረተሰብ ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚደረጉት ጥረቶች የበኩሉን እንደሚወጣ አብራርተዋል።

‎የመድረኩ ተሳታፊዎች በ2018 ዓ.ም አፈፃፀም ላይ ያሉ ጥንካሬዎችንና ክፍተቶችን በመገምገም ሃሳብ አስተያየት የሰጡ ሲሆን የሚሊሻና ሌሎች የፀጥታ አካላትን በሥነ-ምግባር ማነፅና ሙያዊ አቅማቸውን ማጠናከርም በመድረኩ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ሆኗል። ይህም የአካባቢና የሀገር ሰላምና ፀጥታን በተሻለ ሁኔታ ለማስከበር የሚያስችል ቁመና እንዲኖራቸው የሚያግዝ መሆኑን በማንሳት የዞኑ የሰላምና ፀጥታ ሥራዎች በተቀናጀ አሠራር፣ በተገቢ መረጃና በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ እንዲመሩም አቅጣጫ ተቀምጧል።

‎በመጨረሻም በዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ የ2019 የግብ ስምምነት ከወረዳና ከተማ አስተዳደር የሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤቶች ጋር ተፈራርመዋል።

‎ከግምገማው መድረክ በተጨማሪም መምሪያው ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ፣ በግዳጅ እያሉ ለተሰው የፀጥታ አካላት የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የአልባሳት ድጋፍ አድርገዋል።

‎ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

  በሚል መሪ ቃል በመስቃን ወረዳ በውሪብ ቀበሌ በበጎ ፈቃደኞች ድጋፍ ፣ በአመራሩ፣  በማህበረሰብ እና በወጣቶች አስተባባሪነት የአቅም ውስንነት ላለባቸው ቤተሰቦች የመኖሪያ የአዲስ ቤት ግን...
03/09/2026

በሚል መሪ ቃል በመስቃን ወረዳ በውሪብ ቀበሌ በበጎ ፈቃደኞች ድጋፍ ፣ በአመራሩ፣ በማህበረሰብ እና በወጣቶች አስተባባሪነት የአቅም ውስንነት ላለባቸው ቤተሰቦች የመኖሪያ የአዲስ ቤት ግንባታ ተጀመረ።
===========================
ነሀሴ_28/2018 ቡታጅራ
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ በጎነት ለኢትዮጲያ ከፍታ በሚል መሪ ቃል በመስቃን ወረዳ በውሪብ ቀበሌ በበጎ ፈቃደኞች ድጋፍ፣ በአመራሩ፣ በማህበረሰብ እና በወጣቶች አስተባባሪነት የአቅም ውስንነት ላለባቸው ቤተሰቦች የመኖሪያ የአዲስ ቤት ግንባታ በዛሬው እለት ተጀምሯል።

የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊና የቀበሌው ደጋፊ አመራር አቶ ጀማል በድሩ፤የመስቃን ወረዳ ገቢዎች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ነጃ ሳቢር፣ የመስቃን ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ም/ሃላፊ እና የወጣት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አህመድ መሃመድ እና ሌሎችም የቀበሌ አጠቃላይ አመራሮችና የኦዶ ማዘጋጃ ስራ አስኪያጅ እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ወጣቶችና ሴቶች የቤት ግንባታ ስራውን አስተባብረዋል።

በዕለቱ ተገኝተው በጋራ መልዕክት ያስተላለፉት አመራሮቹ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ሰው ተኮር ተግባር ከመሆኑም በላይ በመንግስት ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ ነው ብለው የጀመርነውን በማጠናቀቅ በቀጣይ የሌሎች ወገኖቻችን ቤቶች የመገንባትና የማደስ ስራችን በተባበረ ክንድ አጠናክረን መቀጠል አለብን ብለዋል።

የበጎ ተግባር የስራ እንቅስቃሴውን እንደ ቀበሌ በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉ የመረዳዳትና የአብሮነት እሴት የሚያጎላ ነው ብለው በእለቱ ይህንን ተግባር ላስተባበሩ አመራሮች፣ ወጣቶች እና የማህበረሰብ አካላትን አመስግነዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የወዶ ታዳጊ ማዘጋጃ ስራስኪያጅን ጨመሮ የውሪብ ቀበሌ አጠቃላይ አመራሮች፣ የቀበሌው ባለሙያዎች፣ በጎ አስተባባሪ ወጣቶች፣ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት ፣ የአካባቢው ማህበረሰብ እና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው:-የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ነው።

‎==================
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
📌 ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL
📌ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31
📌 ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA
📌 ቲክቶክ -tiktok.com/.woreda.gov
📌 ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT
📌 ኢሜል[email protected]

በመስቃን ወረዳ የ2018 ዓ/ም የጳጉሜ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች በደመቀ መልኩ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራ ላይ ለአመራሮች እና ለኮሚቴዎች ኦረንቴሽን ተሰጠ።‎ ======= #‎ነሀሴ_27/20...
02/09/2026

በመስቃን ወረዳ የ2018 ዓ/ም የጳጉሜ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች በደመቀ መልኩ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራ ላይ ለአመራሮች እና ለኮሚቴዎች ኦረንቴሽን ተሰጠ።
‎ =======
#‎ነሀሴ_27/2018_ቡታጅራ

‎በምስራቅ ጉራጌ ዞን በመስቃን ወረዳ የ2018 ዓ/ም የጳጉሜ ቀናት በተለያዩ ሁነቶች በደመቀ መልኩ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ስራ ላይ ለአመራሮች እና ለኮሚቴዎች ኦረንቴሽን በዛሬው እለት ኦረንቴሽን ተሰጥቷል።

‎የመስቃን ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪና ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም የጳጉሜ ቀናት በዓል አከባበር ዐብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መሀመድ ሳኒ የዝግጅቱ አከባበር ማስፈጸሚያ ዕቅድ ላይ አጭር ገለፃ በማድረግ ኦረንቴሽን ሰጥተዋል ።

የበዓሉን ሁነቶችን የሚያስተባብርና የሚያስፈፅም አብይና ንዑሳን ኮሚቴዎች መደራጀታቸውን የገለፁት ኃላፊው ለዚህ ተግባር ማሳኪያ በዛሬው ዕለት የዝግጅቱ አከባበር ማስፈጸሚያ ዕቅድ ላይ ሰፋ ባለ መርኩ ቀርቦ የጋራ ተደርጓል።

የዕቅዱ ዋና ዓላማ በሀገራችን የሚስተዋለዉን ፈጣን ለዉጥ እና የብልጽግና ጉዞ የተገኘዉን እምርታ፣ ማንሰራራት፣ ጽናት፣ ህብር እና የወደ ፊት ህልምና ትልም የጳጉሜ ቀናትን በመጠቀም ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማስገንዘብ ለቀጣይ የመስፈንጠር ጉዞ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ንቁ የልማት ተሳታፊ ማድረግ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በመድረኩ የመስቃን ወረዳ አስተባባሪ አካላት፣ የሚመለከታቸው ተቋማት የካቢኔ አባላት እና ሌሎች አመራሮችም የተገኙ ሲሆን በቀረበው እቅድ ላይ ተሳታፊዎች ሀሳብ አስታያታቸውን ሰጥተው ተግባቦት በመፍጠር በቀጣይ አቅጣጫ ላይ የስራ ስምሪት በመስጠት ውይይቱ ተጠናቋል።

‎==================
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
📌 ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL
📌ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31
📌 ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA
📌 ቲክቶክ -tiktok.com/.woreda.gov
📌 ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT
📌 ኢሜል[email protected]

የመስቃን ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ከወረዳው ሴቶች አደረጃጀቶች ጋር በመሆን የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ እንዲሁም ለአቅመ ደካማ ወላድ ቤተሰቦችና ለሁለት የወላድ እናቶች ማቆያ ድጋፍ አደረጉ=...
02/09/2026

የመስቃን ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ከወረዳው ሴቶች አደረጃጀቶች ጋር በመሆን የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ እንዲሁም ለአቅመ ደካማ ወላድ ቤተሰቦችና ለሁለት የወላድ እናቶች ማቆያ ድጋፍ አደረጉ
==========
ነሀሴ 27_2018 (የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን)

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ከወረዳው ሴቶች ማህበር፣ የሴቶች ክንፍ እና ሴቶች ፌዴሬሽን ጋር በመሆን የአንድ ሳምንት የክረምት በጎ ፈቃድ ንቅናቄ መርሃ -ግብር አካል የሆነው በጤናው እና በሰላምና ደህንነት መስክ በሚል መሪ ቃል የማህፀን ጫፍ ካንሰር ምርመራ ግንዛቤ ሰጥተዋል።

በተጨማሪም " ቡና ለሰላም!" እና "እኔ የሰላም እናት ነኝ!" በሚል መሪ ቃል በግዴና አቦራት ቀበሌ በርካታ መርሃ ግብሮች በማካሄድ ማለትም የጤናና የሰላም ግንዛቤ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን በ2 ጤና ጣቢያዎች የእናቶች ማረፊያ ጉብኝትና ድጋፍ ተደርጎ ለአቅመ ደካማ ወላድ ቤተሰቦችና ለሁለት የወላድ እናቶች አስፈላጊ ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርገዋል።

የመስቃን ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ የወይን ሀረግ ተስፋዬ እንደገለፁት ሴቶች እንደ ሀገር የተሻለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚደረገው ጉዞ ዋነኛ ተዋናዮች ናቸውና ዕራሳቹን ልትጠብቁና ልትንከባከቡ ይገባል ብለው ሴቶች በየትኛውም መስክ ድጋፍ ሊደረግላቸው እና ከየትኛውም ጎጂ ባህል ተፅኖዎች በጋራ በመሆን ልንጠብቅ ይገባል እኛም እንደ ሴቶችና ህፃናት በየትኛውም ጉዳይ ከጎናችን ነን ሲሉ ገልፀዋል።

በዕለቱም የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ፅ/ቤት ሀላፊ፣የሴቶች አደረጃጀቶች ሀላፊዎች፣የወረዳ ሴት አመራሮች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

ዘገባው የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ነው።

አዲሱን ዓመት በተስፋና በከፍታ የምንቀበልባቸው የጳጉሜን ቀናት መርሃ-ግብሮች ******************የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፣ ...
02/09/2026

አዲሱን ዓመት በተስፋና በከፍታ የምንቀበልባቸው የጳጉሜን ቀናት መርሃ-ግብሮች
******************

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፣ የ2018 ዓ.ም የጳጉሜ ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል እንደሚከበሩ ይፋ አድርገዋል፡፡

ይህ መሪ ቃል ኢትዮጵያ አሁን ላይ ያለችበትን ሁለንተናዊ የለውጥና የዕድገት ጉዞ እንዲሁም የነገዋን የበለፀገች ሀገር የመገንባት ጽኑ ፍላጎት የሚያንፀባርቅ ነው፡፡

እያንዳንዱ የጳጉሜን ቀን የራሱ ልዩ ትርጉምና ዓላማ ያለው ሲሆን፣ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድነትና በተስፋ እንዲያከብረው ተዘጋጅቷል፡፡

✅ጳጉሜን 1 “የምርታማነት ቀን” በሚል ስያሜ፣ ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ጉዞ ተላቃ ወደ ፈጣንና ምርታማዊ እድገት መግባቷን በማሰብ ይከበራል፡፡

በእለቱ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በእዳ ቅነሳ፣ በቱሪዝም እና በውጭ ምንዛሬ ዘርፎች የተመዘገቡት አስደማሚና ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ይነሳሉ።

✅ጳጉሜን 2 “የማንሰራራት ቀን” ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በታዳሽ ሀይል፣ በከተሞች ገጽታ እና በገጠር ኮሪደር ልማት በጣለችው ጠንካራ መሰረት ላይ በመቆም ወደ ተሻለ ከፍታ የተሻገረችበት ድንቅ ስራ ይወሳል፡፡

✅ጳጉሜን 3 “የፅናት ቀን”፣ የሀገራችንን ነፃነትና ሉአላዊነት ደማቸውን አፍሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው ጠብቀው ያቆዩልን ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን የሚዘከሩበት ክቡር ቀን ነው፡፡

የዛሬውን ትውልድ ሀገራዊ ተሳትፎ የሚያበረታቱ እና የነገውን ጀግኖች የሚቀርጹ ልዩ ልዩ ክንውኖችም ይኖራሉ። በእለቱ ከማለዳው 12 ሰዓት ላይ በሁሉም የመንግስትና የግል ተቋማት እንዲሁም በኤምባሲዎች የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የመስቀልና ብሄራዊ መዝሙር የመዘመር ስነ-ስርዓት በታላቅ ስነስርዓት ይካሄዳል።

✅ጳጉሜን 4 “የህብር ቀን”፣ የኢትዮጵያ ጌጥ የሆነው ብዝሃነት ጎልቶ የሚወጣበትና የሚከበርበት ቀን ነው፡፡ በመካከላችን የሚፈጠሩ ልዩነቶችን ሁልጊዜም በውይይትና በምክክር ለመፍታት ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷልና፤ እለቱ የምክክርና የትብብር እሴቶችን በሚያጎለብቱ ተግባራት ይከበራል።

በእለቱ ነፃ የጤና ምርመራና ህክምና፣ የደም ልገሳ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፣ ማዕድ ማጋራት እና የእግር ጉዞ መርሃግብሮች ይኖራሉ።

✅ጳጉሜን 5 “የነገ ቀን” በሚል ስያሜ፣ ነገን ዛሬ ላይ የመገንባት እሳቤ የሚጎላበት ቀን ነው። በዲጂታል ኢኮኖሚ፣ በመረጃ ሉአላዊነት፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ በወጣቶች የክህሎት ልማት እና በዲጂታላይዜሽን ላይ ትኩረት በማድረግ ይከበራል፣ ይህም የሀገራችንን የወደፊት ብሩህ ተስፋ ያሳያል።


የመስቃን ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በዝናብ እጥረት ምክንያት እየተከሰተ ያለውን የሰብል ጉዳት ለመከላከል አርሶ አደሩ አስፈላጊውን የቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርግ እየተደረገ ያለው ንቅናቄ በዛሬው ዕ...
01/09/2026

የመስቃን ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በዝናብ እጥረት ምክንያት እየተከሰተ ያለውን የሰብል ጉዳት ለመከላከል አርሶ አደሩ አስፈላጊውን የቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርግ እየተደረገ ያለው ንቅናቄ በዛሬው ዕለት በሁሉም የወረዳው ቀበሌዎች ተጠናክሮ ቀጥሏል።
==================
ነሐሰ 26/2018/የመስቃን ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኤክስቴንሽን ኮሚኒኬሽን)

በዝናብ እጥረት ምክንያት በቀጣይ የምርት እጥረት እንዳኖርና የሚጎዳውን ሰብል ሁሉም ባለሙያ ቀጠና በመከፍፈል ያለምንም መዘናጋት አርሶ አደሩ በእጁ ያለውን ሞተር ፓምፕ በመጠቀም ሰብሉን ውሃ የማጠጣት ተግባር መደገፍ ማገዝ ይኖርበታል ተብሏል።

የዝናብ እጥረት መኖሩን ተረድተው አስቀድመው ሰብልን ውሃ ማጠጣት የጀመሩ አርሶ አደሮች ቢኖሩም አሁን ችግሩ እጅግ አሳሳቢ በመሆኑ ሁሉም አመራር ባለሙያ በቅንጅት ተግባሩ በአጭር ጊዜ እንዲፈፀም ማድረግ ያስፈልጋል።

ዘገባው:-የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ነው።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማት አገልግሎት እና የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት  በተከናወኑ ስራዎች ውጤት ተመዝግቧል :- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ (ሆሳዕና...
01/09/2026

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማት አገልግሎት እና የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ስራዎች ውጤት ተመዝግቧል :- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ

(ሆሳዕና ፣ነሐሴ 26/2018)"ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ሀሳብ በወልቂጤ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የጤና ሴክተር ጉባኤ ተጠናቋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ እንደገለጹት በክልሉ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትን እና ተደራሽነትን ለማሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማት አገልግሎት እና የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ስራዎች ውጤት መመዝገቡን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በጤና ተቋማት ቀልጣፋ፣ውጤታማ እንዲሁም ጥራት ያለው አገልግሎት ከመስጠት አንጻር በሚፈለገው ደረጃ አለመሆኑን አቶ አንተነህ አንስተዋል።

የጤና ተቋማት የህብረተሰቡን እርካታ መሰረት አድርገው መስራት እንዳለባቸውም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

በክልሉ ሞዴል ወረዳዎችን ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በክልሉ በዲጂታል መድሀኒት ቤቶች አገልግሎት ላይ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው ስራ ውጤታማ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

የነፍሰ ጡር እናቶች እና የህጻናት ማቆያ ማዕከላትን በማቋቋም ረገድ መሰረታዊ ለውጥ ስለመኖሩም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል።

በክልሉ በ54 ጤና ጣቢያዎች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን የአልትራ ሳውንድ አቅርቦት ላይ የተጀመረውን ጥረት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

ክልሉ ሲመሰረት ተቀዛቅዞ የነበረው የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም በአዲስ መልክ ማነቃቃት መቻሉን ጠቁመዋል።

የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ የማድረግ ጥረት፣የመጸዳጃ ቤቶች ግንባታ እና አጠቃቀም፣የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥር እና ህክምና ላይ ለውጥ መኖሩን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በክልሉ የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ካለው የላቀ ጠቀሜታ አንጻር በዘርፉ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አቶ አንተነህ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የጤና አገልግሎትን በማሻሻል የእናቶችን እና የህጻናትን ሞት መቀነስ ስለመቻሉም አመላክተዋል።

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የተናገሩት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን አስቀድሞ ለመከላከል የጤና ተቋማት በትኩረት መስራት አለባቸው ብለዋል።

የግብአት አስተዳደር እንዲሁም የመድሀኒት አቅርቦት ስራ ውጤታማ እንዲሆን መስራት እንደሚገባም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

ተላላፊ በሽታዎችን በቅድመ መከላከል ስራ ምላሽ መስጠት እንደሚገባም ጠቅሰዋል።

ህብረተሰቡን በማሳተፍ የሀብት አሰባሰብ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ያሉት አቶ አንተነህ በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራት ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ወደ ሚፈለገው ደረጃ ለማድረስ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እንደሚገባም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንደገለጹት በጤናው ዘርፍ እየተሰጠ ያለውን አገልግሎት በማሻሻል ለዘርፉ እድገት በትኩረት መስራት ተገቢ ነው ብለዋል።

በጤና ተቋማት የመድሀኒት እና የግብአት አቅርቦትን በማሻሻል ረገድ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቶ ሳሙኤል ጠቁመዋል።

በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል ለባለሙያዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠር ተገቢ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በክልሉ በአንድ አንድ አካባቢዎች የጤና ተቋማትን ደረጃ ማሻሻል ላይ ፍላጎት መኖሩን የጠቆሙት ኃላፊው ዘርፉ በቂ የፋይናንስ እና የሰው ሀይል የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በጥንቃቄ ሊመራ ይገባል ብለዋል።

በዋናነት በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራት እና የህዝብ እርካታ ማረጋገጥ ተገቢ መሆኑን አቶ ሳሙኤል አስታውቀዋል።

ከተማ አስተዳደሮች በጤናው ዘርፍ የተሻለ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የመሰረተ ልማት አቅርቦት ላይ እየሰሩ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

በክልሉ በ2019 በጀት ዓመት በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት በውጤታማነት ለማሻሻል የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ኃላፊው ጠቁመዋል።

በጉባኤው በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ሲል መረጃው ያደረሰን የማ/ኢ/ክ/መ/ኮ/ጉ/ቢሮ ነው።

በዓድዋ ፋይት ናይት ብቃቷን ላሳየችው ያብስራ ወንድሙ በቡታጅራ ከተማ አቀባበል ተደረገላት።በETFC ዓድዋ ፋይት ናይት በሞንታይ ከተማዋን በጥሩ ስፖርታዊ ጨዋነት በማስተዋወቅ ጭምር አስደናቂ ...
01/09/2026

በዓድዋ ፋይት ናይት ብቃቷን ላሳየችው ያብስራ ወንድሙ በቡታጅራ ከተማ አቀባበል ተደረገላት።

በETFC ዓድዋ ፋይት ናይት በሞንታይ ከተማዋን በጥሩ ስፖርታዊ ጨዋነት በማስተዋወቅ ጭምር አስደናቂ ብቃቷን ላሳየችው ስፖርተኛ ያብስራ (ያቡ) ወንድሙ በከተማ አስተዳደሩ፣በስፖርተኞች፣ በአድናቂዎቿና ደጋፊዎቿ በቡታጅራ ከተማ አቀባበል ተደረገላት።

ነሐሴ 21/2018 በተካሄደው ዓድዋ ፋይት ናይት በሞንታይ ውድድር ስፖርታዊ ብቃትና ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ ውድድሩን ላደረገቸው ወጣቷ ስፖርተኛ የከተማው የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ስፖርተኞች ፣አድናቂዎቿና ደጋፊዎቿ ደማቅ አቀባበል አድርገውላታል።

መረጃው፦ የቡታጅራ ከ/መ/ኮ/ ነው

የመስቃን ወረዳ ሳይናስና እንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ለመምህራንና ከወረዳው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ባለሞያውች መሰረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው ዕለት አስመርቋል። ...
01/09/2026

የመስቃን ወረዳ ሳይናስና እንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ለመምህራንና ከወረዳው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ባለሞያውች መሰረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
=================
ነሃሴ_26/2018 ዓም (የመስቃን ወረዳ የመንግስት ኮሙንኬሽን)

የመስቃን ወረዳ ሳይናስና እንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ለመምህራንና ከወረዳው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ባለሞያዎች መሰረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ያስመረቀ ሲሆን በምርቃቱም የወረዳው አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሃመድ ውልጫፎ እና የመስቃን ወረዳ ረዳት የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የፖለቲካ እና የማስፈጸም አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንዴ ነሲቡ፣ የመስቃን ወረዳ ረዳት የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተሾመ አርጋው ፤የመስቃን ወረዳ ሳይናስና እንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ አይሻ ከድር ሌሎችም አመራርና የጽ/ቤቱ ባለሞያዎችና ከሴክተር የተውጣጡ ተመራቂዎች ተገኝተውበታል።

በዕለቱም የተገኙት የመስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ መሃመድ ውልጫፎ ስልጠናው በኮንፒውተር ሳይንስ ክህሎት የዳበረ የሰው ሃይል ማፍራት ለፈጣን እና ቀልጣፋ የስራ እንቅስቃሴ ሊያበቃ የሚችል ዘርፈ ብዙ ወረዳዊ ችግሮችን በቀላሉ እንዲፈታ እና ያለ አግባብ የወጪ ብክነትን መከላከል የሚቻልበትን ስርዓት እንዲኖር ያደርጋል ያሉ ሲሆን

ተመራቂዎች የኮምፒውተር ክህሎቶች በመጠቀም ዘመናዊ እና ወጪ ቆጣቢ አሰራሮችን በመከትል ወደ ትግባር ማዋል ብሎም የአገልግሎት ተጠቃሚ የሆነውን ማህበረሰባችንን ከተለያዩ እንግልቶች ነጻ የሚሆንበት አሰራር መከተል ያስፈልጋል ብለዋል።

የመስቃን ወረዳ ሳይናስና እንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ አይሻ ከድር በበኩላቸው እንደገለፁት ስልጠናው ሁሉም ባለሞያ መሰልጠን ቢችል እራሱን በዚህ ዘርፍ በማብቃት ተጠቃሚ የሚሆንበት እንደሆነ ጠቅሰው ካለው የኮንፒውተር ውስንነት አንጻር በፈረቃ እየተሰጠ ይገኛል ሆኖም ለሁሉም የወረዳው ባለሞያና አመራር እንደሚሰጥና ቀጣይነት ያለው መሆኑን ገልፀዋል።

ስልጠናው ቀደም ተብሎ በተደረገው የዳሰሳ ጥናት መሰረት በየጊዜው በሚያጋጥሙ ችግሮችና ክፈተቶች ለመቅረፍ የሚቻልበትን የክህሎት ብቃት እንዲኖር በማድረግ የበቁ ሰልጣኝ ባለሞያዎች ማፍራትና የመፍትሄ አካል ለማድረግ የሚያስችል ሲሆን

ስልጠናው በዋናነት ትኩረት ተደርጎ ሲሰጥ የነበረው፦
1. አጠቃላይ ስለ ኮምፒውተር ግንዛቤ
2 . ሚይክሮሶፍት የወርድ አጠቃቀም
3. ማይክሮሶፍት ዊንዶው
4. ማይክሮሶፍት excel አጠቃቀም
5.ማይክሮሶፍት ፓወር ፖይንት አዘገጃጀት ና
6. ማይክሮሶፍት ፐብሊሸር
ቀለል ያሉ በየጊዜው የሚያጋጥሙ ብልሽቶች ላይ የሜንቴናንስ ስልጠናን አካቶ ተሰጥቷል።

ስልጠናው ለተከታታይ ለ21የስራ ቀናት የቆየ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን
መምህራንና የሴክተር ባለሞያዎች ሰልጣኞችን በዛሬው ዕለት የእውቅና ና ሰርተፍኬት እንዲሁም ማበረታቻዎችን በስጦታነት ተበርክቷል።

የስልጠናው ዋና አላማው አጠቃላይ በመንግስታዊ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ በሚኖሩ የክህሎት እና ግንዛቤ እጥረቶችን ለመቅረፍ ብሎም በተሻለ አሰራር ውጤታማና የዘመነ አስራር እንዲኖር ስለሚያስችል እንደሆነ ጠቁመውናል።

እንዲሁም ኤሌክትሮኒክስ መገልገያ ከሆኑና አዳዲስ በመጡ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን እንዴት በቀላሉ መገልገል እንዲቻል ማድረግና የመገለገያ እቃዎች ብልሽት እንዳይኖር ያስችላል ብለዋል።

=================
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን!!
በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
👉ፌስቡክ-https://www.facebook.com/gzmwgcao?mibextid=ZbWKwL
👉ቴሌግራም-https://t.me/meskanweredacom31
👉ዩቲዩብ-https://www.youtube.com/channel/UC6PBsPYR5dltyXhEJchdlaA
👉ቲክቶክ -tiktok.com/.woreda.gov
👉ትዊተር-90ijTxwVTG6dwoT
👉ኢሜል[email protected]

የጤናው ሴክተር በክልሉ የልማት ስትራቴጂ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ነው:- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ (ሆሳዕና ፣ነሐሴ 26/2018)"ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎ...
01/09/2026

የጤናው ሴክተር በክልሉ የልማት ስትራቴጂ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ነው:- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ

(ሆሳዕና ፣ነሐሴ 26/2018)"ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ሀሳብ በወልቂጤ ከተማ የጤና ሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ እንደገለጹት ጤና የእድገታችን ፣የብልጽግናችን እና የማህበራዊ እድገታችን መሰረት ነው ብለዋል።

ጤናማ ህብረተሰብ መገንባት የጠንካራ ኢኮኖሚ፣ጥራት ያለው ትምህርት፣የተረጋጋ ማህበራዊ ህይወት ፣ጤናማና አምራች ዜጋ እንዲሁም ጠንካራ ሀገር መፍጠር ያስችላል ሲሉም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የጤናው ሴክተር በክልሉ የልማት ስትራቴጂ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ተቋም ስለመሆኑም አቶ አንተነህ ጠቁመዋል።

በጉባኤው ባለፈው አመት የታዩ መልካም ልምዶችን ለማስቀጠል፣በአፈጻጸም ረገድ የተስተዋሉ ውስንነቶችን ለማረም እና ቀጣይ የትኩረት መስኮች ላይ አቅጣጫ ማስቀመጥ የሚያስችል መድረክ መሆኑን አመላክተዋል።

በክልሉ ባለፉት ሶስት ዓመታት የጤና ተቋማትን ተደራሽነት እና የአገልግሎት ጥራት ለማሻሻል የእናቶችን እና የህጻናትን ሞት ለመቀነስ ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

በዘርፉ የተመዘገበው ውጤት ቀጣይነት እንዲኖረው፣ ህብረተሰቡ የራሱን ጤና መጠበቅ እንዲችል የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ ላይ ትኩረት መደረጉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው አመላክተዋል።

በተለይም የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ በማድረግ ለህብረተሰቡ በቅርበት አገልግሎት እየተሰጠ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

በዚህም ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን የመከላከል እና የመቆጣጠር አቅም ለማሳደግ፣የህክምና ግብአቶችን እና መድሀኒቶችን ለማረጋገጥ ጥረት መደረጉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በክልሉ በጤና አገልግሎት ዘርፉ የህብረተሰቡን ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ለማሟላት አሁንም ቀሪ ስራዎች እንዳሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው በሀገሪቱ በጤናው ሴክተር በርካታ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በጤናው መስክ በመከላከል እና በህክምና ረገድ በተከናወኑ ስራዎች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው አብራርተዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንደገለጹት ክልሉ በይፋ ተመስርቶ ስራ ከጀመረ ወዲህ በጤናው ዘርፍ የህዝብ ተጠቃሚነት ማሳደግ በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ የቅድመ ዝግጅት ስራ በማጠናቀቅ የጤናውን ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ በንቅናቄ መምራት የሚያስችል ስርዓት በመዘርጋት ወደ ተግባር መገባቱን አመላክተዋል።

በንቅናቄው ጤና ኬላዎች፣ጤና ጣቢያዎች ሆስፒታሎች በየደረጃው የሚገኙ መዋቅሮች በባለቤትነት ዘርፉን የማይመሩበት አሰራር እንደነበር አቶ ሳሙኤል አስታውሰዋል።

በተለይ በጤና ኬላዎች የሚሰጠው አገልግሎት ከ25 በመቶ በላይ እንዳልነበርም ጠቅሰዋል።

በዘርፉ የሚስተዋለውን ችግር በጥናት በመለየት የንቅናቄ ስራው መጀመሩን ኃላፊው ጠቁመዋል።

በክልሉ በ2018 በጀት አመት በጤናው ዘርፍ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ ስለመቻሉም አቶ ሳሙኤል አብራርተዋል።

በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን፣በበሽታዎች ወረርሽኝ፣በጤና ኤክስቴንሽን እና በሌሎችም መስኮች የተጠናከረ የንቅናቄ ስራ ተግባራዊ መደረጉን ኃላፊው ተናግረዋል።

በጤናው ዘርፍ በሚያጋጥሙ ህገወጥ አሰራሮች ላይ የተጠናከረ የቁጥጥር ስራ ተግባራዊ መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው በተለይ የግሉ ዘርፍ የጤና ተቋማት በባለቤትነት እንዲሰራ መደረጉን አስታውሰዋል ሲል መረጃው ያደረሰን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ነው።

Address

ምስራቅ ጉራጌ ዞን/መስቃን ወረዳ/ቡታጅራ
Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት:

Shortcuts

Share