Debre Birhan city Communication Affairs Office

Debre Birhan city Communication Affairs Office ይህ ገጽ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ነው

03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ምን አሉ

"ሚሊሻው የሕዝባዊነትን ትርጉም በተግባር ያሳየ ኃይል ነው" ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ   የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ግንቦት 29/2018 ዓ.ም በክልል ደረጃ የሚካሄደውን የሚሊሻ 30ኛ ዓመት...
03/06/2026

"ሚሊሻው የሕዝባዊነትን ትርጉም በተግባር ያሳየ ኃይል ነው" ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ

የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ግንቦት 29/2018 ዓ.ም በክልል ደረጃ የሚካሄደውን የሚሊሻ 30ኛ ዓመት የምሥርታ በዓል እና የእውቅና መርሐ ግብር አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ የሚሊሻ 30ኛ ዓመት ክብረ በዓል የሚሊሻውን ታሪካዊ ተጋድሎ እና መስዋዕትነቱን ለመዘከር የታሰበ ነው ብለዋል።

በዓሉ ለሚሊሻ አባላት እና ለቤተሰቦቻቸው ክብር እና ምስጋና ለማቅረብ፤ ተቋማዊ ሪፎርም እና ዝግጁነቱን ለማረጋገጥ፤ የሕዝቡን እና የሚሊሻውን ትስስር ለማጥበቅ እና ሌሎች ዋና ዋና ዓላማዎች እንዳሉትም አንስተዋል።

ግንቦት 29/2018 ዓ.ም የአማራ ክልል ሚሊሻ የ30 ዓመታት የጀግንነት እና የሕዝባዊነት ጉዞ የሚከበርበት ልዩ ቀን እንደኾነም ገልጸዋል።

የሚሊሻ 30ኛ ዓመት ክብረ በዓል ሲባል የሚሊሻ ምስረታ ዕድሜው 30 ዓመት ነው ለማለት ሳይኾን በክልል ደረጃ የተቋቋመበትን ለመግለጽ እንደኾነም ተናግረዋል። ሚሊሻ ከንጉሠ ነገሥቱ ዘመን ጀምሮ ዘመናዊ ወታዳር ባልነበረት ወቅትም ነበር ብለዋል።

ባለፉት ሦሥት አስርት ዓመታት የክልሉ ሚሊሻ በርካታ ታሪካዊ ምዕራፎችን ማለፉንም ገልጸዋል።

ሚሊሻው መደበኛ የሥራ ድርሻውን ሳያስተጓጉል በአንድ እጁ አምራች በሌላ እጁ ደግሞ የሰላም ዘብ በመኾን "የሕዝባዊነትን ትርጉም በተግባር ያሳየ ኃይል ነው" ብለዋል።

ሀገራዊ የሉዓላዊነት ፈተናዎች እና ክልላዊ የጸጥታ ስጋቶች ባጋጠሙ ጊዜያት ሚሊሻው ከመከላከያ ሠራዊት እና ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመሰለፍ በደም እና በአጥንቱ ደማቅ ታሪክ መጻፉን ገልጸዋል።

በክልሉ አንጻራዊ ሰላም እንዲመጣ የበኩሉን ሚና ተጫውቷልም ብለዋል፡፡

ኮሚሽኑ ይህንን 30ኛ ዓመት በዓል ሲያከብር ወደፊት የክልሉን ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ማስከበር እና የሰላም ጥሪ ተግባራት ላይ በትኩረት ለመሥራት ታሳቢ አድርጓል ነው ያሉት።

አሚኮ

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁየአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡ምርጫውን አ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ

የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

"ምርጫው የኢትዮጵያን የወደፊት የዴሞክራሲ አቅጣጫ ያመላከተ ነው" ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማ መንገድ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።...
02/06/2026

"ምርጫው የኢትዮጵያን የወደፊት የዴሞክራሲ አቅጣጫ ያመላከተ ነው" ምርጫ ቦርድ

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬታማ መንገድ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

ቦርዱ በአሁኑ ሰዓት የድምጽ መቁጠር እና የማረጋገጥ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም ገልጿል።

የቦርዱ ሠብሣቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ በጋዜጣዊ መግለጫው
የምርጫ ሂደቱ ውጤታማ እና የኢትዮጵያን የወደፊት የዴሞክራሲ ሂደት የሚያመላክት ስኬት የተመዘገበበት መኾኑን ነው የገለጹት።

የምርጫ ውጤቱን ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ወደ ምርጫ ክልሎች፣ የምርጫ ክልሎች ደግሞ ወደ ማዕከላዊ ቋት ከላኩ በኋላ ምርጫ ቦርድ የማረጋገጥ ሥራ አከናውኖ አጠቃላይ ውጤቱን ይፋ የሚያደርግ ይኾናል ነው ያሉት ሠብሣቢዋ።

አሚኮ

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ  ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ...
02/06/2026

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ክልልም ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው የክልላችን ሕዝብ ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል፤ በአማራ ክልል ምርጫ ማካሄድ ድምጽ ከመስጠት ባሻገር ነው" ብለዋል።

በክልላችን ምርጫ እንዳይካሄድ፤ ዜጎች መብታቸውን እንዳይጠቀሙ፤ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠርት፣ ክልሉ ሁልጊዜ በድህነት እና በግጭት ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጉ የውይይት እና የሰላም ተቃራኒ ኃይሎች ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል። "ይሁን እንጂ በሕዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ኃይላችን ጀግንነት እነርሱ የፈለጉት ሳይኾን ሕዝብ የፈለገው ኾኗል" ነው ያሉት።

የክልሉ ሕዝብ ትናንት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያሳየው ተሳትፎ፣ ጽናት እና ትዕግሥት የብልሃት እና የጥበብ ምንጭ መኾኑን ያሰመሰከረበት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ምርጫው ሕዝቡ ለፈተና የማይበገር፤ በዛቻ እና በማስፈራሪያ የማይሰበር፣ ለሰላም እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የትኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል ያሳየበት እንደሆነ አስታውቀዋል። "የክልላችን ሕዝብ በትናንትናው ምርጫ የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በሕዝብ ድምጽ እንጂ በኃይል አለመኾኑን ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ነው" ብለዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ ሰላም ወዳድነቱን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈላጊነቱን፤ በሕግና በሕዝብ ይሁንታ ለሚጸና መንግሥት ቀናዒነቱን በግልጽ እንዳሳየም አብራርተዋል። ለዚህ ደግሞ የከበረ ምስጋናዬን ከጥልቅ አክብሮት ጋር ማቅረብ እወዳለሁ ነው ያሉት።

"ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምርጫው በክልላችን በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ለሀገር መከለካያ ሠራዊት፣ ለክልላችን የጸጥታ ኃይል፣ በየደረጃው ለሚገኙ የክልላችን አመራሮች እና ለመላው የክልላችንን ሕዝብ በራሴ እና በአማራ ክልል መንግሥት ስም የላቀ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ለሀገር እና ለሕዝብ በአንድነት መሥራት ምን አይነት ስኬታማ ውጤት እንደሚያስገኝ ምርጫው ሕያው ምስክር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በምርጫው ጫፍ ረገጥ አስተሳሰቦች እስከ አደረጃጀቶቻቸው በሕዝብ ደምጽ ከሽፈዋል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ክልልም ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው የክልላችን ሕዝብ ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል፤ በአማራ ክልል ምርጫ ማካሄድ ድምጽ ከመስጠት ባሻገር ነው" ብለዋል።

በክልላችን ምርጫ እንዳይካሄድ፤ ዜጎች መብታቸውን እንዳይጠቀሙ፤ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠርት፣ ክልሉ ሁልጊዜ በድህነት እና በግጭት ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጉ የውይይት እና የሰላም ተቃራኒ ኃይሎች ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል። "ይሁን እንጂ በሕዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ኃይላችን ጀግንነት እነርሱ የፈለጉት ሳይኾን ሕዝብ የፈለገው ኾኗል" ነው ያሉት።

የክልሉ ሕዝብ ትናንት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያሳየው ተሳትፎ፣ ጽናት እና ትዕግሥት የብልሃት እና የጥበብ ምንጭ መኾኑን ያሰመሰከረበት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ምርጫው ሕዝቡ ለፈተና የማይበገር፤ በዛቻ እና በማስፈራሪያ የማይሰበር፣ ለሰላም እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የትኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል ያሳየበት እንደሆነ አስታውቀዋል። "የክልላችን ሕዝብ በትናንትናው ምርጫ የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በሕዝብ ድምጽ እንጂ በኃይል አለመኾኑን ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ነው" ብለዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ ሰላም ወዳድነቱን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈላጊነቱን፤ በሕግና በሕዝብ ይሁንታ ለሚጸና መንግሥት ቀናዒነቱን በግልጽ እንዳሳየም አብራርተዋል። ለዚህ ደግሞ የከበረ ምስጋናዬን ከጥልቅ አክብሮት ጋር ማቅረብ እወዳለሁ ነው ያሉት።

"ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምርጫው በክልላችን በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ለሀገር መከለካያ ሠራዊት፣ ለክልላችን የጸጥታ ኃይል፣ በየደረጃው ለሚገኙ የክልላችን አመራሮች እና ለመላው የክልላችንን ሕዝብ በራሴ እና በአማራ ክልል መንግሥት ስም የላቀ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ለሀገር እና ለሕዝብ በአንድነት መሥራት ምን አይነት ስኬታማ ውጤት እንደሚያስገኝ ምርጫው ሕያው ምስክር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በምርጫው ጫፍ ረገጥ አስተሳሰቦች እስከ አደረጃጀቶቻቸው በሕዝብ ደምጽ ከሽፈዋል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት።

02/06/2026

በድህረ ምርጫው የሚመጣ ውጤትን ለመቀበል ዝግጁ ነን!!

ወ/ሮ ሀያት ኡስማን በደብረ ብርሃን ምርጫ ክልል የአርጎባ እንድነት ጀበርቲ ፓርቲ በመወከል ለህዝብ ተወካዮች እጩ ተወዳዳሪ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አክለውም ምርጫው በሰላማዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናወኑን ገልጸው በድህረ ምርጫ ውጤት ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል

02/06/2026

የህዝብ ድምጽ ክቡር ነው!!

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን በር ል ለህዝብ ተወካዮች የሚወዳደሩት እና የጋራ የምክር ቤቱ ምክትል ሠብሣቢ ረዳት ፕሮፌሰር ዳምጠው ተሰማ የህዝብ ደምጽ ክቡር ነው ብለዋል።

አክለውም የድህረ-ምርጫ ውጤትን በጸጋ ለመቀበል ዝግጁ መኾንናቸውን ጠቁመዋል።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ የፈተና መስጫ ቀናትን ይፋ አደረገ።  የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም  የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ  ፈተናዎች የሚሰጡ...
02/06/2026

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ የፈተና መስጫ ቀናትን ይፋ አደረገ።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች የሚሰጡበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሰረት የ6ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 08 እስከ ዐ9/2018 ዓ.ም ይሰጣል። የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ደግሞ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ክልላዊ ፈተናውን እንደሚወስዱ ነው ከትምህርት ቢሮው የተገኘ መረጃ የጠቆመው።
አሚኮ

በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ፣ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።‎የባሕርዳ...
02/06/2026

በባሕርዳር ከተማ አስተዳደር የተካሄደው 7ኛው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ፣ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር‎​ ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ዋለልኝ ቢምረው እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 1 የምርጫ ክልል እና 164 የምርጫ ጣቢያዎች የተካሄደው ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሰላማዊ፣ ስልጡን እና ስኬታማ በሆነ መንገድ ተጠናቋል ብለዋል።

‎ኮማንደር ዋለልኝ ቢምረው እንደገለፁት በከተማ አስተዳደሩ የተካሄደው ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ እና ስኬታማ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጸጥታ አባላት ምስጋና አቅርበዋል።

ለመላው ሰላም ወዳድ የከተማው ማህበረሰብ፣ከምርጫው መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ማጠቃለያው ድረስ ሕግን በማክበር፣ ሰላምን በማስቀደም እና ከፍተኛ የዜግነት ኃላፊነት ስሜትን በማሳየት ለቆማችሁ፤​ የጸጥታ አካላት ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ የሕዝብን ደህንነት ለመጠበቅና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ሌት ከቀን ያለመታከት በቁርጠኝነት ለወጣቹህ ለወረዳቹህ ለደከማችሁ፤ በሂደቱም ላይ ንቁ ተሳትፎ ላደረጋችሁ በሙሉ፤ ​በራሴ እና በፖሊስ መምሪያው ስም ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን እና አክብሮቴን አቀርባለሁ ብለዋል።

02/06/2026

በደብረ ብርሃን ከተማ ምርጫ ክልል የሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የድምፅ ቆጠራ ውጤት ይፋ እያደረጉ ይገኛሉ።



Address

Amhara
Debre Birhan
251

Telephone

2516813085

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Birhan city Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Debre Birhan city Communication Affairs Office:

Share