የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ, Government Organization, Butajira city, Butajira.

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የግብር ሕግ ማስከበር ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል።ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተጀመረው የግብር ሕግ ማስከበር ሥራ በጉራጌ ...
04/09/2026

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የግብር ሕግ ማስከበር ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል።

ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተጀመረው የግብር ሕግ ማስከበር ሥራ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል።

በሕግ ማስከበር ሥራው በተለይም የደረሰኝ አጠቃቀምና አሰጣጥ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ሲሆን፣ የግብር ሕግና ደንብን ተከትለው የማይሠሩ ተቋማትና ድርጅቶች ላይም ተገቢው አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ ነው።

የደረሰኝ ሕግን መጣስ፣ግብርን ለመሰወር የሚደረጉ ሕገወጥ ተግባራትና ሌሎች የግብር ሕግ ጥሰቶች በቸልታ እንደማይታዩ በማስገንዘብ፣ የቁጥጥርና የሕግ ማስከበር ሥራው በተጠናከረ መልኩ በዞኑ ወልቂጤ ከተማ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ይህ ጥብቅ የሕግ ማስከበር አቅጣጫ ሁሉም ግብር ከፋይ ሕጋዊ ግዴታውን በወቅቱና በትክክል እንዲወጣ፣ ፍትሐዊ የግብር ሥርዓት እንዲጠናከር እና የገቢ መሰረቱ እንዲሰፋ የሚያግዝ እንደሆነ ተገልጿል

በተጨማሪም በነሐሴ ወር የታቀደውን የገቢ ግብ በሙሉ ለማሳካት፣ የገቢ አሰባሰብን ለማሳደግና የገቢ ክፍተትን ለማስቀረት የደረሰኝ ቁጥጥር፣ የግብር ሕግ ማስከበርና የግብር ከፋይ ክትትል ሥራዎች በቅንጅትና በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል።

በክልሉ በሳምንቱ መጀመሪያ ቀናት ጀምሮ በግብር ህግ ማስከበር ላይ የተጀመረው ተግባር በሁሉም የገቢ መዋቅሮች ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ቀጣይም በተጠናከረ መልኩ እንደሚሠራበት ተገልጿል።

👇👇👇👇👇
👉የፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61562204634443
👉የቲክቶክ ገፅ
https://www.tiktok.com/.ethiopia4?_t=ZM-8ynTRPSsANR&_r=1
👉የዩቲዩብ ገፅ (https://youtube.com/?si=ELneJRp2Lj7xJ8GK
👉ኢንስታገራም
https://www.instagram.com/centralethiopiarevenue?igsh=cmY4a2g5dnAxcmQ3

👉በሬዲዮ ፕሮግራም በDebub Fm100.9 ሬዲዮ በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ8:40_9:00 ይከታተሉን
👉 ይደውሉ
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ አስመልክቶ የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን እና የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ለእይታ ክፍት አደረጉ ዘላቂ የትምህር...
04/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ አስመልክቶ የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን እና የፎቶ አውደ ርዕይ መርቀው ለእይታ ክፍት አደረጉ

ዘላቂ የትምህርት ጥራት ለላቀ የመማር ውጤት እና ብልጽግና በሚል መሪ ሀሳብ 3ኛው የትምህርት ሴክተር ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።

በኤግዚቢሽኑ ልዩ ልዩ የፈጠራ ስራዎች ቀርበው ለእይታ ክፍት የተደረጉ ሲሆን የክልሉ ትምህርት ቢሮ በ2018 በጀት አመት ያከናወናቸውን ስራዎች የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ ርዕይ ቀርቧል።

ግብይትን በደረሰኝ የምናካሂደው ለምንድነው ?ማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ለገዛው ዕቃ ወይም አገልግሎት ለሚከፍለው ገንዘብ ደረሰኝ መጠየቅ አለበት፡፡ ለዚህም ደግሞ የተለያዩ ጠቃሚ ምክንያቶች ...
04/09/2026

ግብይትን በደረሰኝ የምናካሂደው ለምንድነው ?

ማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ለገዛው ዕቃ ወይም አገልግሎት ለሚከፍለው ገንዘብ ደረሰኝ መጠየቅ አለበት፡፡

ለዚህም ደግሞ የተለያዩ ጠቃሚ ምክንያቶች አሉ።

በግብይት ወቅት ደረሰኝ መቀበል ግዢ በትክክል መፈጸሙን ያሳያል። የከፈሉት ገንዘብ እና የገዙት ዕቃ ወይም የአገልግሎት አይነት በደረሰኙ ላይ በግልጽ ሰፍሮ ስለሚገኝ ግብይቱ ግልጽ እና ህጋዊ እንዲሆን ያደርጋል።

ከገዙ በኋላ ዕቃው ላይ ችግር ቢያጋጥም ወይም ዕቃውን ለመመለስ ቢፈልጉ ፣ ደረሰኝ እንደማስረጃ ሆኖ ያገለግላል። ደረሰኝ ከሌለ የገዙትን ዕቃ ለመመለስ ወይም ለማስቀየር ችግር ይገጥሞታል።

ደረሰኝ ጠይቆ መቀበል ሕጋዊና ስልጡን የንግድ ስርዓት መኖሩን ያመላክታል። ደረሰኝ ሲቀበሉ፣ ገቢዎች በትክክል ይመዘግባሉ። መንግስትም ትክክለኛውን የግብር ገቢ ያገኛል፡፡ የሚሰበሰበውም ግብር ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ መሰረተ ልማቶችን ማለትም መንገድ ፣ ትምህርት ቤት እና ሆስፒታሎችን ወዘተ. ለመገንባት እና ለማሻሻል ያግዛል።

ግብይቶች ያለደረሰኝ ሲካሄዱ፤ የዋጋ ጭማሪ ሊደረግ ይችላል። ደረሰኝ መቀበል አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ ለመቆጣጠር ይረዳል፡፡

በአጠቃላይ ፣ ግብይቶችን በደረሰኝ ማካሄድ በግል ከምናገኘው ጥቅም ባሻገር የሀገርን የገቢ አሰባሰብ፣ የንግድ ስርአት እና ኢኮኖሚን ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

የክልሉ መንግስት በገጠር እና በከተሞች የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ሁሉን አቀፍ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ ...
03/09/2026

የክልሉ መንግስት በገጠር እና በከተሞች የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ሁሉን አቀፍ ስራዎች ተጠናክረው
እንደሚቀጥሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ

(ነሐሴ 28/2018)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ የዘንድሮውን የጳጉሜ ቀናት አስመልክቶ በጽ/ቤታቸው መግለጫ ሰጥተዋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ የዘንድሮውን የጳጉሜ ቀናት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ድሎችን አስመዝግባለች ብለዋል፡፡

በሂደት ያጋጠሙ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለማቀፋዊ ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር በጽናት እየተሻገረች ስለመምጣቷም ኃላፊው አስታውቀዋል፡፡

ሀገራችን በአሁኑ ወቅት ሁለንተናዊ ለውጦችን በማስመዝገብ በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ መሆኗን አቶ ዘሪሁን አብራርተዋል።

በሌላ በኩል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ 3ኛ አመቱን ማስቆጠሩን የገለጹት ኃላፊው በነዚህ አመታት በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች ለቀጣይ ስራ መነቃቃት መፍጠሩን አስረድተዋል።

ያለፉት ዓመታት ጉዞ ድልም ፈተናም እንደነበረው የገለጹት ኃላፊው ተግዳሮቶችን በጽናት በመሻገር ረገድ የክልሉ መንግስት የነበረው ቁርጠኝነት የላቀ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በየዓመቱ የጳጉሜ ቀናትን ለውጡንና የለውጡን ትሩፋቶች በሚያመላክቱ ስያሜዎች እና መሪ ሐሳቦች የግንዛቤ ፈጠራ ንቅናቄዎች ሲሠሩ መቆየቱን አቶ ዘሪሁን ጠቅሰዋል፡፡

በክልሉ በሁሉም መስክ የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች የላቀ ውጤት መመዝገቡን አቶ ዘሪሁን በመግለጫቸው አብራርተዋል።

የክልሉ መንግስት በገጠር እና በከተማ የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸው ሁለንተናዊ የልማት እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ኃላፊው በመግለጫቸው ጠቅሰዋል።

በዋናነት በምግብ ዋስትና፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በመሰረተ ልማት በማህበራዊ አገልግሎቶች እና በሌሎችም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ ለማስመዝገብ እንደሚሰራም አብራርተዋል።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር ውስጥ ወደ ዓዲሱ ዓመት የምንሸጋገርበት ድልድይ ነው ሲሉም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

የጳጉሜን ወር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ አንኳር ስኬቶችን የምንመዝንበትና ከወረቶቻችን ጋር የምንደምርበት፣ ድክመቶችን የምንገመግምበት እና ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ ዐዲስ ተስፋን የምንሰንቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው ብለዋል።

የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ ሀገራችን የምትገኝበትን ታሪካዊና ፖለቲካዊ ሁኔታዎች ታሳቢ ያደረገ ስለመሆኑም ኃላፊው በመግለጫቸው አብራርተዋል።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት የሚከበረው ሀገራችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ የሕዝብ ይሁንታ ያገኘው ፓርቲ መንግሥት የሚመሠርትበት፣ የተመረጠው መንግሥት ከሕዝብ የተጣለበትን ከፍተኛ ኃላፊነትና አደራ ለመወጣት በሚዘጋጅበት ወቅት መሆኑ የተለየ ያደርገዋል ብለዋል።

መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር እየተካሄደ ያለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ውጤቶችን ወደ ትግበራ ለማስገባት ጠንካራ ዝግጅት መደረግ ባለበት ታሪካዊ ወቅት መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር በዋናነት በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ያተኮረ ይሆናል ብለዋል።

የጳጒሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል የጋራ መሪ መልእክት ይከበራሉ ሲሉም ኃላፊው ጠቁመዋል።
ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፣
ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን፣
ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን፣
ጳጉሜን 4- የኅብር ቀን እና
ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን በሚሉ ስያሜዎች እንደ ቅደም ተከተላቸዉ በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበሩ አቶ ዘሪሁን በመግለጫቸው አመላክተዋል።

በሆሳዕና ከተማ ከሚገኙ በእህል ንግድ ስራ ከተሰማሩ ነጋዴዎች ጋር ከግብር አከፋፈል እና ውሳኔ ጋር ተያይዞ ውይይት ተደረገ (ነሐሴ 28/2018 ) የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት እና  ንግድ...
03/09/2026

በሆሳዕና ከተማ ከሚገኙ በእህል ንግድ ስራ ከተሰማሩ ነጋዴዎች ጋር ከግብር አከፋፈል እና ውሳኔ ጋር ተያይዞ ውይይት ተደረገ

(ነሐሴ 28/2018 ) የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት እና ንግድ ልማት ጽ/ቤት በጋራ በመሆን በእህል ንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮችን በግብር አወሳሰን ዙሪያ ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን ውድነህ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አውላቸው ዮሐንስ እና የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ንግድ ገበያ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አይናለም ይርዳው ወይይቱን መርተውታል ።

በውይይቱ ላይ ግብር ከፋዮች በግብር ውሳኔው ላይ ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን በውይይቱ የተገኙ የማዕከላዊ ኢት/ያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሰለሞን ውድነህ ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ የሰጡ ሲሆን በ2018 የግብር ዘመን የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች የግብር ውሳኔ የተሻሻለውን የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 39/2018 እና በአዋጁ መሠረት በተዘጋጀው የዋጋ ግሽበት ማስተካከያ ሰነድ መሠረት መሆኑን አብራርተዋል።

እንዲሁም በ2015 በተካሄደው የቀን ገቢ ግመታ መረጃ እና በ2018 በወጣው አዋጅ ቁጥር 39/2018 አንቀጽ 14 መሠረት፣ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ጠቅላላ ሽያጭ በሚወድቅበት የገቢ ማዕቀፍ መሠረት ከ2 እስከ 9 በመቶ የሚደርስ ግብር መወሰኑን ገልጸዋል።

በተለይም በእህል ንግድ ዘርፍ የሚሰሩ ነጋዴዎች በቀደሙት ዓመታት የሚከፍሉት ግብር ከአሁኑ የግብር አወሳሰን ጋር ሊለያይ እንደሚችል ጠቁመው፣ የተሻሻለው የገቢ ግብር ሕግ ተግባራዊ መደረጉ ለውጡን ያመጣ መሆኑን አስረድተዋል።

የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አውላቸው ዮሐንስ በበኩላቸው፣ በከተማው የግብር አወሳሰንና አከፋፈል ሥራ በሕግ፣ በመመሪያና በተቀመጠው አሠራር መሠረት መከናወኑን ገልጸው፣ ግብራቸውን ያልከፈሉ ግብር ከፋዮች ተጨማሪ ቅጣትና ወለድ እንዳይጨምርባቸው በጊዜ እንዲከፍሉ አሳስበዋል።

በመጨረሻም፣ በውይይቱ ለተነሱ ጥያቄዎች በቂ ማብራሪያ እና ምላሽ በመስጠት የዕለቱ ስብሰባ ተጠናቋል።

የሆሳዕና ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት

የግብር ከፋዮችን ግንዛቤ በየደረጃው ማጠናከር ለታክስ ህግ ተገዥነት መሻሻል ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ(ነሐሴ 28/2018) አዲሱን የፌዴራል የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 መነሻ በ...
03/09/2026

የግብር ከፋዮችን ግንዛቤ በየደረጃው ማጠናከር ለታክስ ህግ ተገዥነት መሻሻል ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ

(ነሐሴ 28/2018) አዲሱን የፌዴራል የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 መነሻ በማድረግ፣ የታክስ ሕግ ተገዥነትን ለማሻሻል በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማና መስቃን ወረዳ ለሚገኙ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ገቢዎች ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ እንደተናገሩት የውስጥ አቅም በመገንባት የህዝቦች እድገትና ለውጥ ለማሳደግ ግብር ዋንኛ መሠረት ነው ብለዋል።

ግብር ከፋዮች በአዋጁ የተጠቀሱ ህጎችን ምንነት በጥልቀት በመረዳት የሚጠበቅባቸውን የግብር ግዴታ በጊዜና በታማኝነት በወቅቱ መወጣት ይጠቀቃል ብለዋል።

በተለይም ከገቢ ተቋማት ጋር የቅርብ ግንኘነትን መፍጠር ፣ብልሹ አሰራርን በጋራ መከላከል ላይ የነቃ ተሳትፎን ከማጠናከርም ባለፈ በአዋጁ የተጠቀሱ ሕጎችን በጥልቀት መረዳት ለአሰራር ቅልጥፍናና ለጋራ ውጤት መሳካት መሠረት በመሆኑ ቀጣይ በነዚህ ተግባራት ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።

ግብር ከፋዩ በቅንነትና በታማኝነት ከመንግስት የተሰጡ ኃላፊነቶችን በአገልጋይነት መንፈስ መወጣት እንደሚጠበቅ ገልፀዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ይሽልጌታ በላይነህ እንደገለጹት፣ የዞኑን ገቢ ለማሳደግ የግብር ከፋዮች የታክስ ሕግ ተገዥነትን ማጠናከር እና ትክክለኛና ሙሉ የግብር ገቢ እንዲመዘገብ የቁጥጥርና ክትትል ሥራን ማጠናከር ዋና ትኩረቶች ናቸው።

የግብር ከፋዮች ሕጋዊ ግዴታቸውን በተገቢው እንዲወጡና የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የግንዛቤ ስልጠናው ጉልህ ሚና እንዳለውም አቶ ይሽልጌታ ጠቁመዋል።

በመርሃ ግብሩ የቡታጅራ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወልዩ ከበደ እንደገለጹት፣ የከተማዋን ገቢ ለማሳደግ ግብር ከፋዮች የተደነገገውን የአሠራር ሥርዓት በመከተል ግዴታቸውን በወቅቱና በትክክል መወጣት ይገባቸዋል።

በተለይም ግብርን በወቅቱ መክፈልና በእያንዳንዱ ግብይት ደረሰኝ መስጠት የግብር ከፋዮች ግዴታ መሆኑን ጠቅሰው፣ ሕግና አሠራርን በማይከተሉ እና ደረሰኝ በማይሰጡ ግብር ከፋዮች ላይ ተገቢው ቁጥጥርና የሕግ ማስከበር ስራ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

ግብር ግዴታ ብቻ ሳይሆን የከተማችን የልማት መሠረት ነው፤ ግዴታችንን በመወጣት የዞኑን ብሎም የቡታጅራ የከተማችንን ልማት ልናፋጥን ይገባል ያሉት በግንዛቤ ማስጨበጫው የተሳተፉ የደረጃ "ሀ" ግብር ከፋዮች ገልፀዋል።

‎ህገወጥ የንግድ ስርአት መከላከል ከንግድ ፍቃድ፣ደረሰኝ መስጠት እንዲሁም በተመሳሳይ ዘርፍና አቅርቦት ላይ የደረጃ አስመልክቶ የሚስተዋለው ውስንነት ከመንግሥት ጋር ተቀራርቦ መስራት ይገባል ብለዋል።

‎የስልጠናና የግንዛቤ ስራዎች በስፋት መስራት ይገባል ያሉት ተሳታፊዎች ህግና አሰራር በመትከል በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የሚሳተፉ አካላት ላይ ተጠያቂነት በማስፈን ለጋራ ለዞናችን ብሎም ለከተማችን የልማት እድገት የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ አስታየታቸውን ሰጥተዋል ።

‎በመጨረሻም የታክስ የህግ ተገዢነት በማረጋገጥ የ2019 በጀት ዓመት በዞኑና በቡታጅራ ከተማ የገቢ ስራን በማሳካት የሚጠበቀው ውጤት እንዲመጣ በቅንጅት መስራት እደሚጠበቅ ተገልጿል ።

‎ 👇👇👇👇👇
👉የፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61562204634443
👉የቲክቶክ ገፅ
https://www.tiktok.com/.ethiopia4?_t=ZM-8ynTRPSsANR&_r=1
👉የዩቲዩብ ገፅ (https://youtube.com/?si=ELneJRp2Lj7xJ8GK
👉ኢንስታገራም
https://www.instagram.com/centralethiopiarevenue?igsh=cmY4a2g5dnAxcmQ3

👉በሬዲዮ ፕሮግራም በDebub Fm100.9 ሬዲዮ በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ8:40_9:00 ይከታተሉን
👉 ይደውሉ
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያን ለማስተካከል የሚያስችሉ ምክንያቶች(ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም )በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 96 መሰረት በታክስ ውሳኔ ...
03/09/2026

የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያን ለማስተካከል የሚያስችሉ ምክንያቶች

(ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም )በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 96 መሰረት በታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ላይ ማስተካከያ ሊደረግ የሚችለው፦

👉 የስሌት ወይም የሂሳብ ስህተት ያለ ከሆነ፤
👉 በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልታየ አግባብነት ያለው ማስረጃ ወይም በዚህ አዋጅ መሰረት የቀረበ አዲስ ማስረጃ ያለ እንደሆነ፤
👉 የታክስ ውሳኔው አስገዳጅ ከሆነው የታክስ ህጎች ትርጉም ጋር የማይጣጣም ከሆነ፤ ወይም
👉 ታክስ የመክፈል ግዴታን በመወሰን ረገድ የተሳሳተ ውጤት የሚያስከትል ሌላ ስህተት ካለ ነው፤

👉(የገቢዎች ሚኒስቴር)

የታክስ ሕግ ተገዥነትን ለማሻሻል በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማና መስቃን ወረዳ ለሚገኙ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው(ነሐሴ 28/2018) በ2019...
03/09/2026

የታክስ ሕግ ተገዥነትን ለማሻሻል በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማና መስቃን ወረዳ ለሚገኙ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው

(ነሐሴ 28/2018) በ2019 በጀት ዓመት አዲሱን የፌዴራል የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 መነሻ በማድረግ፣ የታክስ ሕግ ተገዥነትን ለማሻሻል በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማና መስቃን ወረዳ ለሚገኙ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

በስልጠናው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አሰፋ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ይሽልጌታ በላይነህ፣ የቡታጅራ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወልዩ ከበደ እና የንግዱ ማህበረሰ
ተገኝተዋ።

👇👇👇👇👇
👉የፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61562204634443
👉የቲክቶክ ገፅ
https://www.tiktok.com/.ethiopia4?_t=ZM-8ynTRPSsANR&_r=1
👉የዩቲዩብ ገፅ (https://youtube.com/?si=ELneJRp2Lj7xJ8GK
👉ኢንስታገራም
https://www.instagram.com/centralethiopiarevenue?igsh=cmY4a2g5dnAxcmQ3

👉በሬዲዮ ፕሮግራም በDebub Fm100.9 ሬዲዮ በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ8:40_9:00 ይከታተሉን
👉 ይደውሉ
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

የከተሜነት ምጣኔ መጨመር እና የከተሞችን እድገት ማሻሻል ላይ በትኩረት መስራት ይገባል:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) (ነሐሴ 28/2018)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀጣይ አ...
03/09/2026

የከተሜነት ምጣኔ መጨመር እና የከተሞችን እድገት ማሻሻል ላይ በትኩረት መስራት ይገባል:- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

(ነሐሴ 28/2018)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀጣይ አምስት ዓመታት የከተሞችን እድገት ማሻሻል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በክልሉ የከተሞች እድገት በቀጣይ ዓመታት እየተሻሻለ መምጣት እንዳለበት በሀገር አቀፍ ደረጃ የጋራ ተግባቦት መፈጠሩን ተናግረዋል።

የከተሜነት ምጣኔ መጨመር እና የከተሞችን እድገት ማሻሻል ተገቢ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

ከተሞች ለኑሮ፣ለንግድ እና ለኢንቬስትመንት ተመራጭ በማድረግ ሂደት ያልተሟሉ ጉዳዮች መኖራቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

ባለፉት ዓመታት ከተሞችን ለማሻሻል የተጀመሩ ስራዎች መኖራቸውን የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ ነገር ግን በሚፈለገው ደረጃ የተሟላ አለመሆኑን ጠቅሰዋል።

በክልሉ በቀጣዩ አምስት ዓመታት ሰባት ዋና ዋና ከተሞች ሊተገበሩ በታቀዱ ስራዎች ላይ የጋራ ተግባቦት መፍጠር አስፈላጊ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በሚቀጥሉት ዓምስት አመታት በከተሞች እድገት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት አስቀድሞ ማቀድ አስፈላጊ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በመድረኩ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች የአምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ አቅርበው ምክክር እንደሚካሄድበት ይጠበቃል።

👉የክ መ ኮ

የካፒታል ገቢ(ነሐሴ 28/2018)የካፒታልየካፒታል ገቢ (Capital Gains) ማለት አንድን ንብረት (እንደ ቤት፣ መሬት፣ ወይም የድርጅት ዕክሲዮን) ከገዙበት ዋጋ በላይ አትርፈው ሲሸጡ የ...
03/09/2026

የካፒታል ገቢ

(ነሐሴ 28/2018)
የካፒታልየካፒታል ገቢ (Capital Gains) ማለት አንድን ንብረት (እንደ ቤት፣ መሬት፣ ወይም የድርጅት ዕክሲዮን) ከገዙበት ዋጋ በላይ አትርፈው ሲሸጡ የሚያገኙት ገቢ ነው።
በኢትዮጵያ የግብር ሥርዓት መሠረት፣ ከካፒታል ገቢ ላይ የሚከፈል ግብር (Capital Gains Tax) አለ።
ዋና ዋና ነጥቦች
የግብር ተፈጻሚነት፦ ግብሩ የሚጣለው በቋሚ ንብረቶች (ሕንፃ እና መሬት) እንዲሁም በሕጋዊ ድርጅቶች ዕክሲዮን (Shares) ሽያጭ ላይ ነው።

የግብር መጠን፦ የግብር ምጣኔው እንደ ንብረቱ ዓይነት ይለያያል።

ትርፍ ማስላት፦ ግብሩ የሚታሰበው በሽያጭ ዋጋው ላይ ሳይሆን፣ ንብረቱ ከተገዛበት ዋጋ በላይ በተገኘው የተጣራ ትርፍ ላይ ብቻ ነው።

የግብር መጠኖች (የኢትዮጵያ የገቢ ግብር አዋጅ)
የድርጅት ዕክሲዮን (Shares)፦ ከዕክሲዮን ሽያጭ በሚገኝ የተጣራ ትርፍ ላይ 30% ግብር ይከፈላል።

ሕንፃ ወይም ቤት፦ ለንግድ ወይም ለመኖሪያ የሚሆን ሕንፃን በመሸጥ ከሚገኝ የተጣራ ትርፍ ላይ 15% ግብር ይከፈላል።
ከግብር ነፃ የሆኑ ሁኔታዎች

የመኖሪያ ቤት፦ ግለሰቡ ለረጅም ጊዜ የኖረበት ብቸኛ መኖሪያ ቤቱ ከሆነ በተወሰኑ ሁኔታዎች ከግብር ነፃ ሊሆን ይችላል።
ውርስ እና ስጦታ፦ ንብረቱ በውርስ ወይም በቅርብ የቤተሰብ ስጦታ የተገኘ ከሆነ የግብር አሰላሉ ልዩ ሁኔታዎች አሉት።

👇👇👇👇👇
👉የፌስቡክ ገፅ
https://www.facebook.com/profile.php?id=61562204634443
👉የቲክቶክ ገፅ
https://www.tiktok.com/.ethiopia4?_t=ZM-8ynTRPSsANR&_r=1
👉የዩቲዩብ ገፅ (https://youtube.com/?si=ELneJRp2Lj7xJ8GK
👉ኢንስታገራም
https://www.instagram.com/centralethiopiarevenue?igsh=cmY4a2g5dnAxcmQ3

👉በሬዲዮ ፕሮግራም በDebub Fm100.9 ሬዲዮ በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ8:40_9:00 ይከታተሉን
👉 ይደውሉ
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

Address

Butajira City
Butajira

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ገቢዎች ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share