የደባርቅ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች/Debark woreda pp supportres

  • Home
  • Ethiopia
  • Debark'
  • የደባርቅ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች/Debark woreda pp supportres

የደባርቅ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች/Debark woreda pp supportres Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የደባርቅ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች/Debark woreda pp supportres, ሰሜን ጎንደር ደባርቅ ዙሪያ ወረዳ, Debark'.

ለሀገር በቀል የምግብ ዋስትና እና ለከተሞች ልማት የሚሆን አቅም የ'ሌማት ትሩፋት' እና የከተማ ግብርና! ​ምግብን በራስ አቅም መሸፈንና የገበያ እጥረትን በዘላቂነት መቅረፍ የብልጽግናችን መ...
30/08/2026

ለሀገር በቀል የምግብ ዋስትና እና ለከተሞች ልማት የሚሆን አቅም የ'ሌማት ትሩፋት' እና የከተማ ግብርና!

​ምግብን በራስ አቅም መሸፈንና የገበያ እጥረትን በዘላቂነት መቅረፍ የብልጽግናችን መሠረት ነው፤በሀገራችን የተጀመረው የ'ሌማት ትሩፋት' መርሐ-ግብር በዋናነት ወተት፣ እንቁላል፣ዓሳ ሥጋ እና ማር ከቅንጦትነት ወጥተው በትርፍነት ለእያንዳንዱ አባወራ እንዲደርሱ የማስቻል ትልቅ ራእይ አንግቦ እየሰራ ይገኛል።

​ነዋሪዎች የራሳቸውን የምግብ ፍጆታ በራሳቸው እንዲሸፍኑ፣ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመፍጠር ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ፣ጤንነቱና ደህንነቱ የተጠበቀ የምግብ ምርት ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣የገበያ አቅርቦት እጥረትን የሚሞሉ ሞዴል አምራቾችና ተቋማት እንዲፈጠሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው።

​የአማራ ክልል እንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮም ነባር ስራዎችን በማስቀጠልና አዳዲስ አምራቾችን ወደ ስራ በማስገባት የመርሐ-ግብሩን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በግንባር ቀደምትነት እየሰራ ይገኛል።

በጎነት ለሀገር ምርኩዝ ፣ ለወገን ፈውስ ነው !በጎ ፈቃደኝነት ጊዜንና ዕውቀትን ያለክፍያ ለወገን ከመስጠት የዘለለ ወደር የለሽ የሕሊና ዕረፍት የሚገኝበት ታላቅ መንፈሳዊ እርካታ ነው። በክረ...
30/08/2026

በጎነት ለሀገር ምርኩዝ ፣ ለወገን ፈውስ ነው !

በጎ ፈቃደኝነት ጊዜንና ዕውቀትን ያለክፍያ ለወገን ከመስጠት የዘለለ ወደር የለሽ የሕሊና ዕረፍት የሚገኝበት ታላቅ መንፈሳዊ እርካታ ነው። በክረምት ወቅት ዜጎች የወደቁትን በማንሳት፣ ለተከፋው እንባ በማበስና ለደከመው ምርኩዝ በመሆን እያሳዩ ያሉት ልባዊ አጋርነት ኢትዮጵያዊ የሞራል ልዕልናችን ማሳያ ነው። ይህ ድንቅ ማኅበራዊ መስተጋብር ልብን የሚጠግንና የሀገርን ተስፋ በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ደማቅ የበጎነት ኪዳን ነው።

የክረምት በጎ ፈቃድ ትሩፋት እጅግ መልከ ብዙና የመንግሥትንም ሆነ የሕዝብን ሙገሳ ያስገኘ ነው። ርኅሩኅ ዜጎች ሕይወት አድን ደም በመለገስ፣ ማዕድ በማጋራት፣ የአቅመ ደካሞችን ቤት በመጠገን፣ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠትና የትምህርት ቁሳቁስ በመለገስና በማሰባሰብ ፣ ማሳን በማረምና በተራቆቱ መሬቶች ላይ ችግኝ በመትከል ወዘተ ሁለንተናዊ አሻራቸውን እያሳረፉ ይገኛሉ። እያንዳንዱ የበጎነት ተግባር ለሀገር ምርኩዝና ለወገን ፈውስ ነውና በጎነት ይለምልም እንላለን።

 #በኮሪደር ልማት_ #ዘላቂ ከተማ_ #ውብ ገጽታ_ #የተሻለ ኑሮ~~~~~~~~~~~~~~ኮሪደር ልማት መንገድን ብቻ መገንባት ሳይሆን፣ ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለንግድ ማራኪ፣ ለአካባቢ ተስማሚና ለቀጣ...
30/08/2026

#በኮሪደር ልማት_ #ዘላቂ ከተማ_ #ውብ ገጽታ_ #የተሻለ ኑሮ
~~~~~~~~~~~~~~
ኮሪደር ልማት መንገድን ብቻ መገንባት ሳይሆን፣ ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለንግድ ማራኪ፣ ለአካባቢ ተስማሚና ለቀጣይ ትውልድ የሚበቃ ዘላቂ ከተማ መፍጠር ነው። የዛሬው የኮሪደር ልማት ለነገው ዘመናዊ እና ውብ ኢትዮጵያዊ ከተማ መሠረት እየጣለ ይገኛል።

እንችላለን እየቻልን ነው ! ባለፉት 50 ዓመታት በርካታ ሀገራት በእውቀት ላይ ባደረጉት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በአንድ ትውልድ ዕድሜ ውስጥ ከፍፁም ድህነት ወደ ላቀ ብልፅግና መሻገር ችለዋል።...
30/08/2026

እንችላለን እየቻልን ነው !

ባለፉት 50 ዓመታት በርካታ ሀገራት በእውቀት ላይ ባደረጉት ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በአንድ ትውልድ ዕድሜ ውስጥ ከፍፁም ድህነት ወደ ላቀ ብልፅግና መሻገር ችለዋል።

ኢትዮጵያም እንደ ዱባይና ሲንጋፖር ሁሉ የደረሱበት የዕድገት ማጫወቻ ሜዳ ላይ ለመድረስ ግልጽ ትልም አስቀምጣ ወደ ተግባር ገብታለች።

ይህ የብልፅግና ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን ግን የሁላችንም አወንታዊ አስተዋፅኦ ወሳኝ ነው!

ለውጡን ለማፋጠን የሚከተሉት አራት ምሰሶዎች ያስፈልጉናል፡

የእውቀት ሽግግር፡ በክህሎትና በቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ እውቀት መገንባት።

የአስተሳሰብ ሽግግር፡ መላው ህዝብ የብልፅግናን ራዕይ በአእምሮው አምኖ ለተግባራዊነቱ መጋት።

ከአሮጌ አሰራር መላቀቅ፡ ወደ ኋላ እያዩ ወደ ፊት መጓዝ ስለማይቻል ከተለመዱ አሰራሮችና አስተሳሰቦች መውጣት።

ከፋክክር ወደ ትብብር፡ ኃይልን በግጭትና በፋክክር ከመጨረስ እጅ ለእጅ ተያይዞ በትብብር መስራት።

እውቀትና ህብረት የብልፅግናችን መሰረቶች ናቸው።

“የሀገር ኩራትና የሰላም ዋስትና!”የአንድ ሀገር ኅልውና፣ ሉዓላዊነት እና ሁለንተናዊ ዕድገት ሊረጋገጥ የሚችለው አስተማማኝና ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር ሲኖር ብቻ ነው። ረጅም የታሪክ ማህደር ያ...
30/08/2026

“የሀገር ኩራትና የሰላም ዋስትና!”

የአንድ ሀገር ኅልውና፣ ሉዓላዊነት እና ሁለንተናዊ ዕድገት ሊረጋገጥ የሚችለው አስተማማኝና ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር ሲኖር ብቻ ነው።

ረጅም የታሪክ ማህደር ያላት ኢትዮጵያ፣ በርካታ ውጫዊና ውስጣዊ ፈተናዎችን ተቋቁማ ሉዓላዊነቷን አስከብራ እንድትቀጥል የመከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የደኅንነትና ሌሎች የጸጥታ ተቋማት የማይተካ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።

እነዚህ ተቋማት ለሀገራችን የብልጽግና ጉዞ መሠረት በመሆን ረገድ እያበረከቱት ያለውን አስተዋጽዖ ስንመለከት፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር በማስከበርና ሕዝባዊ ደኅንነትን በማረጋገጥ ቀዳሚው ናቸው።

#መከላከያ #ኢትዮጵያ

30/08/2026

ኢትዮጵያ እና ቀይ ባህር

የማይበጠስ ቁርኝት !

ኢትዮጵያን ከቀይ ባህር ለማራቅ የሚደረግ ማንኛውም ጥረት የታሪክን እውነት የመካድ እና የተፈጥሮን ህግ የመጣስ ያህል ነው።

የሌማት ትሩፋት በአማራ ክልል ከቤተሰብ ፍጆታ እስከ የምግብ ሉዓላዊነት!​በክልላችን እየተተገበረ የሚገኘው የ«ሌማት ትሩፋት» መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር፤ የማህበረሰቡን ...
25/08/2026

የሌማት ትሩፋት በአማራ ክልል ከቤተሰብ ፍጆታ እስከ የምግብ ሉዓላዊነት!

​በክልላችን እየተተገበረ የሚገኘው የ«ሌማት ትሩፋት» መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር፤ የማህበረሰቡን የአመጋገብ ባህል፣ የኢኮኖሚ መዋቅር እና የስራ ባህል የሚቀይር ስትራቴጂካዊ ንቅናቄ ነው።

በጥራጥሬ ላይ ብቻ የተንጠለጠለውን የምርት ስርዓት በመስበር፤ ወተት፣ ስጋ፣ እንቁላል እና ማርን ወደ አርሶ አደሩና ከተሜው ደጅ በማምጣት የህፃናት መቀንጨርን ለመቀነስ አስቻሊ ሁኔታ ፈጥሯል።

​መሬት ለሌላቸው ወጣቶች እና ሴቶች በትንሽ ቦታ የሚሰሩ የዶሮ እርባታ እና የንብ ማነብ ስራዎችን በመክፈት የከተማ ግብርና እንዲነቃቃ አድርጓል።

​ሀገር በቀል እንስሳትን በሰው ሰራሽ ማዳቀል እና በምርጥ ዝርያዎች በመተካት ከአነስተኛ ቁጥር ከፍተኛ ምርት የማግኘት ስራ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

​የወተት ማቀነባበሪያዎችን በማስፋፋት፣ የተሻሻሉ የመኖ ዝርያዎችን በማልማት እና አምራቹን ከደንበኛ ጋር በቀጥታ የሚያገናኙ አሰራሮችን በመዘርጋት ዘላቂነቱ እየተረጋገጠ ነው።

በክልላችን የተጀመረው የ«ሌማት ትሩፋት» ንቅናቄ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የማህበረሰቡን የአመጋገብ ባህልና የኢኮኖሚ መዋቅር እየቀየረ ይገኛል።

የተማሪዎቻችን ውጤት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አልፎ የተመዘገበ ታሪካዊ ድል ነው!ተማሪዎቻችን ያስመዘገቡት የላቀ ውጤት ተራ የስኬት ዜና ሳይሆን፤ እጅግ ፈታኝ፣ አሰልቺ እና በርካታ መሰናክሎች ...
24/08/2026

የተማሪዎቻችን ውጤት በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አልፎ የተመዘገበ ታሪካዊ ድል ነው!

ተማሪዎቻችን ያስመዘገቡት የላቀ ውጤት ተራ የስኬት ዜና ሳይሆን፤ እጅግ ፈታኝ፣ አሰልቺ እና በርካታ መሰናክሎች በበዙበት መንገድ ውስጥ አልፎ የተገኘ ታሪካዊ ድል ነው።

ትምህርት የእውቀት ብቻ ሳይሆን የፅናት መለኪያ መሆኑን ተማሪዎቻችን በተግባር አሳይተውናል። የሚያጋጥሙ ችግሮች ላለመማር ምክንያት ሊሆኑ በሚችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንኳን እነሱ ግን እንቅፋቶችን ወደ ድልድይነት በመቀየር ለትልቅ አላማ ተጋድለዋል። ሌሊቱን ከቀን ጋር አዋህደው ያጠኑት እያንዳንዱ ሰዓት፣ የተወጡት እያንዳንዱ ጭንቀት እና ያሳዩት የማያወላውል ፍላጎት ዛሬ ለዚህ የሚያኮራ ውጤት አብቅቷቸዋል።

"ዛሬ ተማሪዎችን እናስመዝግብ፣ነገ ለሀገሪቱ የተማረ የሰው ሃይል እናፍራ"ትምህርት የአንድ ሀገር ዕድገትና ብልፅግና መሰረት ነው። ዛሬ ሕፃናትንና ወጣቶችን ወደ ትምህርት ገበታ ማምጣት፣ ነገ ...
24/08/2026

"ዛሬ ተማሪዎችን እናስመዝግብ፣ነገ ለሀገሪቱ የተማረ የሰው ሃይል እናፍራ"

ትምህርት የአንድ ሀገር ዕድገትና ብልፅግና መሰረት ነው። ዛሬ ሕፃናትንና ወጣቶችን ወደ ትምህርት ገበታ ማምጣት፣ ነገ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ከፍታ የሚያሸጋገሩ አሳቢና አቅም ያላቸው ዜጎችን የመገንባት ዋስትናችን ነው።

ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ልጆቻችሁን ሳይዘገዩ በማስመዝገብ የመማር መብታቸውን አረጋግጡ።

በአካባቢያችሁ በኢኮኖሚም ሆነ በሌሎች ምክንያት ከትምህርት ገበታ የቀሩ ልጆች ካሉ እንዲመዘገቡ አግዟቸው።

ትምህርት የነገ ህልማችሁ መክፈቻ ቁልፍ በመሆኑ በአዲሱ የትምህርት ዘመን በጉጉት እንዲመዘገቡ የሁሉም ማህበረሰብ ኃላፊነት ነው።

እያንዳንዱ ዛሬ የሚመዘገብ ተማሪ፣ ነገ ሀገርን የሚያስተዳድር፣ የሚያድግ የሰው ኃይል ነው። አካባቢያችንን በማነቃቃት የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ በጋራ እንገንባ!

ፈተና ያልበገረው፣ በድል የታጀበ ውጤት !የአማራ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከሰተው የፀጥታ ችግር ከጎዳቸው ተቋማት አንዱ የትምህርት ዘርፉ ነው። የፀጥታ ችግሩ በተማሪዎች፣ በመምህራን እና በወ...
24/08/2026

ፈተና ያልበገረው፣ በድል የታጀበ ውጤት !

የአማራ ክልል ባለፉት ዓመታት የተከሰተው የፀጥታ ችግር ከጎዳቸው ተቋማት አንዱ የትምህርት ዘርፉ ነው። የፀጥታ ችግሩ በተማሪዎች፣ በመምህራን እና በወላጆች ከፍተኛ የስነልቦና ጫና አሳድሯል፤ በዘርፉ ላይ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳትንም አስተናግዷል።

ይሁን እንጂ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ውጤት የአማራ ክልል ከክልሎች መካከል ቀዳሚ በመሆን ፈተና ያልበገረው፣ በድል የታጀበ ውጤት አስመዝግቧል። ይህ ውጤት የክልሉ ትምህርት በፈተና ውስጥ ሆኖ የተመዘገበ በመሆኑ ለቀጣይ የትምህርት ስራ ትልቅ መነቃቃት የሚፈጥር ነው።

ከተባበርን፣ ከተደጋገፍን እና ትምህርት የትውልድ መቅረጫ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ከተረዳን የማናስመዘግበው ውጤት፣ የማናልፈው ፈተና አይኖርም። የተመዘገበው ውጤትም ክልሉ በትምህርት ፍትሐዊነት እና ጥራት ላይ እያደረገ ያለውን ሁለንተናዊ ጥረት በተግባር ያረጋገጠ ነው።

Address

ሰሜን ጎንደር ደባርቅ ዙሪያ ወረዳ
Debark'
0581170450

Telephone

0581170450

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደባርቅ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ደጋፊዎች/Debark woreda pp supportres posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share