23/07/2026
ለጡረታ ባለመብቶች በሙሉ!
የኢፌድሪ የመንግሥት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር፣ የ2019 በጀት ዓመት የጡረታ መታወቂያ ዕድሳት ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ መሆኑን ይገልጻል፡፡
ይህ ወሳኝ የዕድሳት አገልግሎት እስከ መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ብቻ የሚቆይ በመሆኑ፣ የተከበራችሁ የሀገር ባለውለታ የጡረታ ባለመብቶች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የአስተዳደሩ ጽሕፈት ቤቶች ወይም ጽ/ቤቶቹ በሚያዘጋጇቸው የዕድሳት ማዕከላት እና መርሃ ግብር መሠረት በአካል በመገኘት መታወቂያችሁን እንድታድሱ በአክብሮት እናሳስባለን።
ስለ ዕድሳቱ ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገዎት፣ በአስተዳደሩ የነፃ ስልክ መስመር 8926 ላይ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የመንግሥት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር!