East Gojjam Zone Disaster Risk Management Office

East Gojjam Zone Disaster Risk Management Office ለአደጋ የማይበገር እና የምግብ ዋስትናው የተረጋገጠ ማህበረሰብ ለመፍጠር ተግተን እንሰራለን!

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!"‎‎በምስራቅ ጎጃም ዞን በስናን ወረዳ አስተዳደር በረዕቡ ገበያ ከተማ  ውስጥ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች በስጦታ ቤት ሰርቶ ለማስረከብ በረዕቡ ገበያ  ከተማ 01 እና 0...
07/08/2026

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!"

‎በምስራቅ ጎጃም ዞን በስናን ወረዳ አስተዳደር በረዕቡ ገበያ ከተማ ውስጥ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች በስጦታ ቤት ሰርቶ ለማስረከብ በረዕቡ ገበያ ከተማ 01 እና 02 ቀበሌዎች ውስጥ የቤት የግንባታ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎ ይህ የበጎነት ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የስናን ወረዳ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሽደብር በለጠ ተናግረዋል።

‎ሃላፊዋ በበጎ ተግባራት ላይ መሳተፍ የህሊና እርካታን የሚያጎናፅፍ ከመሆኑም በላይ ለችግር ተጋላጭ የሆኑ አቅመ ደካሞችን ካለባቸው የመጠለያ እጦት ችግር መታደግ ነው ብለዋል።

‎ ከተማችን ውስጥ በሚገኙ በሁለቱም ቀበሌዎች ላይ ለአቅመ ደካሞች በበጎ ፈቃደኞች በሚደረግ ድጋፍ አማካኝነት ቤት በመገንባት ለመስጠት እስከ አሁን ድረስ በእያንዳንቸው ቀበሌ 10 ክፍል ቤት የተገነባ ሲሆን በሁለቱ ቀበሌዎች በድምሩ 20 ክፍል ቤት መገንባቱን ገልፅው የግንባታ ስራው በሁለቱም ቀበሌዎች ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልፀው ለዚህ በጎ ተግባር ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚጠበቅበት መልዕክታቸውንም አስተላልፈዋል።

‎በበጎ ተግባሩ ላይ የወረዳ አመራሮች፣በጎ ፈቃደኞች፣የመንግስት ሰራተኞች፣ የቀበሌ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

‎መረጃው የስናን ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ነው።

በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" የሚደረገውን ሽግግር እውን ለማድረግ የተቋቋመው ቴክኒክ ኮሚቴ በዘርፉ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን ገመገመ።   =======...
07/08/2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" የሚደረገውን ሽግግር እውን ለማድረግ የተቋቋመው ቴክኒክ ኮሚቴ በዘርፉ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን ገመገመ።
======================
ነሀሴ 01/2018 ዓ.ም (ጎዛምን ኮሙዩኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎዛምን ወረዳ"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" የሚደረገውን ሽግግር እውን ለማድረግ የተቋቋመው ቴክኒክ ኮሚቴ በዘርፉ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በመድረኩ እስካሁን በወረዳው በዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን አስመልክቶ ጥቅል ሪፖርት ቀርቦ በተሳታፊዋች ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

የኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ እንዳዘዘ ጓዴ በወረዳው በበጀት ዓመቱ ለአስቸኳይ ጊዜ የመጠባበቂያ እህል ክምችት ለመያዝ በወረዳው 32 ሄ/ር መሬት በሰብል ለማልማት ተለይቶ እስካሁን ድረስ 23.85 ሄ/ር መሬት በማረስ 15.45 ሄ/ር የሚሆነውን መሬት ደግሞ በስንዴ ዘር መሸፈን መቻሉን ገልፀዋል።

የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ ከማሰባሠብ አኳያ በበጀት ዓመቱ 28 ሚሊየን 970 ሽህ 282 ብር ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለመሠብሠብ ታቅዶ እስካሁን በተሰራው ስራ 787 ሽህ 350 ብር መሠብሠብ መቻሉ ተገልጿል።

በቀጣይ የታረሠውን ቀሪ 8.4 ሄ/ር መሬት በፍጥነት በጤፍ ዘር ለመሸፈንና የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድን በቅንጅት በውጤታማነት ለመሰብሰብ አቅጣጫ ተቀምጧል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር  ቴክኒክ ኮሚቴ ሰብአዊ ድጋፍ በራስ አቅም በሳምንቱ ያከናወናቸውን ተግባራት ገመገመ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሐምሌ 30/11...
07/08/2026

የምስራቅ ጎጃም ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ቴክኒክ ኮሚቴ ሰብአዊ ድጋፍ በራስ አቅም በሳምንቱ ያከናወናቸውን ተግባራት ገመገመ ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሐምሌ 30/11/2018 ቴክኒክ ኮሚቴው በዛሬው እለት ባካሄደው መድረክ የእለቱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ገነት በቀለ የምስራቅ ጎጃም ዞን የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ መድረክ ሲከፍቱ የቴክኒክ ኮሚቴው በሳምንቱ በየተቋማቱ ምን ተግባር ፈፀምን በተለይም 5ቱን ፍኖተ ካርታና ፓኬጆችን ግንዛቤ በመያዝ መግባባት፣ማቀናጀት፣ማጥራት፣ማዘጋጀተና ማሻገር የሚሉት ወሳኝ ተግባራችን መሆኑን ተገንዝበን መድረኮችን በመፍጠር ከማኔጅመንቱና ከጠቅላላ ሠራተኞችጋር ከዞን እስከ ወረዳ ባሉ ተቋማትና የማህበረሰብ ክፍሎች ምን ተግባራት እንደተከናወኑ ሁሉም ተቋማት እንዲየብራሩ ከገልፁ በኋላ
የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት የሃብት አሰባሰብ ተወካይ ቡድን መሪ አቶ ያረጋል መንጋው በሳምንቱ የተከናወኑና የመጡ ለውጦችን በዝርዝር የአፈፃፀም ሰብአዊ ድጋፍ በራስ አቅም የተጠቃለለ ሪፖርት ካቀረቡ በኋላ
በቀረቡት አጀንዳዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የተወያየ ሲሆን በዋናነት
-ተቋማዊ ቅንጅታዊ አሠራራችን ምን ይመስላል
-በምግብ እራስን መቻል አፈፃፀም
-ተለይተው የልታረሱና ያልተዘሩ መሬቶች
-የሪፖርት ግንኙነት ከመቀናጀት አንፃር ምን ይመስላል
_እስከ ታች ለመግባባት የተሰሩ ተግባራት
_ከአመራሩ፣ከሠራተኛው የገንዘብ አሰባሰብ
_ቴክኒክ ኮሚቴው ለተቋሙ ሞዴል ስለመሆን
_ተግባራትን ጀምሮ ከመጨረስ አኳያ በሚሉ
ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ገለፃ ከተደረገ በኋላ
እያንዳንድ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት ከተቋማቸው ተግባር አስተሳስረው በሳምንቱ የተከወኑ ሥራዎችን በተለይም ከስደትተመላሾች፣ተፈናቃዮች፣የጎዳና ተዳዳሪዎች ፣በድንገተኛ አደጋ ተጋላጮች፣ የከተማና የገጠር ሴፍቴኔት ተጠቃሚዎችን መሠረት አድርገው የተፈጠረ ግንዛቤና የተሠሩ ተግባራትን ሁሉም የቴክኒክ ኮሚቴዎች ከተቋማቸው ተግባር ክንውን በመነሳት ሪፖርት ካቀረቡ በኋላ በጥያቄና አስተያየተ ዳብሮ ወ/ሮ ገነት በቀለ በማጠቃለያ ንግግራቸው የትኩረት አቅጣጫ ያሏቸውን የተለዩ መሬቶች ጊዜ ሳይሰጣቸው ከወዲሁ ታርሰው በዘር እንዲሸፈን ፣በገንዘብ ማሰባሰቡ በኩል ህጋዊ ደረሰኝ ተዘጋጅቶ በሁሉም ዘርፍና ተቋማት ሠራተኞችን በማሶሰን ፈጥነን መስራት እንዳለባቸው በመግለፅ ከአጀንዳ ወጥተን ወደ ተግባር እንቅስቃሴ መገባት እንደሚገባ በመጠቆም በመጨረሻም በሱፐር ኢሊኖ ስጋት የተደቀነብን በመሆኑ የቅድመ ጥንቃቄና የዝግጅት ስራ መሠራት እንደሚገባ የስራ መመሪያ በመስጠት ተጠናቋል።

በምስራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ «ከተረጅነት ወደ ምርታማነት  ለመሸጋገር ከሚያስችሉ ተግባራት አንዱ የሆነው » የስንዴ ቡቃያ ሰብል አሁናዊ ቁመና ተጎበኘ ። በምስራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ...
07/08/2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ «ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር ከሚያስችሉ ተግባራት አንዱ የሆነው » የስንዴ ቡቃያ ሰብል አሁናዊ ቁመና ተጎበኘ ።

በምስራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ «ከተረጅነት ወደ ምርታማነት» ለመሸጋገር በተከናወነው የከተማ ግብርና ንቅናቄ በ7 ሄክታር መሬት ላይ የለማው የስንዴ ዘር ሰብል የመስክ ምልከታና ጉብኝት ተካሂዷል።በጉብኝቱ ላይ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፥ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸው ተገልጿል።

በጉብኝቱ ወቅት እንደተገለጸው፥ «ከተረጅነት ወደ ምርታማነት» ለመሸጋገር የተዘራው የ7 ሄክታር ስንዴ ቡቃያ ሰብል በጥሩ ቁመና ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ የአካባቢውን ማህበረሰብ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ራስን በምግብ ለመቻል እየተደረገ ላለው ርብርብ ትልቅ ማሳያ መሆኑ ተጠቅሷል።

07/08/2026
07/08/2026

Address

Debra Markos

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when East Gojjam Zone Disaster Risk Management Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share