01/05/2026
የጌዴዞ ዞን ዋና አስተዳደር ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር በእርግጥም የህዝብ ልጅ ነው!
በቀን 22/8/2018 ዓ.ም በወርቃ ሳካሮ ቀበለ የህዝብ የውይይት መድረክ የተደረገ ሲሆን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር፣ የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ስሳይ ታደሰ እና ሌሎች የሥራ ኃላፍዎች በተገኙበት የውይይት ስብሰባ ተደርጎ የተለያዬ የልማት ጥያቄዎች ከተሳታፍዎች ተነስቶ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል
የተነሱ ጥያቄዎች
1ኛ ከገደብ - ጎትቲ መንገድ አስፓልት እንድሰራልን
2ኛ የባንክ ቤት እንድሰራልን
3ኛ የወረዳ መዋቅር ጥያቄ
4ኛ የወጣቶች እስፖርት ማዘወተርያ ቦታ፣የስብዕና መገንብያ፣ የመዝናኛ ማዕከል እና የሥራ ዕድል ፈጠራ እንድመቻች
5ኛ የመብራት መቆራረጥ ችግር እንድፈታ እና ዝርጋታ ያልደረሰባቸው አካባቢዎች ዝርጋታ እንድደረግ
6ኛ የጤና ጣብያ አግልግሎት እንድዘመን እና ወደ ሆስፒታል እንድያድግ እንድደረግ
7ኛ የተጀመረው የከተማ ኮርደር ልማት ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለመንገድ ሥራ ማሽን እንድሰጥ
8ኛ የንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ከሕዝብ እድገት ጋር ምዛናዊ እንድሆን እና የውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ ጥገና እንዲደረግ
9ኛ የቴክንና ሙያ ስልጠና ተቋማት እንድገነባልን እና
10 ከአጎራባች ቀበያት ያለን ግንኙነት እንድታደስ እና እንድጠነክር እንድደረግልን የምል ጥያቄዎች እና ሌሎች አስተያየቶች እና የድጋፍ ሀሳቦች ከስብሰባ ተሳታፍዎች ተነስቶ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል።
እያንዳንዳቸው ከህዝብ የተነሱ ጥያቄዎች ተገብ እና በጨዋነት የተጠየቁ እንደሆነ ሁሉም ምላሽ ሰጭዎች ተናግረው ሁሉም በህዴት ምላሽ የሚያገኝ እና የሚፈታ መሆኑን በመናገር ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመሆን እና ለሰላም ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር እንድሰራ ተጠይቀዋል። በተጨማር በማዘጋጃ ቤት፣ በወረዳ፣ በዞን፣ በክልል እና በፌዴራል መንግሥት መፈታት ያለባቸው ጥያቄዎች በቅደም ተከተል ምላሽ የምሰጥ መሆኑን ተናግረዋል
የብልፅግና መንግስት በህዝብ የተመሰረት ለህዝብ ጥቅም የምሰራ ፓርቲ መሆኑን ሁሉም አውቀው ድጋፋቸውን አጠናክረው በመቀጡል የልማት ተጠቃምዎች እንድሆኑ እና በቀጣይ ከአጎራባች ቀበለያት ጋር የምክክር፣ የውይይት እና ግንኙነትን የማደስ እና የማጠናከር ስብሰባ እንደምደረግ ከጌዴኦ ዞን አስተዳደር ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር በኩል የውይይት መድረክ እንደምመቻች ተናግሮ የወርቃ ህዝብ በእርግጥም ጨዋ ህዝብ ነው ብሎ በማመስገን በከተማ ልማት ፣ በትምህርት፣ በግብርና ሥራ እና በአንድነት እንድጠነክሩ በማሳሰብ በቀጣይ ጊዜ ፈጣር በሰላም ያገናኘን ብሎ መልካም ምኞቱን በመግለጽ እና የውይይት ስብሰባ በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል።
ምርጫችን ብልጽግና ነው!
ምልክቱም የስንዴ ነዶ ነው!
ሚያዝያ 22/8/2018ዓ.ም
ወርቃ