21/08/2026
ከ18ሺ ሄ/ር በላይ ማሳ በተለያዩ የመኸር ሰብሎች በዘር መሸፈኑን በምስራቅ ጎጃም ዞን የቢቡኝ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታውቋል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘላለም ጌቴ አንደገለፁት በ2018/219 የምርት ዘመን 18ሺ 88 ሄ/ር ማሳ በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እስከ አሁን 18ሺ 42.5 ሄ/ር ማሳ በዘር ተሸፍኗል ብለዋል።
የምርት ዘመኑን በዘር የመሸፈን እቅድ ለማሳካትና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እስከ አሁን ድረስ 34ሺ 97 ኩንታል ያህል ሰው ሰራሽ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ተሰራጭቷል ።
በተጨማሪም 410ሺ 720 ሜትር ኪብ የሚሆን ተፈጥሮዊ የአፈር ማደበሪያ በማዘጋጀት ከ1ሚሊዮን ኩንታል በላይ ኮምፖስት ወደ አርሶ አደሮች ማሳ አንዲበተን ተደረጓል።
እንደ ወረዳ የሚጠበቀውን የምርት መጠን ለማግኘት የባለሙያ ምክረ ሀሳብን መሰረት ያደረገና ወቅታዊ የሆነ የአረም ስራ ፣ ተባይ የመከላከል ፣ ማዳበሪያ የመጨመርና የደረሱ ሰብሎችን በወቅቱ የመሰብሰብ ተግበር መከናወን አንዳለበት አሳስበዋል።
የግብርና ባለሙያዎችም በቀበሌዎች በመንቀሳቀስ መያዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑንና ለሰብል ምርታማነት መሻሻል ትኩርት ሰጠው እየሰሩ እንደሆነ ተገልጿል።
ሀላፊው ጨምረው አንደተናገሩት " ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" የሚለውን በራስ አቅም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በመሆኑም በምርት ዘመኑ 1ሚሊዮን 111ሺ 511 ኩንታል ያህል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ዘላለም ገልፀዋል።
Woreda Communication