North Gondar Communication

North Gondar Communication የፌስቡክ ገፃችንን ይውደዱን፣ይጋሩንና አስተያየት ይስጡን?

"አረጋዊያንን መርዳት የሕሊና እርካታ ነው።" የሰሜን ጎንደር ዞን የመቄዶንያ ቅርንጫፍ። ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም  (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)         የሰሜን ጎንደር ዞን የኅብረት ...
08/05/2026

"አረጋዊያንን መርዳት የሕሊና እርካታ ነው።" የሰሜን ጎንደር ዞን የመቄዶንያ ቅርንጫፍ።

ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

የሰሜን ጎንደር ዞን የኅብረት ሥራ ማኅበራት ተጠሪ ጽሕፈት ቤት በደባርቅ ከተማ ለሚገኘው መቄዶንያ አረጋዊያንና የሕሙማን መርጃ ማኅበር የስኳርና የዘይት ድጋፍ አድርጓል።

የድጋፉን ያስረከቡት የዞኑ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ተጠሪ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ አስራት ከብረት የደባርቅ ከተማ ዩኒዬን አስተባብሮ 50 ኪሎ ግራም ስኳርና 150 ሊትር ዘይት ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል። ዩኒዬኑ ባስቀመጠው ደንብና መመሪያ መሠረት ከሚያገኘው ትርፍ ለማኅበራዊ አገልገሎት በፐርሰንት እንዲቆረጥ አድርጎ ለማኅበራዊ አገልግሎት የሚውለውን የትርፍ ክፍፍል ለመቄዶንያ እንዲውል ወስኗል ብለዋል።

ወይዘሮ አስራት እንደሚሉት "ሰው ለመርዳት ሰው መኾን በቂ ነው" የሚለውን የመቄዶንያ መሪ ቃል መደገፍና መርዳት የሁሉም ተቋም ኃላፊነት እንደኾነ ተናግረዋል። ይህን መነሻ በማድረግ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ መሠረታዊ የኅብረት ማኅበራት መቄዶንያን መደገፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የሰሜን ጎንደር ዞን ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊና የመቄዶንያ አስተባባሪ አቶ ወገኔ አማረ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው አረጋዊያን ከመርዳት በላይ ትልቅ ተግባር እንደሌለ አስገንዝበዋል። የሰሜን ጎንደር ዞን የኅብረት ሥራ ማኅበራትና የደባርቅ ዩኒዬን ያደረጉት ድጋፍ በጎ አስተሳሰብ በመኾኑ ሌሎች ግለሰቦች፣ የመንግሥት ተቋማትና መንግሥትዊ ያልኾኑ ድርጅቶች ድጋፋቸው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል።

መቄዶንያ የሰሜን ጎንደር ዞን ቅርጫፍ አስተባባሪ ዲያቆን አስማማው መንግሥቴ ለተደረገላቸው ድጋፍ በማኅበሩ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል። ለሀገር ባለውለታ የኾኑት በመቄዶንያ ግቢ የተጠለሉ አረጋዊያን የሰው ናፍቆት ስላለባቸው ሁሉም ሰው ቢጎበኛቸው የሚል አስተያየት ሰጥተዋል።

እንደ ሀገር ከ8,500 በላይ አረጋዊያን በመቄዶንያ እንክብካቤ እየተደረገላቸው እንደኾነ የጠቆሙት ዲያቆን አስማማው እንደ ደባርቅ ቅርንጫፍ ከግንቦት 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ አረጋዊያንን ከጎዳና ላይ የማንሳት ሥራ እንደሚሠራ ጠቅሰዋል። ማንኛውም በጎ እና ቅን ልቡና ያለው ሰው ሁሉ በሚችለው ልክ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ሲሉ አሳስበዋል።

በመጨረሻም አረጋዊያኑ ለመቄዶንያ መሥራችና ድጋፍና እንክብካቤ ለሚያደርጉት ወገኖች ሁሉ ምስጋና እና አባታዊ ምርቃንም ለግሰዋል።

የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፌስቡክ ገፅ ከተቋሙ ቁጥጥር ውጭ መሆኑ ተገለፀ።የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፌስቡክ ገፅ ከሚያዚያ 27/2018ዓ.ም ጀምሮ ከተቋሙ ቁጥጥር ውጭ ሆኗ...
08/05/2026

የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፌስቡክ ገፅ ከተቋሙ ቁጥጥር ውጭ መሆኑ ተገለፀ።

የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የፌስቡክ ገፅ ከሚያዚያ 27/2018ዓ.ም ጀምሮ ከተቋሙ ቁጥጥር ውጭ ሆኗል።

የፌስቡክ ገፁ አድሚን የነበረው የተቋሙ ዲን አቶ አስጨንቅ ካሳ በጠላት ታፍነው በመወሰዳቸው ፔጁን ጠላት ሀሰተኛ መረጃ እያስተላለፈበት ይገኛል።

በመሆኑም ግለሰቡ በጠላት ቁጥጥር ስር ከዋለበት ቀን ማለትም ከሚያዚያ 27/2018ዓ.ም ጀምሮ በተቋሙ ገፅ የሚለቀቁ መረጃዎች የተቋሙ አለመሆናቸውን ለመግለፅ እንወዳለን።

በሰሜን ጎንደር ዞን በአዲ አርቃይ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ የምረጡኝ ቅስቀሳና ዕጩዎችን የማስተዋወቅ ጀመረ።
08/05/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን በአዲ አርቃይ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ የምረጡኝ ቅስቀሳና ዕጩዎችን የማስተዋወቅ ጀመረ።

"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር"! በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ከተማ  የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ እና ምልክት ትውውቅ  መርሐ ግብር የክልልና የዞን አመራሮች በተገኙበት ተካሄዷል።
08/05/2026

"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር"!
በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ እና ምልክት ትውውቅ መርሐ ግብር የክልልና የዞን አመራሮች በተገኙበት ተካሄዷል።

በሰሜን ጎንደር ዞን የጃናሞራ ወረዳ የሴት አደረጃጀቶች  በተለያዩ ቀበሌዎች የ7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ፣ የምርጫ ቅስቀሳ እና የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃግብር ።
08/05/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን የጃናሞራ ወረዳ የሴት አደረጃጀቶች በተለያዩ ቀበሌዎች የ7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ፣ የምርጫ ቅስቀሳ እና የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ መርሃግብር ።

በሰሜን ጎንደር ዞን የጠለምት ወረዳ ሴቶች አደረጃጀት የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የማሰተዋወቅ ፕሮግራም ተካሄደ።
08/05/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን የጠለምት ወረዳ ሴቶች አደረጃጀት የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የማሰተዋወቅ ፕሮግራም ተካሄደ።

ዓለም አቀፍ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ሰብአዊ አገልግሎት ማህበር ለ78ኛ ጊዜ ተከበረ።ሚያዚያ 30/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን )" ትብብር ለሰብአዊነት" በሚል መሪ ቃል የሰሜን ጎንደ...
08/05/2026

ዓለም አቀፍ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ሰብአዊ አገልግሎት ማህበር ለ78ኛ ጊዜ ተከበረ።

ሚያዚያ 30/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን )

" ትብብር ለሰብአዊነት" በሚል መሪ ቃል የሰሜን ጎንደር ዞን ቀይ መስቀል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን 78ኛውን የአም ዓቀፍ ቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ መታሰቢያ በአል በደባርቅ የመቄዶንያ መርጃ ማእከል አክብሯል ።

የዞኑ ቀይመሰቀል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ የኛ ነጋ በዓሉ የሚከበርበት ዓላማ ለሰብአዊነት አገልግሎት እውቅና ለመስጠት ፣ የማህበሩን መርሆዎች ለማስተዋወቅና አጋርነትን ለማጠናከር እንደሆነ አስታውቀዋል።

በአሉን በመቄዶንያ የአረጋውያን መርጃ ማእከል ማክበር ያስፈለገበት ምክንያት አጋርነታቸውን ለማሳየት እንደሆነ ተናግረዋል ። ለአረጋውያን የአልባሳትና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ በበጎ ፈቃደኞች እግር የማጠብ ፕሮግራም መካሄዱ ትልቅ እርካታ እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል ።

የደባርቅ መቄዶኒያ መርጃ ማእከል አስተባባሪ የሆኑት አቶ ወገኔ አማረ ማስተባበሪያ ጽ/ቤቱ በማእከሉ ለሚገኙ አረጋውያን ያደረገውን ድጋፍ አመስግነው ሁሉም አካላት ገንዘብና ቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግ ባሻገር በሃሳብ ማገዝም ድጋፍ እንደሆነ ተናግረዋል ።

የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ሜዲካል ላቦራቶሪ የትምህርት ክፍል ኃላፊ መ/ር ትንፋሽ ከበደ ከዞኑ ቀይ መስቀል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት በሙያቸው መርጃ ማእከሉን ለማገልገል ፈቃደኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አረጋውያንም ለተደረገላቸው የቁሳቁስ ድጋፍና የእግር አጠባ ፕሮግራም በምርቃት አመስግነዋል ።

የሚዲያ ዘርፉ እውነትን በማሳወቅ እና ለጋራ ብሔራዊ ማንነት ግንባታ በትኩረት ሊሠራ ይገባል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን) መ...
08/05/2026

የሚዲያ ዘርፉ እውነትን በማሳወቅ እና ለጋራ ብሔራዊ ማንነት ግንባታ በትኩረት ሊሠራ ይገባል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ሚያዝያ 30/2018 ዓ.ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

መንግሥት የሚዲያ ምህዳሩ በነጻነት እንዲሠራ የሚያስችለውን ምቹ አውድ መፍጠሩን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ዘርፉ የታዩ ድክመቶችን በማረም ለጋራ ብሔራዊ ማንነት ግንባታ በትኩረት እንዲሠራ አሳስበዋል።

ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የጠንካራ ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሚዲያው በዚህ ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸዋል።

ከለውጡ በፊት ለመናገር እና ለመጻፍ እንቅፋት የነበሩ አሳሪ ሕጎች፣ በተለይም የፀረ-ሽብር ሕጉ በሚዲያ ነጻነት ላይ የነበረው ተጽዕኖ እንዲሻሻል መደረጉንም አስታውሰዋል።

በሚዲያ ነጻነት ዙሪያ በርካታ መሠረታዊ ለውጦች መከናወናቸውን ገልጸው፣ በሙያቸውና በዘገባዎቻቸው ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች እንዲፈቱ መደረጉን አንስተዋል።

በተጨማሪም ከውጭ በሚተላለፉ የሚዲያ ስርጭቶች ላይ ይደረግ የነበረው የሲግናል ማፈን እንዲቆም መደረጉንና ታግደው የነበሩ የውጭ ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች በነጻነት ወደ ኢትዮጵያ ገብተው እንዲሠሩ መፈቀዱን ገልጸዋል።

ሆኖም የሚዲያ ምህዳሩን የማስፋቱ ሂደት ያለ ፈተና እንዳልነበረ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በተለይም ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ያልተከተሉና የተሰጠውን ነጻነት በአግባቡ መጠቀም የተሳናቸው አካላት መኖራቸው በሂደቱ ላይ ተጽዕኖ ማሳረፉን ጠቁመዋል።

በመሆኑም የሚዲያ ተቋማት እውነትን በማሳወቅና የጋራ ብሔራዊ ማንነትን በመገንባት ረገድ የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር!በደቡብ ወሎ ዞን በወረባቦ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ  ሰልፍ እየተካሄ ነዉ። 7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ፣ ...
08/05/2026

ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር!

በደቡብ ወሎ ዞን በወረባቦ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ እና የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄ ነዉ።

7ኛው ሃገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ፣ ሚዛናዊ እና ነጻ ሆኖ እንዲከናወን የበኩላቸውን ድጋፍ እንደሚያደርጉም በዛሬው ዕለት ባደረጉት የድጋፍ በሰላማዊ ሰልፍ ገልጸዋል።

በጎንደን ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በፎቶ!!
08/05/2026

በጎንደን ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በፎቶ!!

በምስራቅ ጎጃም ዞን በአዋበል ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ  በተለያዩ ቀበሌዎች ተካሂዷል። ‎
08/05/2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን በአዋበል ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የጎዳና ላይ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ ቀበሌዎች ተካሂዷል።

Address

North
Debark'

Telephone

+251584171125

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when North Gondar Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to North Gondar Communication:

Share