13/08/2026
የደ/ብርሀን ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የ2018ዓ .ም እቅድ ግምገማ እና የ2019 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ መመድርክ አካሄደ ።
በመድርኩ የተሳተፉ የተቋሙ ሰራኛ ፣ምስጉን ግብር ከፍዮች፣የከተማው አመራሮች ፣የክፍለተማ ስራ አስፈፃሚዎች እና አጋርና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የደ/ብርሀን ከተማ ስተዳደር ተቀዳሚ ከቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በመክፈቻ ንግግራቸው ገቢ መሰብሰብ እንደከተማ የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር እንደሆነ ገልፀው የ2018 ዓ .ም የገቢ እቅድ መሳካት የገቢተቋሙ ሰራተኛች ጠረት የጎላ እንደሆነ እውቅና ሰጥተዎል። በተጨማሪም የ2019ዓ.ም እቅድ ለማሳካት ከፍተኛ ጥረት የሚጠይቅ መሆኑንግልፀው ከተማ አሰተዳደሩ በበጀት እንደሚደግፉ ገልፀዎል።
የደ/ ብርሀን ከተማ ገቢዋች መምሪያ እቅድ የስራ ሂደት አሰተባባሪ አቶ ገዛህኝ ነገሰ በ2018 2.75 ቢሊዬን ውይም የእቅዱን 94.08% ገቢ መሰብሰቡን ገልፀው
መደበኛ ገቢ 1.77ቢሊዬን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የተሰበሰበ ብር 1.99 ቢሊዬን አፈፃፀም 112% የአገልግሎት ገቢ ከታቀደው 1.15 ቢሊዬን አቅዶ ብር የተሰበሰበ 756.01ሚሊየን አፈፃፀም 65.65% ገቢ የተሰበሰበ መሆኑን ገለፁ። አያይዘውም ከ2017በጀት አመት ከተሰበሰበው ገቢ ጋር ሲነፃፀር የብር 1.06 ቢሊዬን ብር ወይም 62.6% እድገት አንዳለው በመግለፀ የ2019 ዓ.ም እቅድ 5.5 ቢሊዮን ብር ለማሳካት በትጋት መስራት እንደሚገባ ገልፀዎል።
አቶ አበባየሁ ምገስ የደ/ብርሀን ከተማ ገቢዎች
ለገቢው ማደግ አስተዎፅኦ ያላቸው የግብርን አስፈላጊነትን በመርዳት ግብራየቸውን በወቅቱ በመክፈል የከተማችን ግብር ከፋዩች ፣ከክፍለ ከተማ እስከ መምሪያ ያለ ባለሞያ እና አመራር ለገቢ አሰባሰቡ ትኩርት ሰጥቶ በመሰራቱ ፣ከቀበሌ እስከ መምሪያ ያለው አመራር ግባአት ከማሟላት ጀምሮ ክትትል ናድጋፍ በማድርግ የጋራ ውጤት መሆኑን ገልፀው በቀጣይ ለ2019 በጀት አመት እቅድ ለማሳካት በ2018ዓ.ም መደበኛ ገቢ ከ100% በላይ የተፈፀመበትን ጥንካራጉን በማሰቀጥል እና የአገልግሎት ገቢ ላይ የታዩትን ክፍተቶች በመለየት የእቅድ አካል በማድርግ በቅንጅት በመስራት የተሻለ ገቢ በመሰብሰብ የከተማችን ህዝብ የልማት ተጠቃሚ ማድርግ ይገባል ብለዎል። በመጨርሻም በ2018ዓ.ም በገቢ አሰባሰቡ የተሻለ አፈፃፀም ላላቸው የገቢተቋሙ ሰራተኞች፣ ለክፍለከተሞቾ፣ ለምስጉን ግብር ከፋዮች እና አጋርና ባለድርሻ አካላት እውቅና እና ሸልማት ተሰጥቶል።