North Gondar Communication

North Gondar Communication የፌስቡክ ገፃችንን ይውደዱን፣ይጋሩንና አስተያየት ይስጡን?

በደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ቀጥለዋል። ደባርቅ፡ ጳጉሜን 01/2018 ዓ.ም(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በጫ...
06/09/2026

በደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ቀጥለዋል።
ደባርቅ፡ ጳጉሜን 01/2018 ዓ.ም(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ቀጥለዋል።

በወረዳው ከአሁን በፊትም በርካታ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለው መግባታቸው ይታወሳል። ዛሬም በወረዳው በምስራቁ ቀጠና ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 32 የሚሆኑ ተጨማሪ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል።

የሰላም አማራጭ የተቀበሉትን ታጣቂዎች የደባርቅ ወረዳ የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የሰላም አማራጭን የተቀበሉት ታጣቂዎች ሲጓዙበት የነበረው መንገድ የተሳሳተ መኾኑን መገንዘባቸውን ገልጸዋል። የነበሩበትን የጥፋት መንገድ በመተው ወደ ኅብረተሰቡ እና ሰላማዊ ሕይወት ለመመለስ መወሰናቸውንም አስታውቀዋል።

ደባርቅ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን

የእመርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ የሰብል ጉብኝት ተካሄደ።ጳጉሜን 01/2018 ዓ/ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)በሰሜን ጎንደር ዞን በበየዳ ወረዳ በመልባ ቃራ ቀበሌ ግራሩ ጎጥ  የእምርታ ...
06/09/2026

የእመርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ የሰብል ጉብኝት ተካሄደ።

ጳጉሜን 01/2018 ዓ/ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

በሰሜን ጎንደር ዞን በበየዳ ወረዳ በመልባ ቃራ ቀበሌ ግራሩ ጎጥ የእምርታ ቀንን ምክኒያት በማድረግ በክላስተር የተዘራ ስንዴ ጉብኝት ተካሂዷል።

ሀገራችን ከተረጂነት አስተሳሰብ ለመውጣት ግብርናን በማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ገለጸ።

የበየዳ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/ህይዎት በላይነህ በጉብኝቱ እንደገለጹት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የኢኮኖሚ ሉዓላዊነቷን ለማስከበር ግብርና ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሰራት እንዳለበት አብራርተዋል።

እንደ አቶ ገ/ህይዎት በላይነህ ገለጻ የዘንድሮው ክረም ዘግይቶ በመግባቱ በወረዳችን ድርቅ እንዲከሰት እንዳደረገው ገልጸው ጉብኝት የተካሄደበት የክላስተር ስንዴ ዝናቡ ቀጣይነት ከሌለው የሚፈለገውን ምርት ለማግኘት ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸዋል።

"እመርታ ለዘላቂ ከፍታ"

በዓላት ትናንትን ከዛሬ፤ ዛሬን ከነገ የሚያገናኙ ድልድዮች ናቸው!የአማራ ክልል ባሕል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ የክረምት የአደባባይ በዓላት የማጠቃለያ መርኀ ግብር በባሕር ዳር ከተማ እያካሄደ...
06/09/2026

በዓላት ትናንትን ከዛሬ፤ ዛሬን ከነገ የሚያገናኙ ድልድዮች ናቸው!

የአማራ ክልል ባሕል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ የክረምት የአደባባይ በዓላት የማጠቃለያ መርኀ ግብር በባሕር ዳር ከተማ እያካሄደ ነው።

በመርሐ ግብሩ የተገኙት የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ በዓላትን ማክበር የመዝናኛ እና የመደሰቻ ብቻ ሳይኾን የማንነት፤ የታሪክ እሴቶችን፤ የትውልድ ቅብብሎሽን የሚያሳዩ መንገዶች ናቸው ብለዋል።

ክብረ በዓላት ትናንትን ከዛሬ፤ ዛሬን ከነገ የሚያገናኙ ድልድዮች መኾናቸውን ተናግረዋል። የበዓላት መከበር የባሕል ልምድን ለመጠበቅ፤ ለማጎልበት፤ የልጃገረዶችን ተሳትፎ ለማጠናከር፤ የሴቶችን ባሕላዊ ሚና ለማክበር እና የቱሪዝም ሃብት የኾኑት በዓላት ትውፊታቸው ተጠብቆ እንዲዘልቅ ጠቀሜታው የጎላ መኾኑን አንስተዋል።

በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አሥተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር) በኢትዮጵያ የክረምት ወቅት የልጃገረዶች የነጻነት፣ የአብሮነት እና የባሕል ማሳያ የኾኑ በዓላት በድምቀት የሚከበሩበት ልዩ ጊዜ ነው ብለዋል።

ክብረ በዓላት የቱሪዝም መስህቦች መኾናቸውን ተናግረዋል። ባሕልን እንደ ታላቅ ሃብት ማየት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ቱሪዝም የሥራ ዕድል መፍጠሪያ፤ የኢኮኖሚ ማነቃቂያ እና የገቢ ምንጭ መኾኑንም አንስተዋል።

ወጣቶች የሕዝብ መገለጫ በጎ ባሕሎችን ወደ ዲጂታል ዓለም ልታመጡት ይገባል ነው ያሉት። የማይዳሰሱ የባሕል ቅርሶችን በዓለም ቅርስነት ለማስመዝገብ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

የተከበሩ የባሕል እሴቶችን ከዘመናዊው የዴሞክራሲ ባሕል ጋር ማስተሳስር ይገባል ነው ያሉት። በዓላት እና ባሕላዊ ሥርዓቶች የጋራ ማንነትን ያጠናክራሉ፤ ትውልድን ከትውልድ ያስተሳስራሉ፤ የፍቅር እና የመከባበር እሴቶችን ያስተላልፋሉ፤ የጋራ ታሪካችንንም በሕያው መልኩ ያስቀጥላሉ ነው ያሉት። በዓላትን በአንድነት እናክብር፣ በጋራ እንድመቅ፣ በመከባበር አንድነታችንን እናጠናክር ብለዋል።

#ኢትዮጵያ

በእምርታ ቀን የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ፍፃሚያቸውን አገኙ ። ደባርቅ :- ጳጉሜን 01/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን) በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስ...
06/09/2026

በእምርታ ቀን የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ፍፃሚያቸውን አገኙ ።

ደባርቅ :- ጳጉሜን 01/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)


በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽቤት ለሁለት ወራት ሲካሄዱ የነበሩ ስፖርታዊ ውድድሮች "በእምርታ ቀን" ፍፃሚያቸውን አግኝተዋል ።

በፍፃሜው ጨዋታ ንግግር ያደረጉት የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባና የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስጦታው ታጀበ በክረምት ወራት ሲካሄዱ የቆዩት ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባሻገር ጤንነትን በመጠበቅ ጉልህ ሚና መጫወታቸውን ገልፀዋል።

በቀጣይም ስፖርቱን ለማሳደግ በተለያዩ የስፖርት አይነቶች የበጋ ውድድሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ ስጦታው ተናግረዋል።

በእለቱ በ13 አመት በታች የእግር ኳስ ጨዋታ ኢቫንጋዲ ከወንደማማቾች በነበረው ጨዋታ ኢቫንጋዲ የዋንጫና የሰባት ሺ ብር ተሸላሚ ሰሆን በ15 አመት በታች እግር ኳስ ውድድር ደግሞ በሰባ ደረጃና ማክቬል ተካሂዶ ሰባ ደረጃ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

ከጧቱ 4:00 ሰአት ጀምሮ በማክቤልና ቦልማ መካከል የተካሄደው የታዳጊዎች የፉት ሳል ውድድር ማክቬል ቦልማን 3ለ1 አሸንፎ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነ ሲሆን በአዋቂዎች በቀይመስቀልና ምርጦቹ በተካሄደው የፉት ሳል ውድድር ጨዋታው ሁለት አቻ በመጠናቀቁ ምርጦቹ በመለያ ምት አሸንፈው የዋንጫ ተሸላሚ በመሆን የእለቱ ውድድር ተጠናቋል።

"በጀግንነት እንጠብቃለን፤ በሰብዓዊነት እናገለግላለን!"የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 አመታዊ ግምገማና የ2019 የእቅድ ትዉዉቅ አካሄዷል።ደባርቅ፦ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም(...
06/09/2026

"በጀግንነት እንጠብቃለን፤ በሰብዓዊነት እናገለግላለን!"

የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 አመታዊ ግምገማና የ2019 የእቅድ ትዉዉቅ አካሄዷል።

ደባርቅ፦ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
(የሰሜን ጎንደር ኮሙኒኬሽን)

የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 አመታዊ የአፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 የእቅድ ትዉዉቅ መድረክ በዞኑ መቀመጫ ደባርቅ ከተማ አካሄዷል። በመድረኩም የዞን፣ የወረዳዎችና የከተሞች የፓሊስ አዛዦችና የማኔጅመንት አባላት ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ምህረት መለሰ የዞኑ ፖሊስ በ2018 ዓ.ም በርካታ ተግባራትን አከናውኗል። ጥሩ ዉጤትም አስመዝግቧል። ለዚህ ዉጤትም አባላት ተገብረዋል፤ የህይወት ዋጋ ተከፍሏል፣ በርካታ ፈተናዎችን አልፈን ዛሬ ላይ ላለንበት ደረጃ ደርሰናል።

2018 ዓ.ም ያለፈዉ የፖሊስ ሪፎርምን ተግባራዊ ከማድረግ ጎን ለጎን ህግ የማስከበር ስራዎችን ስናከናውን ቆይተናል ያሉት የፖሊስ አዛዡ ፖሊስ በሃገራችን ብሎም በክልላችን የተከሰተው የጸጥታ ችግር ሳይገድበዉ፦ ወንጀለኞችን አሳድዶ ለህግ በማቅረብ፣ ብሄራዊና ኃይማኖታዊ በዓላትን በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን፣ 7ኛዉን ሃገር አቀፍ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ፣ ብሄራዊና ክልላዊ ፈተናዎችን በብቃት የማስፈጸም፣ እንደባህል የሚቆጠረዉን የጥይት ተኩስ ማስቆም ተችሏል።

በተጨማሪም የወረዳ ቀበሌዎችን ከታጣቂዎች ነጻ የማዉጣት፣ በተወሰኑ ቀበሌዎች የኮሚዩኒቲ ፖሊሲንግ ማስተግበር፣ ለታጣቂ ኃይሎች ሊተላለፉ የነበሩ የምግብና የሎጀስቲክስ ቁሳቁሶች፣ የጦር መሳሪያዎችን ተከታትሎ መያዝና የማስቆም፣ ህገ ወጥ ተግባራትን (የመሬት ወረራ፣ ልቅ ግጦሽ፣ የጨረቃ ቤት) ስራዎችን የማስቆም ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል።

አሁን ላይ በተሰሩ ጠንካራ የህግ ማስከበር ተግባራት ፖሊስ ለህይወቱ ሳይሰስት ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት አብዛኞች ቀበሌዎች የአመራሮችና ባለሙያዎች ተንቀሳቅሰው አገልግሎት መስጠት መቻላቸውን ከበየዳ ወረዳ የመጡ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

በጃናሞራ ወረዳ ቀበሌዎች እስካሁን ታጣቂዎች ገብተዉ አያውቅም። ይህም ሊሆን የቻለው ከወረዳው የጸጥታ መዋቅር፣ ከአመራሩ እና ከማህበረሰቡ ጋር በመናበብ በቅንጅት በመሠራቱ ነዉ። ይሄንም አጠናክረን ማስቀጠል ይኖርብናል ሲሉ ከጃናሞራ ወረዳ የመጡ የፖሊስ አመራሮች ገልጸዋል።

የፖሊስ አባላትን መብትና ጥቅማቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ፖሊስ ህግ ለማስከበር የሚያግዝ ተሽከርካሪ ያስፈልጋዋል፤ በህብረተሰቡ የሚነዙ ሃሰተኛ መረጃዎች ተቋሙን የሚቀላቀሉ አባላት እንዳይፈጠሩ እንቅፋት ፈጥሯል፤ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም ከመምሪያ ፖሊስ መኮንኖች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። የ2019 በጀት አመት የእቅድ ኦረንቴሽን ቀርቧል። የቀጣይ አቅጣጫ እና የስራ መመሪያ ተሰጥቷል።

"የኢትዮጲያ ማንሰራራት"  በሚል መሪ ቃል በዳባት ወረዳ  እየለሙ ያሉ የተለያዩ የልማት ስራዎችን  አስመልክቶ የመስክ ምልከታ ተካሄደ ፡፡ ዳባት፡ዻጉሜ 01/2018 ዓ.ም (ሰሜን ጎንደር  ኮ...
06/09/2026

"የኢትዮጲያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በዳባት ወረዳ እየለሙ ያሉ የተለያዩ የልማት ስራዎችን አስመልክቶ የመስክ ምልከታ ተካሄደ ፡፡

ዳባት፡ዻጉሜ 01/2018 ዓ.ም (ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ "የኢትዮጲያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የእምርታ ቀንን በልማት ጉብኝት ተከብሮ ውሏል፡፡

የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ውጤታማ ለማድረግ እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በወረዳው በርካታስራዎች መከናናቸውን የዳባት ወረዳ መሬት ጽ/ቤት ኃላፊና ተወካይ አስተዳዳሪ አቶ አግንቸ ጌጡ ገልፀዋል፡፡

የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት ስራዎች እየተተገበሩ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡
ሰብሎችን በክላስተር ማልማቱ ቁጥጥርና ክትትል ለማድረግ እና በቀጣይ የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተወካይ አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡

በልማቱ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን በመስክ መመልከት፣ ተሞክሮዎችን መቀመር፣ የተሻሉ አሠራሮችን ማስፋፋት ይጠበቃል ብለዋል አቶ አግንቸ፡፡

የእምርታ ቀን መከበሩ የግብርናው ዘርፍ ትልቅ የኢኮኖሚ ለውጥ የሚያመጣበት እና ከእርሻ መር ወደ ኢንዱስትሪ መር የሚሸጋገርበት ድልድይ መሆኑን የዳባት ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ዳውድ ጡሃየ አስረድተዋል፡፡

ስንዴን በክላስተር በማልማት ሃገራችንን ከተረጅነት ወደ ማምረት ከማሸጋገር ባለፈ የተለያዩ የጎንዮሽ ችግሮችን ለመፍታት የጎላ አስተዋፅኦ እንዳለው ምክትል ሃላፊው ተናግረዋል፡፡

በወረዳው ከ29 ሺ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን የጠቆሙት አቶ ዳውድ ከዚህም ውሥጥ 2ሺ ሄክታሩ በስንዴ ማሳ የተሸፈነ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ከተረጅነት ወደ ማምረት ለመሸጋገር በአስተደዳር ምክር ቤቱ በተገኘ ገንዘብ ድጋፍ ፣ ከአመራሩና ከማህበረሰቡ በተሰበሰበ የአይነት እና የገንዘብ የተሸ ስራ መከናወኑ ተገልጿል፡፡
አንድ ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ብር እና 60 ኩንታል የምግብ ፍጆታ መሰብሰብ መቻሉን አቶ ዳውድ ተናግረዋል፡፡

በወረዳው እየለሙ ያሉ የልማት ስራዎችን የመስክ ምልከታ በማድረግ የእምርታን ቀን ተከብሮ መዋሉ ተመላክቷል ፡፡

ዳባት ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን

በሰሜን ጎንደር ዞን በጃናሞራ ወረዳ የደረስጌ ቀበሌ የቢራ ገብስ ክላስተር አሁናዊ ገፅታ
06/09/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን በጃናሞራ ወረዳ የደረስጌ ቀበሌ የቢራ ገብስ ክላስተር አሁናዊ ገፅታ

ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ታሳቢ ተደርጎ የግብርና ገጠር ልማት ፖሊሲ ተቀርፆ ተግባራዊ እየተደረገ ነው"አቶ ጌታቸው አዳነ የግብርና መምሪያ ኃላፊ ደባርቅ :- ጳጉሜን 01/2018(ሰሜን ጎን...
06/09/2026

ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ታሳቢ ተደርጎ የግብርና ገጠር ልማት ፖሊሲ ተቀርፆ ተግባራዊ እየተደረገ ነው"
አቶ ጌታቸው አዳነ የግብርና መምሪያ ኃላፊ

ደባርቅ :- ጳጉሜን 01/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

የሰሜን ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ አቶ ጌታቸው አዳነ ጳጉሜን አንድን "የእምርታ" ቀንን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

አቶ ጌታቸው በመግለጫው የለውጡ መንግስት የምግብ ሉኣላዊነትን በሃገራችን ለማረጋገጥ ሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድሬ እንደዞን አበረታች ለውጦች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

ኃላፊው ጨምረውም የገጠር ልማት ዘርፉን ለማሳደግ የነበሩ መሰረታዊ ማነቆዎችን ለመፍታትና ዘመኑ የደረሰበትን ቴከኖሎጂ ታሳቢ ያደረገ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ተቀርፆ ተግባራዊ እንደሆነ ተናግረዋል ፡፡

በዚህም የህግና የአሰራር ማሻሻያ ማዕቀፍ በማድረግ የግብርና ምርታማነትና ተወዳዳሪነትን የማረጋገጥ፣ግብርና በቴክኖሎጂና በሳይንስ እንዲመራ፣ኮሜርሻላይዜሽንን የማስፋፋት፣ በሌሎች ዘርፎች እንዲደገፍ የገጠር መዋቅራዊ ሽግግርን የመተግብር ዘላቂነትን ለማረጋገጥ የአየር ንብርት ለዉጥን ያገናዘበ የግብርና ልማት፣ የገጠር ልማት ፋይናንስ አቅርቦትና ተደራሽነት፣ የተቀናጀ የገጠር መሰረተ ልማትን ትኩረት ያደረገ ስራ እየተሰራ እንደሆነ አቶ ጌታቸው አብራርተዋል።

በዞናችን ባሉ ወረዳዎች የጥራት፣ የተደራሽነትና የዘላቂነት ችግር ቢኖርም በርካታ ሞዴል ተግባራት እንተሰሩ ኃላፊው ገልጸዋል ፡፡

በቀጣይ የአካባቢዉን እምቅ አቅምና ፀጋ በመጠቀም ቁልፍ የዉጤት መስኮች ላይ ትኩረት በማድረግ የተጀመረዉን የዘርፉ እምርታ አጠናክሮ የማስቀጠልና ራስን የመቻል አቅምን በመገንባት የምግብ ሎኣላዊነት የማረጋገጥ ተግባርን ሁሉም ባለድርሻ አካላት አሻራቸዉን እንዲያሳርፍ አሳስበዋል።

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ ታጥቀው በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀበሉ።ደባርቅ፡ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (የሰሜን ጎንደር ኮሙኒኬሽን)በሰሜን ጎንደር ዞ...
05/09/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ ታጥቀው በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀበሉ።

ደባርቅ፡ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (የሰሜን ጎንደር ኮሙኒኬሽን)

በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ ምስራቃዊ ቀጠና ከበለስ እስከ አጣምታና መረባ አካባቢዎች ታጥቀዉ በጫካ ውስጥ ሲንቀሳቀስ የቆየውና ራሱን የ208ኛ ኮር የራስ ገብሬ ብርጌድ ብሎ የሚጠራዉ ታጣቂ ቡድን የሰላም አማራጭን በመምረጥ በሰላም ገብተቀል።

በታጣቂዎች አጠራር በብርጌድ መሪው ዜናው ሃይለማርያም መሪነት የተደራጀው ይህ ኃይል፣ የሻለቃ አመራሮችንና የሻምበል መሪዎችን ጨምሮ አጠቃላይ 56 ታጣቂ አባላቱን ይዞ ወደ ሰላሙ ማህበረሰብ ተቀላቅሏል።

ቡድኑን ይዞት ከመጣው የጦር መሣሪያ ዝርዝር ውስጥ አንድ ስናይፐር፣ አንድ ብሬን እና የተለያዩ ነፍስ ወከፍ መሣሪያዎች ይገኙበታል።

የአካባቢው ህብረተሰብ እና አመራሮች ታጣቂዎቹን በደማቅ ሁኔታ የተቀበላቸው ሲሆን በስነ-ስርዓቱ ላይ የዞን፣ የመከላከያ፣ እንዲሁም የወረዳ የፀጥታና የፖለቲካ አመራሮች ተገኝተዋል።

የሃገር መከላከያ ሰራዊት የ10ኛ ዕዝ ዘመቻ አመራሮችና አባላት፣ የሰሜን ጎንደር ዞን እና የደባርቅ ወረዳ አመራሮች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ አስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ በየደረጃው ያሉ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎች አካላት ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

መረጃዉ የደባርቅ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነዉ።

በደባርቅ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የቮሊቦል ጨዋታ ፍፃሜውን አገኘ።ደባርቅ:- ነሐሴ 30/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን) በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ከተማ አስተዳደር ባህል  ቱሪዝምና ስ...
05/09/2026

በደባርቅ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የቮሊቦል ጨዋታ ፍፃሜውን አገኘ።

ደባርቅ:- ነሐሴ 30/2018(ሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት በክረምት ሲካሄድ የነበረው የቮሊቦል ጨዋታ በቀይ መስቀል አሸናፊነት ተጠናቋል።

በስድስት ቡድኖች ተከፍሎ ለሁለት ወራት ሲካሄድ የቆየው የቮሊቦል ውድድር በሰሜን በርና በቀይ መስቀል መካከል የተካሄደው የዋንጫ ፍፃሜ በቀይ መስቀል 3ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በፍፃሜው ጨዋታ የከተማ አስተዳሩ ተወካይ ከንቲባና የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊና ስጦታው ታጀበ ሌሎች የዞንና የከተማ አስተዳደሩ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

Address

North
Debark'

Telephone

+251584171125

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when North Gondar Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to North Gondar Communication:

Shortcuts

Share