የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office

  • Home
  • Ethiopia
  • Dilla
  • የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office

የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office ይህ ትክክለኛ የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ገጽ በመሆኑ ይከታተላሉ ።

Permanently closed.
የዲላ ከተማ የመሬት አስተዳደር መምሪያ ለ205 የልማት ተነሺዎች ተለዋጭ መሬት አስረከበዲላ፡ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ምትክ ቦታው ከጪጩ ሰው ሰራሽ ሀይቅ፣ ከክልል ግብርና ቢሮ፣ በ20 እና ...
04/09/2026

የዲላ ከተማ የመሬት አስተዳደር መምሪያ ለ205 የልማት ተነሺዎች ተለዋጭ መሬት አስረከበ

ዲላ፡ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ምትክ ቦታው ከጪጩ ሰው ሰራሽ ሀይቅ፣ ከክልል ግብርና ቢሮ፣ በ20 እና በ30 ሜትር መንገድ ግንባታ እንዲሁም አባገዳ ሶንጎ ቦታ ተነሺ ለሆኑ ግለሰቦች የተሰጠ ነው።

ለልማት ተነሺዎቹ የመሬት ርክክቡ የተከናወነው ፍትሐዊ ሂደትን በተከተለ የዕጣ ስነ-ስርዓት ነው።

በወቅቱ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመሬት አስተዳደር ቢሮ ም/ኃላፊ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለሁ ውድ የሆነውን የመሬት ሀብት በአግባቡ ማስተዳደር እንደሚገባ ገልፀዋል።

በዚህ ሂደት ለጋራ ጥቅም ሲባል ህዝቦች ከይዞታቸው ሊነሱ እንደሚችሉ ገልፀው፣ ተነሺዎች ግን ጥቅማቸው ተጠብቆ ሊነሱ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ይህንኑ ዲላ ከተማ አስተዳደር መተግበሩን የተናገሩት ም/ኃላፊው፣ እርምጃው ከክልሉ መሬት አስተዳደር ቢሮ እውቅና ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።

አክለውም ቦታውን በፍጥነት በማልማት ለኑሮ ምቹ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ(ዶ/ር) በበኩላቸው በከተማው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ከነዋሪዎች ጋር የጋራ መግባባት እና ግልፀኝነት በመፍጠር የሚከናወኑ መሆኑን አንስተዋል።

ዛሬ የተከናወነው የምትክ ቦታ ርክክብም የነዋሪውን ክብር በጠበቀና ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ ሁኔታ የተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።

ይህም የረጅም ጊዜ የልማት ተነሺዎች የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ የሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።

ምትክ ቦታው 10 ሄክታር መሆኑን ጠቅሰው፣ ለ205 ልማት ተነሺዎች የተሰጠ ሲሆን የልማት ተነሺዎች ረጅም ጊዜ ታግሰው በመቆየታቸው ከንቲባው ምስጋና አቅርበዋል።

የዲላ ከተማ የመሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ምህረቱ አበበ እንደገለፁት ሀገር እየበለፀገ ሲሄድ ከተሞች እንደሚሰፉ ተናግረዋል።

በዚህ ሂደትም በዲላ ከተማ በሚከናወኑ የልማት ተግባራት ምክንያት ለተነሱ ነዋሪዎች መምሪያው ዛሬ የምትክ ቦታ መስጠቱን ገልጸዋል።

ምትክ የተሰጠበት ቦታ በግብርና ልማት ላይ የነበረ መሆኑን ጠቅሰው የመንገድ ከፈታ፣ መዝናኛ ስፍራዎችና የግብይት ቦታዎች ተሸንሸነውለት ለልማት ተነሺዎች ርክክብ ተከናውኗል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር አቢይ ኮሚቴ የጳጉሜን ቀናት በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ለማክበር መከረዲላ ነሐሴ 28/2018ዓምየዲላ ከተማ አስተዳደር አቢይ ኮሚቴ አምስቱን የጳጉሜን ቀናት ለማክበር በ...
03/09/2026

የዲላ ከተማ አስተዳደር አቢይ ኮሚቴ የጳጉሜን ቀናት በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ለማክበር መከረ

ዲላ ነሐሴ 28/2018ዓም

የዲላ ከተማ አስተዳደር አቢይ ኮሚቴ አምስቱን የጳጉሜን ቀናት ለማክበር በተዘጋጀው የማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ በመወያየት፣ በሁሉም ቀናት የሚከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ አስቀመጠ።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ህዝባዊና ሀገራዊ መርሃ-ግብሮች በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።

የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ መንግስቱ ተክሌ እንደገለፁት፣ ሀገራችን ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣ የተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በፅናት በመሻገር በአሁኑ ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ እንደምትገኝ ተናግሯል።

ኃላፊ አክለውም በእነዚህ ቀናት የሚከናወኑት መርሃ-ግብሮች የተመዘገቡ ስኬቶችንና መልካም ተሞክሮዎችን በመቀመር እንዲሁም ሀገራዊ እሴቶችን በማጉላት፣ በመጪው አዲስ ዓመት ለበለጠ ድልና ስኬት መነሳሳትን የሚፈጥሩ እንደሚሆኑ ተጠቅሷል።

የ2018 ዓ.ም የጳጉሜ ቀናት መሪ ሃሳቦች ጳጉሜ 1፡ የእመርታ ቀን፣ ጳጉሜ 2፡ የማንሰራራት ቀን፣ ጳጉሜ 3፡የጽናት ቀን፣ ጳጉሜ 4፡ የኅብር ቀን እና ጳጉሜ 5፡ የነገ ቀን በምል መሪ ሃሳቦች እንደሚከበር ተገልጿል።

በአምስቱም የጳጉሜን ቀናት የታቀዱት ተግባራት በስኬት እንዲጠናቀቁ የከተማ የአመራር አካላት እንዲሁም መላው የከተማው ሕዝብ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

በዲላ ከተማ አስተዳደር በሴሳ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ ወጣቶች በስብዕና ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠዲላ፡ነሐሴ፣28/2018 ዓ.ም የዲላ ከተማ አስተዳደር "ለስብዕናው የታነጸ ወጣት ለሀገር ብልጽግ...
03/09/2026

በዲላ ከተማ አስተዳደር በሴሳ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ ወጣቶች በስብዕና ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ዲላ፡ነሐሴ፣28/2018 ዓ.ም የዲላ ከተማ አስተዳደር "ለስብዕናው የታነጸ ወጣት ለሀገር ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል በሴሳ ክፍለ ከተማ ማህበራዊ ክላስተር እና ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ለወጣቶች የስብዕና ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ኦልዬ አንደገለጹት ወጣቶች ለሀገራቸው አሻጋሪ ራዕይ ይዘው የተሻለ ብልጽግና እንዲያስመዘግቡ የአቅም ግንባታ ስልጠና ማዘጋጀቱ መንግስት ለወጣቶች ልዩ ትኩረት መስጠቱን የሚያሳይ ነዉ ብለዋል።

በተለይም ከስልጠናው በቀሰሙት ዕውቀት ታግዞ የለውጡንና የብልጽግናውን ጉዞ ዘላቂ ለማድረግ የዜግነት ድርሻውን እንዲወጣ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የሴሳ ክፍለ ከተማ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብርሃም ጠኮ በበኩላቸው በስብዕና የታነጸ ወጣት ለሀገር ግንባታ ያለው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን ፓርቲው በመረዳት ትኩረት ሰጥተው እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለው ወጣቶች የዛሬ ሀገር ገንቢና የነገ ሀገር ተረካቢዎች በመሆናቸው አዕምሮአቸውን በየጊዜው በእውቀት ማበልጸግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው ወጣቶች ስልጠናውን በዲስፕሊን እንዲከተሉ አሳስበዋል።

ስብዕና የስው ልጅ የታለመለትን ዓላማ ለማሳካት ትልቁ መሳሪያ ስለሆነ ለወጣቶች የሚሰጠውን ስልጠና ሙሉ ስብዕና ያለውና በምክንያት የሚያምን ወጣት ለመገንባት እንደሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ መላኩ አክለው ወጣቱ ያለው እምቅ አቅም ለሀገር ግንባታና ለሀገራዊ አንድነት እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

ስልጠናው በዋናነት ​በአዎንታዊ የህይወት ዘይቤ፣ ​በምክንያታዊነትና በውሳኔ አሰጣጥ፣​በግልና በሀገራዊ ራዕይ፣ ​እንዲሁም በመልካም ስነ-ምግባር ዙሪያ ላይ ያተኮረ እንደነበር ተመልላክቷል።

የሴቶችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በማጠናከር በከተማው ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ መፋጠን ይሠራል ፦ ከንቲባ መስፍን ደምሴ ( ዶ/ር )ዲላ፡ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የዲላ ከተማ ሴቶችና ማ...
03/09/2026

የሴቶችን ፍትሐዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ በማጠናከር በከተማው ለተጀመረው የብልጽግና ጉዞ መፋጠን ይሠራል ፦ ከንቲባ መስፍን ደምሴ ( ዶ/ር )

ዲላ፡ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የዲላ ከተማ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ከልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በሥርዓተ ፆታ ሜይንስትሪሚንግና ሥርዓተ ፆታ ኦዲቲንግ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል።

በወቅቱ የተገኙት የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ ( ዶ/ር ) ብልጽግና ፓርቲ የዜጎች ፍትሐዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ይህንኑ አቅጣጫ በመተግበር በሚያከናውናቸው ሁለንተናዊ ልማች ተግባራት ላይ የሴቶችን ተሳትፎ ማጠናከር በመቻሉ ውጤታማ መሆኑንም ገልፀዋል።

ይህም የሴቶችን ተሳትፎ እንዲጠናከር ያስቻለ መሆኑን ጠቅሰው ለዚህም መጠናከር ሁሉም አካላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ገልፀዋል።

በተለይም ሴቶች በሚሰማሩበት የሙያ መስክ ጠንክረው በመወጣት እና አቅማቸውን በማሳየት ለተጠቃሚነታቸው ሊተጉ እንደሚገባ ከንቲባው አሳስበዋል።

የዲላ ከተማ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ዜና ክፍሌ ስልጠናው የሴቶችን ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

የሴቶችን እኩል ተጠቃሚነት እና ውሳኔ ሰጪነት አቅም ማሳደግ ለተጀመሩ ሁለንተናዊ የልማት ተግባራት ውጤታማነት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል።

መምሪያው በሴቶች ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ላይ በትኩረት መስራቱን እንደሚቀጥልም ነው ወይዘሮ ዜና የተናገሩት።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ስርዓተ ጾታ ዳይሬክተር አቶ አወቀ ታዬ ስልጠናውን በሰጡበት ወቅት በክልሉ የሴት አመራር ቁጥር 23 በመቶ ፣ የምክር ቤት አባላት ቁጥር 48 በመቶ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ይህ ቁጥር በቂ አለመሆኑን ጠቅሰው የሴቶችን ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት በበለጠ ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

ስልጠናው ትልቅ አቅም እንደፈጠረላቸው የገለፁት ደግሞ የከተማው አካባቢ ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሰናይት ጅሶና የከተማው ሳይንስና ኢኖቬሽን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ፀሐይ ቦጋለ ናቸው።

በዚህም ያገኙትን ክህሎት ወደ ተግባር በመለወጥ ለሴቶች ተጠቃሚነት እንደሚሠሩም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብር እያከናወነ ነው‎‎( #ዲላ፣ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም) ዲስትሪክቱ የ...
03/09/2026

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲላ ዲስትሪክት ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለአቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብር እያከናወነ ነው

‎( #ዲላ፣ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም) ዲስትሪክቱ የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመትን በማስመልከት “አዲሱን ዓመት በአገልጋይነትና በበጎነት” በሚል መሪ ቃል ለአቅመ ደካሞችና ጧሪ ደጋፊ ለሌላቸው ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብር አካሂዷል።

‎የዲስትሪክቱ ማዕድ ማጋራት መርሐ ግብር በዓሉን ከመቀበል ባሻገር በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችንና ድጋፍ የሚፈልጉ ወገኖችን በመደገፍ የማህበራዊ ኃላፊነትና የአብሮነት መንፈስን ለማጠናከር ያለመ ነው።

‎በመርሐ ግብሩ ዲስትሪክቱ ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለእያንዳንዱ 25 ኪሎ ግራም ዱቄት፣ 5 ሊትር ዘይት እና 2 ሺህ ብር የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ለበዓሉ መዋያ አጋርተዋል።

‎የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብሩ የአዲስ ዓመትን በዓል በመልካም ተግባር ለመቀበልና በተለይም ድጋፍ የሚፈልጉ ወገኖች የበዓሉን ደስታ እንዲጋሩ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተገልጿል።

‎በመርሐ ግብሩ ላይ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር)፣ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ፣ የዲስትሪክቱ ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ከበደ ጨምሮ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝቷል።

‎@የጌዴኦ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎ!

03/09/2026

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ !

በክልሉ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አቢይ ኮሚቴ የተቀመጡ ቀጣይ አቅጣጫዎች፦

✍️ ተሳትፎን ማጠናከር፦ የኃይማኖት ተቋማትን፣ ባለሃብቶችን እና ወጣቶችን ጨምሮ የሁሉንም ማህበራዊ መሰረት ተሳትፎ በላቀ ደረጃ መጠቀም፤

✍️ ድጋፉ ለተገቢው አካል መድረሱን ማረጋገጥ፦ የሚደረጉ የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፎች በትክክል ድጋፍ ለሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎች መድረሳቸውን በቅርበት ማረጋገጥ፤

✍️ የስምሪት መስኮችና መዋቅርን ማመጣጠን፦ የበጎ ፈቃደኞች የስምሪት መስኮችና መዋቅራዊ አሰራሮች ተመጣጣኝ እንዲሆኑ ማድረግ፤

✍️ ትክክለኛ መረጃ መያዝ፦ በገንዘብና በጉልበት ምን ያህል ወጪ እንደዳነ የሚያሳይ ጥራት ያለውና ትክክለኛ መረጃ ማደራጀት፤

✍️ የአገልግሎቱን ፈጠራና ፍጥነት መጨመር፦ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ፈጠራ እና ፍጥነት ማሳደግ፣ በተለይም ለአቅመ-ደካሞች የሚገነቡ ቤቶች የተቀመጠላቸዉን ስታንዳርድ የጠበቁ እንዲሆኑ ማድረግ፤

02/09/2026

እዉነታዉን የተረዳ፤ ለእዉነት የሚጎዳ አመራር ያስፈልጋል!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)

የህዝብ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ፓርቲ ሰው ተኮር ተግባር ላይ ትኩረት ሰጥተው እየተሰራ መሆኑን ተገለፀ ዲላ፡ነሐሴ፣27/2018 ዓ.ም የዲላ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ...
02/09/2026

የህዝብ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ፓርቲ ሰው ተኮር ተግባር ላይ ትኩረት ሰጥተው እየተሰራ መሆኑን ተገለፀ

ዲላ፡ነሐሴ፣27/2018 ዓ.ም የዲላ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ በሚችሌ ክፍሌ ከተማ ስሶታ ቀበሌ ራሶ መንደር የአረጋውያን መኖሪያ ቤት ግንባታ አስጀምረዋል።

በመርሐ-ግብሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢሳያስ ተፈራ የህዝብ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ሰው ተኮር ተግባር ላይ ፓርቲ ትኩረት ሰጥተው እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለው ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነዉ ያሉት አቶ ኢሳያስ ባለፉት አመታት በተከናወኑ ሥራዎች አመርቂ ውጤት መመዝገባቸውን አንስተዋል።

በቀጣይም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የመረዳዳት፣ የአብሮነትና የዜጎችን ማኅበራዊ ችግር በጋራ የመፍታት ባህል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ኃላፊ ተወካይ አቶ ዳዊት አራሪሶ መምሪያ ባለፉት አመታት ለአዕምሮ እርካታ የሚሰጥ የበጎነት ተግባራቶች እያከናወነ መቆየቱን ገልፀው በዘንድሮው ክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ ተግባር እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ዳዊት አክለው መምሪያ የብልፅግና ፓርቲ እሳቤዎች የሚጎላው አብሮ መሥራት፣ ወገንን መደገፍ፣ ማኅበራዊ ኃላፊነትን መወጣትና የጋራ ተጠቃሚነትን ማሳደግና ሰው ተኮር ሥራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።

የሚችሌ ክፍሌ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ በክፍሌ ከተማው በዘንድሮው ክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 78 አዳዲስ ቤት ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በከተማው አስተዳደር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችና የአረጋውያን የቤት ግንባታ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥለዋል።

የኢትዮጵያ ማንሰራራት !የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች የሚከበር ይሆናል።ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስ...
02/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት !

የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች የሚከበር ይሆናል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በፅናትና በፈጠራ በመሻገር፣ በአሁን ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ የምትገኝ ሀገር ሆናለች።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ዘይቤ ውስጥ ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን የተገኙ ወረቶች የሚደመሩበት እንዲሁም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር የነበሩ ጥንካሬዎችን የሚያስቀጥል፣ የታዩ ክፍተቶችን የሚያርም፣ አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ የሚጠቀም፣ የተመዘገቡ ትላልቅ ስኬቶችን የሚያስታውስ፣ አዳዲስ ብስራቶችን የሚያበስር በመሆሃ በሳቢ ኹነቶችና የንቅናቄ መንገዶች የሚመራ ይሆናል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ያተኮረ እንደሚሆንም በቀረበው የማስፈፀሚያ ዕቅድ ተመላክቷል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀና፤ ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣ ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣ ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣ ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት የሚከበሩ ይሆናል።

የዲላ ከተማ አስተዳደር ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሆነውን የ2019 በጀት ዓመት በጀት አጸደቀዲላ፡ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ምየዲላ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት የልማትና...
01/09/2026

የዲላ ከተማ አስተዳደር ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሆነውን የ2019 በጀት ዓመት በጀት አጸደቀ

ዲላ፡ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ምየዲላ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት የልማትና የአገልግሎት ስራዎች ማስፈጸሚያ የሚውል 2 ቢሊዮን 255 ሚሊዮን 241 ሺህ 187 ብር በጀት አጸደቀ።

የበጀት ድልድሉን ለምክር ቤቱ አባላት በዝርዝር ያቀረቡት የዲላ ከተማ ፋይናንስና ፕላን መምሪያ ኃላፊ አቶ ከባዱ ወራሳ ናቸው።

ኃላፊው በማብራሪያቸው የዘንድሮው በጀት የከተማዋን የልማት አቅጣጫዎች እና የነዋሪዎችን መሰረታዊ ፍላጎቶች ማዕከል አድርጎ በጥንቃቄ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ የጸደቀው በጀት በከተማዋ በታቀደው ልክ የሚከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶችን ከዳር ለማድረስ እና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም አቶ ከባዱ አስገንዝበዋል።

የበጀቱን መጽደቅ ተከትሎ የጸደቀው በጀት ለታለመለት የልማት ዓላማ ብቻ መዋሉን ማረጋገጥ እንደሚገባ ያሳሰቡት የምክር ቤቱ አባላት የበጀቱ አፈጻጸም በተገቢው መንገድ ጥብቅ የክትትል ሥርዓትን የተከተለ እንዲሆን አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን የከተማው መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ዘግቧል።

Address

Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla City Prosperity party Branch office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share