Zinabu Wolde

Zinabu Wolde Gedeo Zone Chief Administrator
Researcher and Lecturer at Dilla University
(1)

07/09/2026
07/09/2026
07/09/2026
06/09/2026

ኢትዮጵያ እየተከተለችው ያለው ብዝሃ መር የኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው

ዲላ፤ ጳጉሜን 1/2018 (ኢዜአ) ፦ኢትዮጵያ እየተከተለችው ያለው ብዝሃ መር የኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።

ቀደም ሲል በግብርና መር ኢኮኖሚ ልማት ላይ ተወስና የቆየችው ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት ወደ ብዝሃመር የኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂ ተሸጋግራለች።

የኢትዮጵያን እምቅ የመልማት አቅሞች በመገንዘብ የግብርና ልማትን ጨምሮ በኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ አይሲቲና የማዕድን ዘርፍ ዋነኛ የልማት ምሰሶዎች ሆነው እየተሰራባቸው ይገኛሉ።

በእነዚህ ዘርፎችም ላይ በተሰሩ ስራዎች ሀገሪቱ እመርታዊ እድገትና ማንሰራራት ላይ ለመሆኗ በርካታ ተጨባጭ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንትና የተፈጥሮ ሃብት ተመራማሪ ሐብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)፤ የልማት ስትራቴጂው ብዝሃ መሆኑ እና ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም መደረጉ ለተመዘገበው ስኬት የላቀ ትርጉም አለው ብለዋል።

የብዝሃ ኢኮኖሚ እድገት አማራጭን ከመከተል ባለፈ በተለይም በግብርናው ዘርፍ አዳዲስ ኢንሼቲቮችን በመተግበርና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ እመርታ መታየቱን አስረድተዋል።

በስንዴ ልማት፣ በቡና ልማት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ሌሎች የግብርና ዘርፎች ውጤቱና ስኬቱ አስደናቂ መሆኑን ነው ያነሱት።

የተፈጥሮ ሃብትና መሬት አስተዳደር ተመራማሪና የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት ፤ እምቅ የተፈጥሮ ሃብቶችን በመጠቀም እየተሄደበት ያለው የልማት ዕቅድ በአጭር ጊዜ ውጤት አምጥቷል።

በተለይም በግብርናው ዘርፍ የተጀመረው የተቀናጀ የልማት ጥረት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነትና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰረት መሆኑን አንስተዋል።

ከመደበኛ የምርት ወቅት በተጨማሪ የመስኖ ልማት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸው፣ የዘርፉ እመርታ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥልም ያላቸውን እምነት ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ የታየው እመርታ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት ለመውጣትና ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት መሰረት የሚጥል መሆኑን ምሁራኑ ገልጸዋል።
Ethiopian News Agency #ኢዜአ

03/09/2026

Address

Gedeo , Ethiopia, Wolaita Sodo, Ethiopia, Arba Mintch, Ethiopia , Addis Ababa
Dila
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zinabu Wolde posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share