PSSSA DAMBI DOLLO

PSSSA   DAMBI DOLLO FOR GOVERNMENT EMPLOYEE ,BY EMPLOYEE

23/07/2026

ለጡረታ ባለመብቶች በሙሉ!

የኢፌድሪ የመንግሥት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር፣ የ2019 በጀት ዓመት የጡረታ መታወቂያ ዕድሳት ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ መሆኑን ይገልጻል፡፡

ይህ ወሳኝ የዕድሳት አገልግሎት እስከ መስከረም 30 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ብቻ የሚቆይ በመሆኑ፣ የተከበራችሁ የሀገር ባለውለታ የጡረታ ባለመብቶች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የአስተዳደሩ ጽሕፈት ቤቶች ወይም ጽ/ቤቶቹ በሚያዘጋጇቸው የዕድሳት ማዕከላት እና መርሃ ግብር መሠረት በአካል በመገኘት መታወቂያችሁን እንድታድሱ በአክብሮት እናሳስባለን።

ስለ ዕድሳቱ ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገዎት፣ በአስተዳደሩ የነፃ ስልክ መስመር 8926 ላይ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

የመንግሥት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና አስተዳደር!

የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ2018 የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል/ገና/ በሠላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻ...
06/01/2026

የመንግስት ሠራተኞች ማኀበራዊ ዋስትና አስተዳደር ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ2018 የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል/ገና/ በሠላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡

አስተዳደሩ የመንግስት ሠራተኞችን የማህበራዊ ዋስትና ለማረጋገጥና ለጡረታ ባለመብቶችም የተሻለ የጡረታ አበል ለመክፈል አቅዶ በመስራት ላይ ይገኛል።

ይህንንም ለማሳካት አሠሪ መስሪያ ቤቶች የቋሚም ሆነ የጊዜያዊ ሠራተኞችን ማስረጃዎች በአግባቡ በማደራጀት እና የሚፈለገውን የጡረታ መዋጮም በወቅቱ ገቢ በማድረግ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

መልካም የገና በዓል ይሁንላችሁ!

ለዋስትናዎ እንተጋለን!
የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር

Address

Dambidolo
Dambidolo
DAMBIDOLO

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when PSSSA DAMBI DOLLO posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share