Dangila communication

Dangila  communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dangila communication, Government Organization, dangila, Dangila.

ይህ ይፋዊ የዳንግላ ወረዳ የፌስ ቡክ ገጽ ነው። በወረዳዉ ውስጥ ያሉ እምቅ ጸጋዎችን በማውጣት የማስተዋወቅ ስራ ይሰራል።በተለይም በማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በስፋት እየዘገበ ለወረዳው ብሎም ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ መረጃዎችን ያጋራል።

የዘንድሮው የ2018 ዓ/ም  #የጷጉሜ ወር 5 ቀናቶች በተለያዩ ዝግጅቶችና ሁነቶች ይከባራሉ።ነሀሴ 30/018(ዳንግላ ኮሚኒኬሽን) የዘንድሮው የ2018 ዓ/ም የጷጉሜ ወር 5 ቀናቶች በተለያዩ ...
05/09/2026

የዘንድሮው የ2018 ዓ/ም #የጷጉሜ ወር 5 ቀናቶች በተለያዩ ዝግጅቶችና ሁነቶች ይከባራሉ።

ነሀሴ 30/018(ዳንግላ ኮሚኒኬሽን)

የዘንድሮው የ2018 ዓ/ም የጷጉሜ ወር 5 ቀናቶች በተለያዩ ዝግጅቶችና ሁነቶች እንደሚከበሩ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳድር የዳንግላ ወረዳ የዝግጅቱ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታወቀ።

‎- ነሀሴ 30/018(ዳንግላ ኮሚኒኬሽን)

‎ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ እና የዝግጅቱ አስተባባሪ ኮሚቴ አቶ አለበል አባት እንደገለፁት የ2018 ዓመተ ምህረት የመጨረሻ ጳጉሜ ወር የብልጽግና መንግስት ያከናወናቸውን ፍሬያማ ስራዎችና ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች በተለያዩ ዝግጅቶች የምናስተውቅበት ነው ብለዋል።

‎መንግስት በሁሉም ዘርፍ ያስመዘገባቸውን በተለይም በስንዴ ምርት፣ በግብርና በሜካናይዜሽን፣ በአረጓዴ አሻራ እና በተለያዪ የመንግስት ኢኒሸቲቭ የልማት ስራዎችን ለማህበረሰቡ የምናስተዋውቅበት ነው ብለዋል።

‎በተለይም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፣ የመንግስት ሰራተኞችና አመራሩ ጋር በመሆን ጷጉሜ 01/13/018 ዓ/ም የምርታ ቀን፣ ጷጉሜ 02 የማንሰራራት ቀን፣ ጳጉሜ 03 የፅናት ቀን፣ ጳጉሜ 04 የህብር ቀን፣ ጷጉሜ 05 የነገ ቀን ተብለው በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳና ሰዓት በተለያዩ ዝግጅቶችና በፓናል ውይይት እንዲሁም ሁነቶች እንደሚከበሩ አቶ አለበል አስታውቀዋል።

‎በመጨረሻም መጪው የጳጉሜ ወር አምስት ቀናት ለመላው የዳንግላ ወረዳ ማህበረሰብ ጳጉሜን በአንድነት፣ በፍቅር በህትማማችነትና በወንድማማችነት እንዲያሳለፉ ምኞታቸውን ገልፀዋል።

በዳንግላ ወረዳ  በ2019 በጀት አመት  #ከ319ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገለጸ።ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም  ዳንግላ ኮሙኒኬሽን በአዊ ብሄረሰብ አስተዳድር የዳንግላ ወረዳ ገ...
04/09/2026

በዳንግላ ወረዳ በ2019 በጀት አመት #ከ319ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገለጸ።

ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም ዳንግላ ኮሙኒኬሽን

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳድር የዳንግላ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት አመት የእቅድ ትውውቅ መድረክ አካሂዷል።

በውይይት መድረኩ የጽ/ቤቱን የ2018 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ያቀረቡት የደንበኞች አገልግሎት ባለሙያ አቶ ደሳለው ታደሰ እንደገለጹት በ2018 በጀት አመት በወረዳው 149ሚሊዮን 238ሽ 773 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 200ሚሊየን 859ሽ 917 ብር የተሰበሰበ ሲሆን አፈጻጸሙም 196.28 ከመቶ ማከናወን ተችሏል።

ባለሙያው አክለውም ገቢው የተሰበሰበው ከገጠር መሬት እና ከእርሻ ስራ ገቢ ፣ ከንግዱ ማህበረሰብ ፣ ከመንግሰት እና ከግል ከተቀጣሪዎች ፣ ከሮያሊቲ እንዲሁም ከልዩ ልዩ ገቢዎች መሆኑን ጠቅሰዋል ።

የተሻለ ገቢ እንዲሰበሰብ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ቁርጠኝነት ፣የወረዳ አመራሮች ትጋት እና የአጋርና የባለድርሻ አካላት ርብርብ ከፍተኛ መሆኑን አቶ አቶ ደሳለው ገልጸዋል ።

የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ ቢሻው ዘነበ በበኩላቸው የ2019 አሻጋሪ እድገትና ዘላቂ ልማት እቅድ ለማሳካት በወረዳው ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን ሃብት አሟጦ በመጠቀም ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብ ስርዓት ለማከናወን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ስለሆነም በ2019 በጀት አመት ከተለያዩ የገቢ አርዕስቶች 319ሚሊየን 505ሽ 860ብር ገቢ ለመሰብሰብ የታቀደ መሆኑንም ገልጸዋል።

የወረዳውን ወጪ በወረዳው የታክስ ገቢ በመሸፈን የማህበረሰቡን የመልማት አቅም ለማሳደግ እንደሚሰራም ገልጸዋል።

ለገቢ አሰባሰቡ ተግዳሮት የሆኑትን የአቅም ውስንነት ፣ሌብነት ፣ የፍትሐዊነት ችግር፣የግብር ባህል ያለመዳበር፣የግብር ህግ ተገዥነት ዝቅተኛ መሆን፣ የመረጃ ስርዓት አለመኖር እና መሰል ችግሮችን ለመከላከል ከአጋር አካላት ጋር በጋራ ለመስራት መታቀዱን ገልጸዋል።

የዳንግላ ወረዳ ም/አስተዳዳሪ እና የንግድ እና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ የክቴ ፈጠነ እንዳሉት የወረዳውን ገቢ በአግባቡ ለመሰብሰብ በተለይም ከንግዱ ማህበረሰብ እና ከሮያሊቲ ገቢ በትኩረት መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

የወረዳውን ሀብት በአግባቡ አሟጦ ለመሰብሰብ ተቋሙ ብቻውን የሚያሳካው ጉዳይ ባለመሆኑ የጸጥታ አካላት እና ሌሎች አጋር አካላት የጋራ ቅንጅትእጅግ አስፈላጊ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የተሻለ አፈጻጸም ላሳዩ የተቋሙ ሰራተኞችንም እውቅናና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።

#ለበለጠ መረጃ
በፊስ ቡክ አካዉንታችን ፡- https://web.facebook.com/dngworda0818
በቴሌግራም ቻናላችን ፡- https://t.me/dngl0818
ዩቲዩብ ገፃችን፡- https://www.youtube.com//about
ቲክቶክ ገፃችን፡- https://www.tiktok.com/?lang=en
በኢሜል አድራሻችን ፡- https://mail.google.com/mail/u/0/
በትዊተር ገጻችን ፡- https://x.com/DangilaWor79797
ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
‼️‼️

 #የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎችFBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
04/09/2026

#የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች

FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)

 #የኢትዮጵያ  ንግድ ባንክ ዳንግላ ቅርንጫፍ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።ነሃሴ 29/2018ዓም ዳንግላ ወረዳ ኮሙኒኬሽን በአዊ ብሄረሰብ አስተዳዳር በዳንግላ ወረዳ የኢትዮጵያ  ንግድ ባ...
04/09/2026

#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዳንግላ ቅርንጫፍ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ነሃሴ 29/2018ዓም ዳንግላ ወረዳ ኮሙኒኬሽን

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳዳር በዳንግላ ወረዳ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዳንግላ ቅርንጫፍ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ ።

" ደብተር #ለአንድ ተማሪ"በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ስራዎች በዳንግላ ወረዳ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዳንግላ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሌ ታከለ እንዳሉት #አንድም ተማሪ በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ እንዳይሆን የተቋሙ ሰራተኞችን በማስተባበር 10 #ደርዘን ደብተር በመግዛት ለዳንግላ ወረዳ ሴቶች ፣ህጻናት ፣ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስረክቧል።

ተቋሙ ለደንበኞች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልገሎት ከመስጠት ባሻገር በማህበራዊ ዘርፎች በበጎ አድራጎት ስራ በንቃት እንደሚሳተፍም አቶ ሙሌ አስረድተዋል።

"  ደብተር  #ለአንድ ተማሪ"በሚል መሪ ቃል  የክረምት በጎ ፈቃድ  የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ስራ ተጠናክሮ  እንደቀጠለ ነው።ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም  ዳንግላ ኮሙኒኬሽን በአዊ ብሔረሰብ አ...
04/09/2026

" ደብተር #ለአንድ ተማሪ"በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ስራ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም ዳንግላ ኮሙኒኬሽን

በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የዳንግላ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ሰራተኞች በኢኮኖሚ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የሚሆን #ሰባት ደርዘን ደብተር ድጋፍ አድርገዋል።

የዳንግላ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ተስፋየ አለበል እንደገለጹት ተቋሙ ማህበረሰቡን የፍትህ አገልግሎት ተጠቃሚ ከማድረግ ጎን ለጎን በማህበራዊ ድጋፎች እንደሚሳተፍ ጠቁመዋል።

ሁሉንም የተቋሙ ሰራተኞች በማስተባበር በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመሳተፍ የራሳቸውን አሻራ እንዲያስቀምጡ በማድረግ አንድም ተማሪ በቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ እንዳይሆን በማሰብ ከ4ሽ ብር በላይ ወጪ በማድረግ #7ደርዘን ደብተር ለዳንግላ ወረዳ ሴቶች ፣ህጻናት ፣ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስረክቧል

03/09/2026
የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት አፈፃፀም 2ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነ።የብሄረሰብ አስተዳደሩ  የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት አ...
02/09/2026

የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት አፈፃፀም 2ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነ።

የብሄረሰብ አስተዳደሩ የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀሙ ከዞንች ተወዳድሮ 2ኛ በመውጣት ዕውቅናና ሽልማት ተቀብሏል።

ሽልማቱን የተቀበሉት የመምሪያ ኃላፊ የሻሽወርቅ መላኩ፥ ለተገኘው የላቀ ውጤት በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ እንዲሁም አጋር አካላተ የላቀ በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

Awi communication

02/09/2026

Address

Dangila
Dangila

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dangila communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share