28/07/2026
በ2018 በጀት ዓመት በፍትሐብሄር ጉዳዮች ፍትህ አስተዳደር በርካታ ተግባራት የተፈጸሙ እና መልካም አፈጻጸም የተመዘገበ ሲሆን ከተከናወኑት ዋና ዋና ተግባራት መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
በፍትሐብሄር ጉዳዮች በቀጥታ ክስ፣ ይግባኝ መልስና ሰበር መልስ ክርክሮች የመዛግብት የማጥራት ቅልጥፍናን 97.5% ለማድረስ በዕቅድ ተይዞ ብር 25 ቢሊየን 014 ሚሊየን 264 ሽህ 920.10 የያዙ 9 ሽህ 784 መዛግብት ቀርበው፣ 24 ቢሊየን 983 ሚሊየን 377 ሽህ 330.20 ብር የያዙ 9 ሽህ 651 መዛግብት ውሳኔ በመስጠት የማጥራት ምጣኔዉን በመዝገብ 98.64% መፈጸም ተችሏል፡፡
የቀጥታ ክስና መልስ ተከራክሮ የማሸነፍ አቅም 90.5% ለማድረስ ታቅዶ፤ ብር 26 ቢሊየን 478 ሚሊየን 200 ሽህ 584 ብር በያዙ 7 ሽህ 389 መዛግብት ላይ ክርክር ተደርጎ ብር 4 ቢሊየን 665 ሚሊየን 092 ሽህ 422 ብር የያዙ 3 ሽህ 254 መዛግብት በአሸናፊነት፤ብር 197 ሚሊየን 169 ሽህ 144 ብር የያዙ 381 መዛግብት በተሸናፊነት ተወስነዋል፡፡ አፈጻጸሙ በገንዘብ 96%፣ በመዝገብ 90% ነው፡፡
በሴቶች፣ በህጻናት፣ በወጣቶች፣ በአረጋውያንና በአካል ጉዳተኞች በፍትሐብሄር የቀጥታ ክስና መልስ ተከራክሮ የማሸነፍ አቅምን 90.5% ለመፈፀም በእቅድ ተይዞ ብር 592 ሚሊየን 991 ሽህ 277 ብር የያዙ 1 ሽህ 406 መዛግብት ቀርበዉ ብር 185 ሚሊየን 347 ሽህ 864 ብር የያዙ 598 መዛግብት በማሸነፍ፣ብር 20 ሚሊየን 239 ሽህ 150 የያዙ 35 መዛግብት በመሸነፍ ውሳኔ አግኝተዋል፡፡ አፈጻጸሙ በመዝገብ 94.47%፣ በገንዘብ 90.16% ነው፡፡
ለመንግስት ተቋማት ህግ ምክር አገልግሎትን 100% ለማከናወን በእቅድ ተይዞ 2 ቢሊየን 026 ሚሊየን 947 ሽህ 657 ብር የያዙ 4 ሽህ 208 ጉዳዮች ቀርበው ሁሉም በመከናወናቸዉ አፈፃፀሙ 100% ነው፡፡
የዉል ረቂቅ የመመርመር እና ረቂቅ ውልን የማዘጋጀት ስራዎችን 100% ለማከናወን በእቅድ ተይዞ 240 ቢሊየን 995 ሚሊየን 623 ሽህ 483 ብር የያዙ 8 ሽህ 454 ጉዳዮች የውል ረቂቅ መመርመር እና 444 ሚሊየን 370 ሽህ 628 ብር የያዙ 345 ጉዳዮች የውል ሰነድ ዝግጅት ቀርበዉ ሁሉም በመሰራታቸው አፈጻጸሙ 100% ነው፡፡
ጉዳዮችን በድርድር የመፍታት ምጣኔን 14% ለማድረስ ታቅዶ፣ብር 50 ቢሊየን 674 ሚሊየን 164 ሽህ 264 ብር የያዙ 16 ሽህ 099 መዛግብት ውስጥ ብር 2 ቢሊየን 211 ሚሊየን 241 ሽህ 567 ብር የያዙ 3,390 መዛግብት በድርድር ተቋጭቷል፡፡ አፈጻጸም በመዝገብ 21% በገንዘብ 4% ነው፡፡
የተወሰደን የመንግስትና የህዝብ ሃብት ለማስመለስ የአፈጻጸም ክስ ከቀረበባቸው ጉዳዮች ውስጥ የማስፈጸም አቅምን 97% ለማድረስ በእቅድ ተይዞ በ4 ሽህ 043 መዛግብት ብር 1 ቢሊየን 680 ሚሊየን 314 ሽህ 533.70 የያዙ ጉዳዮች ተፈላጊ እዳ የነበረ ሲሆን ከ3 ሽህ 254 መዛግብት ብር 1 ቢሊየን 275 ሚሊየን 297 ሽህ 256.53 ገቢ ተደርጓል፡፡ ብር 12 ሚሊየን 683 ሽህ 761.62 የያዙ 61 መዛግብት ንብረት በመጥፋት የተዘጉ በመሆኑ አፈጻጸሙ በመዝገብ 98.16%፣ በገንዘብ 99.02% ለማድረስ ተችሏል፡፡
መንግስት በተከሰሳባቸው ጉዳዮች ብር 23 ቢሊየን 030 ሚሊየን 365 284 ሽህ ከያዙ 4 ሽህ 648 መዛግብት ውስጥ ብር 4 ቢሊየን 235 ሚሊየን 284 ሽህ 723 በያዙ 4 ሽህ 308 መዛግብት በማሸነፍ የመንግሰትን ንብረት ከምዝበራ ማዳን ተችሏል፡፡ ሌሎች የዞሩ፣ ክስ የተነሳ ወዘተ ናቸው፡፡
የአቤቱታ አቀባበል ውሳኔ አሰጣጥ እና የአቤቱታ ተፈጻሚነት ምጣኔን 98.5% ለማድረስ ታቅዶ፣ በፍትሐብሄር 6 ሽህ 290 ቀርቦ 6 ሽህ 246 ውሳኔ ያገኙ በመሆኑ አፈፃፀሙ 99.3% ነው፡፡
በይቅርታ ቦርድ እንዲታዩ 1,643 የይቅርታ ጉዳዮች ቀርበው 1,224 ለመስተዳድር ም/ቤት እንዲቀርብ በማድረግ በይቅርታ እንዲለቀቁ ተደርጓል፡፡ ከ515 የፌዴራል ታራሚዎች 314 በይቅርታ ተፈተዋል፡፡
394,678 ሰነዶችን በጥራትና በፍጥነት በመመዝገብና በማረጋገጥ፣ 669,864 የህብረተሰብ ክፍሎችን በማስተናገድ 1,395,367,796.94 ብር ለመንግስት ገቢ ማድረግ ተችሏል፡፡
14 የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ቀርበው ተመዝግበዋል፡፡ ሁሉም በጥራትና በፍጥነት ስለተመዘገቡ አፈጻጸሙ 100% ነዉ፡፡
በክልሉ ተመዝግበው ከሚገኙ 482 ሲቪክ ማህበራት ውስጥ 457 ድጋፍና ክትትል ማድረግ ተችሏል፡፡ አፈጻጸሙም 94.81% ነው፡፡
የሲቪል ማህበረሰብ ክልል አቀፍ ም/ቤት የማደራጀት ስራ ተሰርቷል፡፡ በተጨማሪም ክልል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ቦርድ ተቋቁሟል፡፡
የጥብቅና ፈቃድ ማሳደስ ከነበረባቸው 1,134 ውስጥ 1,060 ያሳደሱ ሲሆን ሌሎቹ በተለያዩ ምክንያቶች ማሳደስ አልቻሉም ፤ በአዲስ ፈቃድ ያወጡ 71 ናቸው፡፡
የተመዘገቡትን ጠበቆች ድጋፍና ክትትል የማድረግ ስራን 80% ለማድረስ ታቅዶ ከ1,134 ጠበቆች ውስጥ ለ1,028 የክትትል እና ድጋፍ የተደረገ በመሆኑ አፈፃፀሙ 90.65% ነው፡፡
አዲስ በወጡት ሁሉም ህጎች ላይ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ 100% ለመስራት ታቅዶ በአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅ እና የጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር፣ የማረሚያ ቤት ኮሚሽንን ማቋቋሚያ አዋጅ እንዲሁም ስለ አስተዳደር ፍትህ እና ተያያዥ ጉዳዮች በአማራ ሚዲያ ኮሮፖሬሽንም በመቅረብም በቢሮው የበላይ እና መካከለኛ አመራሮች እንዲሁም ባለሙያዎች ለወንድ 879፣ ለሴት 127፣ ድምር 1,006 ለሚሆኑ ለማህብረሰብ አካላት ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተሰርቷል፡፡
የሚወጡ መመሪያዎችን በዘላቂነት የመመርመር እና የመመዝገብ ተግባራትን ለመፈጸም የሚያስችል 1 የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት ታቅዶ ተዘጋጅቷል፡፡
በአስተዳደር ተቋማት የሚወጡ መመሪያዎችን ህጋዊነት በመመርመር ከተለያዩ ተቋማት የቀረቡ 141 መመሪያዎች ሁሉም ህጋዊነታቸዉ ተረጋግጦ የመመዝገብ ስራ ተሰርቷል፡፡ የተመዘገቡት ዌብሳይት ላይ ተጭነዋል፡፡
ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት አተገባበር ክልላዊ ሪፖርት ማዘጋጀት1 በዕቅድ ተይዞ 1 ሪፖርት ተዘጋጅቷል፡፡
በሰው መነገድ ሰዎችን ድንበር ማሻገር ወንጀልን መከላከልና ምላሽ መስጠትን 80% ለማድረስ ታቅዶ፤
የ2017 የፍልሰት ክልላዊ ጥምረት ቡድኖችን ሪፖርት በማደራጀት እና የ2018 ዓ/ም የክልሉን የትብብር ጥምረት እቅድ የማዘጋጀት፣
በየደረጃዉ ለሚመለከታቸዉ የፍልሰት ምክር ቤት፣ የትብብር ጥምረትና የስራ ቡድን አባል ተቋማት ማስገምገም እና ሰነዱን አደራጅቶ ለሚመለከታቸዉ አካላት የማድረስ ተግበባራት ተከናውኗል፡፡
የፍልሰት ማስተባበሪያ ምክር ቤት ማቋቋሚያና የትብብር ጥምረት የአሰራርና አደረጃጀት መወሰኛ ደንብ እንዲጸድቅ ክትትል እና ድጋፍ ተደርጓል፤
አዲስ በተፈጠረው የብሔራዊ የትብብር ጥምረት የቡድኖች አደረጃጀት አግባብ የክልሉን፣ የዞንና የሚትሮፖሊታንት ከተሞች የትብብር ጥምረት አደረጃጀቶችን የማደራጀት ስራተጀምሯል፡፡
ከአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ጋር በመተባበር በሰው የመነገድ እና በሕገወጥ መንገድ ሰዎችን ድንበር የማሻገር ወንጀል ዙሪያ የሕግ ማብራሪያ፣ የክልላዊ ጥምረቱ የአሰራር አደረጃጀት እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተደርጓል፤
የአስተዳደር ፍትሕን የማስተዋወቅ እና የማስረፅ ተግባራትን በተመለከተ
አዲስ በወጡት ሁሉም ህጎች ላይ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ 100% ለመስራት ታቅዶ በአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅ እና የጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር፣ የማረሚያ ቤት ኮሚሽንን ማቋቋሚያ አዋጅ ላይ ወንድ 879፣ ሴት 127፣ ድምር 1,006 ለሚሆኑ አካላት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
በአማራ ሚዲያ ኮሮፖሬሽን በመቅረብም በቢሮው የበላይ እና መካከለኛ አመራሮች እንዲሁም ባለሙያዎች ለማህብረሰቡ ስለ አስተዳደር ፍትህ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ተሰርቷል፡፡ አፈፃፀም 100% ነው፡፡
የሚወጡ መመሪያዎችን በዘላቂነት የመመርመር እና የመመዝገብ ተግባራትን ለመፈጸም የሚያስችል 1 የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት ታቅዶ ተዘጋጅቷል፡፡
በአስተዳደር ተቋማት የሚወጡ መመሪያዎችን ህጋዊነት በመመርመር ምዝገባ ማካሄድ እና ዌብሳይት ላይ መጫንን 100%ለማድረስ ታቅዶ መመሪያዎች ለመመዝገብ የሚያስችል የባህር መዝገብ በማዘጋጀት ከተለያዩ ተቋማት የቀረቡ 141 መመሪያዎች ሁሉም ህጋዊነታቸዉ ተረጋግጦ የመመዝገብ ስራ ሰርተናል፡፡ የተመዘገቡትን ወደ ዌብሳይት ተጭነዋል፡፡
የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች
ተቋማዊ አደረጃጀትንና አሰራርን የሚያጠናክሩትንና የተጀመሩትን ህጎች እና አሰራሮች ፈጥኖ ማጠናቀቅ፤
ከተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ውጤታማ ስራዎችን መስራት፤
መዛግብት ላይ የሚታዩ የውሳኔም ሆነ የክርክር ጥራት ማነስ ችግርን ማስተካከል፤
መዛግብት በድርድር የመቋጨት ምጣኔን ማሳደግ፤
ጠበቆች የፍትህ ስርአቱ አጋዥ እንድሆኑ የተጠናከረ የጠበቆች ማህበር አመራር ማደራጀትና ክትትል ማድረግ፤
መሶብ አንድ ማእከል ላይ መሰጠት ያለባቸዉን ተግባራት ለይተን ማስገባትና የገቡትንም ባግባቡ መከታተል፤
ሙያዊ ነጻነትን በመጠበቅ ተጠያቂነትን ማጠናከር፤
የአስተዳደር ፍትህን ዉጤታማነት እና ኮንስትራክሽን ዉል አስተዳደርን ክትትል ማድረግ፤
የመፈጸምና ማስፈጸም አቅምን ማሳደግ የሚችል የአቅም ግንባታ ስራወችን መስራት፤
በወንጀልም ሆነ በፍታብሄር ጉዳዮች የሴቶችን፣ የህጻናትን፣ የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋዊያንን የፍትህ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የትኩረት መስክ በማድረግ አፈጻጸማችንን ማሳደግ ይኖርብናል፡፡
ልዩ ትኩረት በሚያስፈልጋቸው የወንጀል እና የፍታብሄር ጉዳች ላይ የተጠናከረ ልዩ አሰራር መከተል፣
የአቤቱታ አቀራረብ የውሳኔ አሰጣጥና የአፈፃፀሙን ሁኔታ ለመከታተል የሚያስችል ወጥነት ያለው የአሰራር ስርዓት ተዘርግቶ ተግባራዊ የሚደረግበትን የአሰራር ስርዓት ገቢራዊ ማድረግ፤
ለሙስናና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ የሆኑ የመንግሥት ተቋማትን በጥናት ለይቶ የድጋፍ፣ ክትትልና የቁጥጥር ሥራ መሥራት፤
የታችኛዉን መዋቅር አፈጻጸም ሊያሳድግ የሚያስችል ድጋፍና ክትትልን አጠናክሮ ማስቀጠል፤
የመረጃ አደራረስና ልውውጥ ቅልጥፍናና ጥራት ጉዳይ፤ እጅግ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡