Legehida Woreda Prosperity Party/ለገሂዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ/

  • Home
  • Ethiopia
  • Dessie
  • Legehida Woreda Prosperity Party/ለገሂዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ/

Legehida Woreda Prosperity Party/ለገሂዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ/ Peblic service

የፓይለት የተማሪ ምዝገባ በስረ-ገደል አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ እና መካከለኛ ት/ቤት እየተካሄ ይገኛል========    ========       ======የለገሂዳ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ለሚመለከ...
21/08/2026

የፓይለት የተማሪ ምዝገባ በስረ-ገደል አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ እና መካከለኛ ት/ቤት እየተካሄ ይገኛል
======== ======== ======
የለገሂዳ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ለሚመለከታቸዉ የትምህርት ባለድርሻ አካላት የተማሪ ምዝገባ ዙሪያ የንቅናቄ መድረክ ማካሂዱ ይታወቃል፤ በዚህም የ03 በስረገደል ቀበሌ ለፓይለት የተማሪ ምዝገባ ስራዉ ከተመረጡ ቀበሌዎች ዉስጥ አንዱ ነዉ፡፡
የ03 ስረ-ገደል ቀበሌ አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ እና መካከለኛ ት/ቤት ዛሬ ነሃሴ 15/2018 ዓ.ም ሁሉም ባለድረሻ አካላት በተገኙበት የተማሪ ምዝገባ ስራዉን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በትምህርት ቤቱ ሲያስተባብሩ ያገኘናቸው የለገሂዳ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ እና የቀበሌው ምድብተኛ አመራር አቶ መስዑድ ሲራጅ ትምሀርት የሃገር ችግር መፍቻ ቁልፍ መሳሪያ ነው ያሉ ሲሆን፤ አሁን ላይ ትውልዱን በትምህርት መቅረጽ ካልተቻለ ቀጣይነት ያለው የሃገርን ሁለንተናዊ እድገት ማረጋገጥ አይቻልም ብለዋል፡፡
በዚህም ማንኛውም ህጻን የከብት ጭራ እንዳይከተል በሚል በዛሬው እለት የ2018/19 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ከትምህርት አመራሩ እስከ ማህበረሰቡ የተደረገው ርብርብ ይበል የሚያሰኝ ነው ያሉት አቶ መስዑድ ለተግባሩ አስዋጽዖ ላደረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በምዝገባው የተደረገው እንቅስቃሴ መማር ማስተማሩን ለማስጀመር መደገም እንዳለበት መልእክታቸውን ያስተላለፉት የለገሂዳ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ም/ኃላፊ አቶ ሱለይማን ከበዴ ናቸው፡፡
የትምህርት ቤቱ ኮሚቴ አቶ ሃብታሙ መኮንን እና የትምህርት ቤቱ የወመህ ሰብሳቢው አቶ ሙሃመድ ሰይድ በበኩላቸው የ2018/19 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ለማሳካት ከወረዳ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች በጋራ በመሆን የቅድመ ዝግጅት ተግባር በአጭር ጊዜ በማከናወን ዛሬ ላይ ሁሉም ባለድረሻ አካላት በተገኙበት ተማሪዎችን በማስመዝገብ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
ሲመዘገብ ያገኘነው የ8ኛ ክፍል ተማሪ አሊ ሙሃመድ ዛሬ ላይ ለመመዝገብ መምጣቱን ገልጾ፤ መስከረም አምስት ለሚጀመረው ትምህርት የመማሪያ ቁሳቁስ አሞልቸ ለመጀመር ዝግጁ ነኝ ብሏል፡፡
የስረ-ገደል አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ እና መካከለኛ ት/ቤት ርዕሰ መምህሯ ወ/ሮ ሰናይት ወንዶሰን በበኩሏ የ2018/19 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ለማከናወን ከልየታ ጀምሮ የቅድመ ዝግጀት ተግባር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እያከናወኑ መቆየታቸውን ገልጻ፤ ዛሬ ላይ በንቅናቄ የምዝገባ ሂደቱ እየተካሄደ ይገኛል ብላለች፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን ለጋሂዳ ወረዳ የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ለፖይለት በተመረጠ  ማጅቴ አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት እየተካሄደ ይገኛል።======      ===========      ...
21/08/2026

በደቡብ ወሎ ዞን ለጋሂዳ ወረዳ የ2019 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ለፖይለት በተመረጠ ማጅቴ አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት እየተካሄደ ይገኛል።
====== =========== ===========
በደቡብ ወሎ ዞን በለገሂዳ ወረዳ ለ2019 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ በይፋ የተጀመረ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ በፓይለት ደረጃ በተመረጠው ማጅቴ አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በስኬት እየተካሄደ ይገኛል።
ወላጆች እና አሳዳጊዎች ልጆቻችሁን በጊዜ በመመዝገብ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ዝግጁ እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን

በለገሂዳ ወረዳ የ2019 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች የፓይለት ምዝገባ በብርብርቲ አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በይፋ ተጀመረ======    =======     ========በደቡብ ወሎ ዞ...
21/08/2026

በለገሂዳ ወረዳ የ2019 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች የፓይለት ምዝገባ በብርብርቲ አጠቃላይ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በይፋ ተጀመረ
====== ======= ========
በደቡብ ወሎ ዞን በለገሂዳ ወረዳ የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች የፓይለት ምዝገባ ዛሬ ነሃሴ 15/ 2018 ዓ.ም በ05 ብርብርቲ ቀበሌ በሚገኘው ብርብርቲ አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መካሄድ ጀምሯል።
በምዝገባ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የቀበሌው ማህበረሰብ፣ የትምህርት ቤቱ የስልጠና ቦርድ፣ የወላጅ፣ መምህርና ተማሪ (ወተመህ) አባላት እንዲሁም የወረዳው አስተባባሪ አመራሮች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የለገሂዳ ወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይማም አበበ እንደገለጹት፤ ወላጆችና ማህበረሰቡ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በበጎ በመገንዘብ ልጆቻቸውን በወቅቱ ማስተማር እንዳለባቸው አሳስበዋል። አክለውም ወቅቱ የሚጠይቀውን ዘመናዊ እውቀትና ክህሎት ለልጆች ማቅረብ የቀዳሚነት ተግባር መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
ትምህርት ቤቶች ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ዝግጁ በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ ወላጆች ልጆቻቸውን በጊዜ በመመዝገብ ለትምህርት ዝግጁ እንዲያደርጉ ጥሪ ተ አስተላልፏል።

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!"ለገሂዳ ወረዳ ​በ05 ብርብርቲ ቀበሌ የአቅመ ደካማ ቤት በአዲስ መልክ መገንባት ተጀመረ!።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።​"በጎነት ለኢትዮጵያ ...
20/08/2026

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!"
ለገሂዳ ወረዳ ​በ05 ብርብርቲ ቀበሌ የአቅመ ደካማ ቤት በአዲስ መልክ መገንባት ተጀመረ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
​"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሀሳብ በተከናወነው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በ05 ብርብርቲ ቀበሌ የሚገኙ አቅመ ደካማ ወገን የመኖሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ በአዲስ መልክ መገንባት ተጀምሯል ​የተግባሩ ዓላማ፡ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችን የመኖሪያ ቤት ችግር በመቅረፍ የተሻለና አስተማማኝ የመኖሪያ ቦታ መፍጠር።ለጉዳት ተጋላጭ የነበረውን አሮጌ ቤት ሙሉ በሙሉ በአዲስ መዋቅርና ጥራት ባላቸው ቁሳቁሶች የመገንባት ሥራ።​የተቀናጀ ጥረት፡በግንባታው ሂደት የቀበሌው አመራሮች፣ የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና የማህበረሰብ አባላት በጉልበታቸው፣ በገንዘባቸውና በቁሳቁስ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
​በጎነት የኢትዮጵያውያን የቆየ የመረዳዳት እሴትና የሀገራችን ከፍታ መሰረት በመሆኑ፣ መሰል አወንታዊ ተግባራት በሁሉም አከባቢዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።

20/08/2026
"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በደቡብ ወሎ ዞን በለገሂዳ ወረዳ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የአቅመ ደካሞችን ህይወት የሚታደግ የበጎ ፈቃድ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ።...
20/08/2026

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"
በደቡብ ወሎ ዞን በለገሂዳ ወረዳ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የአቅመ ደካሞችን ህይወት የሚታደግ የበጎ ፈቃድ ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
​በዛሬው ዕለት በተካሄደው የተቀናጀ የቤት ጥገና እና ግንባታ ዘመቻ በአንድ ቀን ጀምበር ብቻ የሚከተሉት አበራች ተግባራት ተከናውነዋል፦
​🏚️ 11ነባር ቤቶች፦ ሙሉ በሙሉ የጥገና ስራ ተደርጎላቸዋል
​🏗️ 10 አዲስ ቤቶች፦ ሙሉ በሙሉ አዲስ ግንባታ ተጀምረዋል
ይህ በአንድ ቀን ውስጥ የተመዘገበው ውጤት የአካባቢው ማህበረሰብ እና የበጎፍቃደኛ ዜጎች ያደረጉት የጉልበት የገንዘበ ድጋፍ የሚበረታታና የሚመሰገን ተግባር በመሆኑ አብሮነት፣ መረዳዳት እና ለበጎ ተግባር ያለው ቁርጠኝነት ማሳያ ነው።በቀጣይም የመክረምት የዜጎችን ችግር የሚቀርፉ የመልካምነት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በአቅጣጫ ተቀምጧል::

➜የ2018 የተማሪ ምዝገባ እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ.ም የተማሪ ምዝገባ እቅድ ኦሬንቴሽን የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚ደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ የ...
18/08/2026

➜የ2018 የተማሪ ምዝገባ እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ.ም የተማሪ ምዝገባ እቅድ ኦሬንቴሽን የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
ደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ የለገሂዳ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የ2018 የተማሪ ምዝገባ እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ.ም የተማሪ ምዝገባ እቅድ ኦሬንቴሽን የንቅናቄ መድረክ ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በወይን አምባ ተካሂዷል።
መድረኩን በይፋ የከፈቱት የለገሂዳ ወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ይማም አበበ ሲሆኑ፣ በንግግራቸው የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪ ምዝገባን በሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ተሳትፎ በማከናወን ሁሉንም የትምህርት ዕድሜ ሕፃናት ወደ ትምህርት ቤት ማስገባት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ የክረምት ሥራዎችን አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የለገሂዳ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሱለሂማን ከበደ ሲሆኑ፣ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ኦሬንቴሽን በዋና ኃላፊው አቶ አወል አሸናፊ ቀርቦ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
በመድረኩ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ የቀበሌ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የቀበሌ ሥራ አስኪያጆች፣ የትምህርት ወኪሎች፣ የወረዳ ጠቅላላ አመራሮችና የትምህርት ጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
በመጨረሻም የ2019 የተማሪ ምዝገባ በታቀደው መሠረት በቅንጅት፣ በኃላፊነትና በሁሉም አካላት ንቁ ተሳትፎ በማከናወን ሁሉንም የትምህርት ዕድሜ ሕፃናት ወደ ትምህርት ቤት ለማስገባት የጋራ ቁርጠኝነት ተገልጿል።

በደቡበ ወሎ ዞን ቀለገሂዳ ወረዳ የ01ማጀቴ ቀበሌ  ስገዴ ስንዴ ክላስተር አሁናዊ ቁመና በከፊል
18/08/2026

በደቡበ ወሎ ዞን ቀለገሂዳ ወረዳ የ01ማጀቴ ቀበሌ ስገዴ ስንዴ ክላስተር አሁናዊ ቁመና በከፊል

በደቡበ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ የ08 ዜና አምባ ቀበሌ የስንዴ ክላስተር አሁናዊ ቁመና በከፊል
18/08/2026

በደቡበ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ የ08 ዜና አምባ ቀበሌ የስንዴ ክላስተር አሁናዊ ቁመና በከፊል

Address

Dessie

Telephone

+251922940085

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Legehida Woreda Prosperity Party/ለገሂዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share