Dire Dawa Police

Dire Dawa Police የድሬዳዋ ፖሊስ ራዕይ::
👉በ2022 በኢትዮጵያ በላቀ ሙያዊ ብቃት ቀዳሚ የፖሊስ ተቋም ሆኖ ማየት::
(1)

This is the official page of the Dire Dawa Police Department
ይህ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ኦፊሻል የፌስብ ቡክ ገፅ ነው።

30/05/2026
29/05/2026

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ያለ ምንም የፀጥታ እንከን እንዲጠናቀቅ ለፖሊስ አመራርና አባላት ስልጠና ተሰጠ።

29/05/2026

"ትከሻችን ማዕረግን ብቻ ሳይሆን አደራንም ይሸከማል!"

29/05/2026

በዛሬው ዕለት የተከናወነው የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት በፎቶ
29/05/2026

በዛሬው ዕለት የተከናወነው የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት በፎቶ

''ማዕረግ የህዝብን ደህንነት በታማኝነት የመጠበቅ ትልቅ አደራ ነው''-ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የቆይታ ጊዜያቸውን ላጠናቀቁ፣ በዲሲ...
29/05/2026

''ማዕረግ የህዝብን ደህንነት በታማኝነት የመጠበቅ ትልቅ አደራ ነው''-ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የቆይታ ጊዜያቸውን ላጠናቀቁ፣ በዲሲፕሊናቸውና በስራ አፈጻጸማቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አመራርና አባላት የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት በድምቀት አካሂዷል።

በዚህ ደማቅ መርሐ-ግብር ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር፣ የፍትህ፣ ፀጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱሰላም አህመድ፣ ወ/ሮ ሹክሪ አብዱረህማን የድሬዳዋ አስተዳደር ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ባለስልጣን ኃላፊ፣ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ፣ የሁርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አመራሮች፣ የጠቅላይ መምሪያው ምክትል ኮሚሽነሮች እና በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ላይ የሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

በመርህ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ፣ ዛሬ በትከሻችሁ ላይ ያረፈው ማዕረግ የደከማችሁበት የሙያ ስኬት መገለጫ ብቻ ሳይሆን፣ ለድሬዳዋ ህዝብ ሰላምና ደህንነት ይበልጥ እንድትተጉ የተሰጣችሁ ታላቅ የህዝብና የሀገር አደራ ነው ብለዋል።

ማዕረግ የህዝብን ደህንነት በታማኝነት የመጠበቅ ትልቅ አደራ ነው ያሉት ክቡር ከንቲባው የከተማችንን ልማትና ኢንቨስትመንት በፅኑ መሰረት ላይ ለማቆም አስተማማኝ ፀጥታ መኖሩ ወሳኝ በመሆኑ፣ ከአዲሱ ማዕረጋችሁ ጋር የሚመጣውን ከባድ ኃላፊነት በቅንነትና በቁርጠኝነት እንድትወጡ አሳስባለሁ ብለዋል።

ማዕረግ በቆይታ ብቻ ሳይሆን በላቀ ዲሲፕሊን የሚገኝ ክብር ነው ያሉት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ በበኩላቸው የማዕረግ ዕድገት ዝም ብሎ በጊዜ ሂደት የሚሰጥ ስጦታ አለመሆኑን አስገንዝበዋል።

ኮሚሽነሩ አክለውም ዛሬ ለዚህ ክብር የበቁ የአመራርና የአባላት ከማዕረጉ ጀርባ ያለውን የህዝብ አገልጋይነት ስሜትና ከባድ ኃላፊነት በመረዳት፣ በየተሰማሩበት የስራ መስክ የህግ የበላይነትን ለማስከበር በግንባር ቀደምትነት ሊሰለፉ እንደሚገባ ጥብቅ መመሪያ አስተላልፈዋል።

በዚህ መርሃ-ግብር ላይ የማዕረግ ማልበስ ሥነ-ሥርዓት የሰራዊቱን አቅም በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና ለነበራቸው አካላት እውቅና የተሰጠ ሲሆን በስልጠና ሂደት ላይ ለነበሩ አመራሮችና አባላት ስልጠናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ላበረከተው ለሁርሶ ኮንተንጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የምስጋና እና የላቀ የእውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል።

በአጠቃላይ በዚህ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ 796 የሚሆኑ የፖሊስ አባላትና አመራሮች የማዕረግ ሽግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በከተማዋ አስተማማኝ ሰላምን ለማስፈን ቃላቸውን በማደስ ስነ-ስርዓቱ በድል ተጠናቋል።

===================
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ትክክለኛ፣ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
#በፌስቡክ:-👇
📌በአማረኛ :-https://www.facebook.com/profile.php?id=100071007202116

📌በኦሮምኛ :-https://www.facebook.com/profile.php?id=100068806916386

📌ስፖርት :-https://www.facebook.com/profile.php?id=100063887688997

📌ዩትዩብ፦https://youtube.com/?feature=shared

📌በቴሌግራም ቻናላችን
👉https://t.me/direpoli

📌ቲክቶክ፦https://www.tiktok.com/?_t=8fY2fIbUgSs&_r=1

፡፡


ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ያለ ምንም የፀጥታ እንከን እንዲጠናቀቅ ለፖሊስ አመራርና አባላት ስልጠና ተሰጠ።የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የፊታችን ግንቦት 24 የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም...
28/05/2026

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ያለ ምንም የፀጥታ እንከን እንዲጠናቀቅ ለፖሊስ አመራርና አባላት ስልጠና ተሰጠ።

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የፊታችን ግንቦት 24 የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ እና ያለ ምንም የፀጥታ እንከን እንዲከናወን ለማስቻል፤ የፀጥታ ኃይሉ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወጡትን የምርጫ ማስፈፀሚያ ህጎችና ደንቦች በሚገባ ተረድቶ ስራውን በዕውቀት እና በገለልተኝነት እንዲሰራ የሚያስችል ስልጠና ለአመራር እና ለአባላት ሰጥቷል።

በዚህም ስልጠና ላይ የድሬዳዋ ፖሊስ አባላት በምርጫ ወቅት የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ፣ የምርጫ ጣቢያዎችን ሰላምና መረጋጋት የማረጋገጥ እንዲሁም ማናቸውንም ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች አስቀድሞ የመከላከል ዝግጁነቱን አጠናክረዋል።

ስልጠናው ፖሊስ በምርጫ ወቅትና ከምርጫ በኋላ ሊከተላቸው ስለሚገቡ የምርጫ ስነ ምግባርና የአፈፃፀም አቅጣጫዎች ትኩረት ያደረገና የምላሽ አሠጣጥን ጭምር የሚያትት ሲሆን በተለይም የምርጫ ቁሳቁሶች ሳይደናቀፉ ለታለመላቸው ጣቢያዎች እንዲደርሱ ጥበቃ ከማድረግ ጀምሮ፣ ህዝቡ በነፃነት ድምፁን መስጠት እንዲችል የህግ የበላይነትን የማስከበርና ድንገተኛ የፀጥታ እክሎች ቢያጋጥሙ እንኳ በአጭር ጊዜ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ምላሽ የመስጠት ስልቶችን ያካተተ ነው ።

የስልጠናው ማጠቃለያ ላይ በመገኘት ለአመራሮች እና ለአባላት ጠንካራ የስራ መመሪያና መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር አለሙ መግራ እንደተናገሩት ምርጫ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማሳያ በመሆኑም እያንዳንዱ የፖሊስ አመራርና አባል ከተሰጠው ስልጠና የተሰነቀውን ዕውቀት በተግባር በመተርጎም፣ ሙሉ በሙሉ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በሆነ መልኩ፣ ህግና ስርዓትን ብቻ መነሻ አድርጎ ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል ብለዋል።

​የድሬዳዋን ህዝብ አስተማማኝ ሰላም ማስጠበቅና ማንኛውንም የጸጥታ ስጋት በንቃት መከላከል ቀዳሚ ተግባራችን ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራትም የምርጫውን ሂደት በስኬት እናጠናቅቃለን ብለዋል።

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከምንጊዜውም በላይ ምርጫው ሠላማዊ እንዲሆን ሁሉን አቀፍ ዝግጅት እያደረገ የሚገኝ ሲሆን በአስተዳደሩ በሚገኙ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎችና አካባቢዎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲኖር የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ ግብዓቶች የተሟሉ ሲሆን፣ ህብረተሰቡም ከፖሊስ ጎን በመቆም የተለመደውን የሰላም አጋርነቱን እንዲያሳይ ጥሪ ቀርቧል።
===================
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ትክክለኛ፣ ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
#በፌስቡክ:-👇
📌በአማረኛ :-https://www.facebook.com/profile.php?id=100071007202116

📌በኦሮምኛ :-https://www.facebook.com/profile.php?id=100068806916386

📌ስፖርት :-https://www.facebook.com/profile.php?id=100063887688997

📌ዩትዩብ፦https://youtube.com/?feature=shared

📌በቴሌግራም ቻናላችን
👉https://t.me/direpoli

📌ቲክቶክ፦https://www.tiktok.com/?_t=8fY2fIbUgSs&_r=1

፡፡


ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬት የምስራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች የፀጥታ አካላት በጋራ መከሩ!የፊታችን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከናወነውን 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ነጻ እና ዲ...
28/05/2026

ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬት የምስራቅ ኢትዮጵያ አጎራባች የፀጥታ አካላት በጋራ መከሩ!

የፊታችን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከናወነውን 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ነጻ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለማስፈጸም የተዘጋጀውን የጋራ የፀጥታ እቅድ በማፅደቅና ቅንጅትን በማጠናከር ዙሪያ የምስራቅ አጎራባች የፀጥታ አካላት ኮማንድ ፖስት የጋራ ውይይት አካሄዱ።

በውይይቱ ላይ በዋናነት በምርጫው ዕለት ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በየደረጃው በሚገኙ የፀጥታ አካላት ሊከናወኑ በሚገባቸው አንኳር የፀጥታ ስራዎች ላይ ሰፊና ጥልቅ ውይይት ተደርጓል።

በዚህ ወሳኝ የጋራ መድረክ ላይ በምስራቅ ኢትዮጵያ የሚገኙ ሁሉም የፀጥታ አካላት ሙሉ በሙሉ የተገኙ ሲሆን፣ የፀጥታ መዋቅሮች ያላቸውን የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ አቅም በማስተባበር የአካባቢውን አስተማማኝ ሰላም ለማስጠበቅ ያላቸውን ቁርጠኝነት አሳይተዋል።

ባለድርሻ አካላቱ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማነት ፍፁም ሰላማዊነት ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ መሆናቸውንና ማንኛውንም የጸጥታ ስጋት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

ህዝቡ ያለምንም ስጋት ወጥቶ ድምጹን መስጠት እንዲችል ቀጣይነት ያላቸው የጋራ የፓትሮልና የክትትል ስራዎች እንደሚጠናከሩም ተመልክቷል።

በዚሁ የምስራቅ አጎራባች የፀጥታ አካላት የጋራ ውይይት መድረክ ላይ የድሬዳዋ የፀጥታ ምክር ቤት ሰብሳቢና የአስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር፣ የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ምስራቅ እዝ ከፍተኛ አመራሮች፣ የፌዴራል ፖሊስ ምስራቅ ምድብ አመራሮች፣ የኦሮሚያ ክልል የምዕራብ እና ምስራቅ ሀረርጌ የፀጥታ አመራሮች፣ እንዲሁም የሶማሊ ክልል የሲቲ ዞን የፀጥታ አመራሮች ተገኝተዋል።

ይህ የፀጥታ አካላት የጋራ ቅንጅትና ዝግጁነት ምርጫው በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።

#7ኛውሀገራዊምርጫ #ምስራቅኢትዮጵያ #ሰላምናፀጥታ #ድሬዳዋ #ኦሮሚያ #ሶማሊ #ፌዴራልፖሊስ #መከላከያሰራዊት

27/05/2026

የቴክኖሎጂ እና የፖሊስ አገልግሎት ውህደት በአለም አቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አይን!

በቲክቶክ አካውንቱ ከ19.6 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያለው እና በፈጣንና ተደራሽ የዓለም አቀፍ መረጃዎቹ የሚታወቀው ዝነኛው ዲላን ፔጅ (Dylan Page)፣ ዘመናዊውን ስማርት ሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ (Smart Police Station - SPS) በመጎብኘት ያዘጋጀውን አስገራሚ ቪዲዮ ለሚሊዮን ተከታዮቹ አጋርቷል።

​ዲላን በቪዲዮው ላይ የቴክኖሎጂን የመጨረሻ ጥግ እና የፖሊስ አገልግሎት ያለ ሰው ንክኪ ምን ያህል ቀልጣፋ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ተደራሽ ሊሆን እንደሚችል አሳይቷል።

ቪዲዮው በአጭር ጊዜ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ እይታዎችንና አስተያየቶችን እያገኘ ይገኛል።

https://vt.tiktok.com/ZSx4DxWVC/

በርካታ ሕዝብ የተሳተፉበት የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) ሰላት በድሬዳዋ በሰላም ተጠናቀቀ​ዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በድሬዳዋ ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው የእስልምና እምነት ተከታዮች በተገ...
27/05/2026

በርካታ ሕዝብ የተሳተፉበት የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) ሰላት በድሬዳዋ በሰላም ተጠናቀቀ

ዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በድሬዳዋ ከተማ በርካታ ቁጥር ያላቸው የእስልምና እምነት ተከታዮች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት እና በሰላም ተከብረዋል ።

​ለበዓሉ በሰላም መጠናቀቅ የድሬዳዋ ፖሊስ ከከተማው ነዋሪዎች እና ከበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ጋር በቅንጅት የሰራው የጸጥታና የደህንነት ሥራ ቀዳሚውን ሚና ተጫውቷል።

የጸጥታ አካላትና የኅብረተሰቡ የጋራ ትብብር በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር፣ በደመቀ ሁኔታና በሰላም እንዲጠናቀቅ አስችሏል።

​የድሬዳዋ ፖሊስ ለበዓሉ ሰላማዊ መሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ለጸጥታ መዋቅሩ ያለውን ከፍተኛ ምስጋና ያቀርባል።

​እንኳን አደረሳችሁ!
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ

የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ​በመጀመሪያ፣ ለዘመናት በዘለቀው የአብሮነት፣ የፍቅርና የአንድነት እሴቶቿ ጎልታ በምትታወቀው የብዝሃነ...
26/05/2026

የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ

​በመጀመሪያ፣ ለዘመናት በዘለቀው የአብሮነት፣ የፍቅርና የአንድነት እሴቶቿ ጎልታ በምትታወቀው የብዝሃነት ከተማችን ድሬዳዋና በመላው ሀገራችን ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ።

​የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል የእስልምና እምነት ተከታዮች የፈጣሪያቸውን ትዕዛዝ በተግባር በመፈጸም ፍጹም መታዘዝን የሚያሳዩበት፣ እንዲሁም ህዝብ ለህዝብ ያለው ትስስርና መተሳሰብ ይበልጥ የሚጠናከርበት ታላቅ በዓል ነው። ይህንን መልካም እሴት ጠብቆ ማስቀጠልና በዓሉ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲያልፍ ማድረግ ደግሞ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው።

​የተከበራችሁ የከተማችን ነዋሪዎች፤
መጪው የዒድ አል-አድሃ በዓልም ሆነ በድሬዳዋ የሚከናወኑ ማናቸውም ሁነቶች ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቁ የድሬዳዋ ፀጥታ ግብረ ኃይል የተቀናጀ የፀጥታ እቅድ በማውጣትና ሰፊ ዝግጅት በማድረግ፣ ማንኛውንም የፀጥታ ስጋት አስቀድሞ መከላከል በሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል። ለዚህም የሰው ኃይልና ቁሳቁስ በበቂ ሁኔታ ተደራጅቶ ወደ ሙሉ ስምሪት መግባቱን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ።

​የፀጥታ መዋቅራችን የህዝብን ደህንነትና ሰላም አስተማማኝ የማድረግ ኃላፊነቱን በላቀ ዝግጁነት፣ ቀንና ሌሊት በቁርጠኝነት ይወጣል። ሆኖም ግን ሰላም በጋራ ቅንጅትና ትብብር የሚጸና በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለበዓሉ ከሚያደርገው መዘጋጀት ጎን ለጎን ለአካባቢው ሰላም ጥበቃ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣና ማንኛውንም አጠራጣሪ ክስተት ሲያጋጥም በፍጥነት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት የተለመደውን አጋርነት እንዲያሳይ ጥሬን አቀርባለሁ።

​በድጋሚ በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅርና የብልጽግና እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ።

​ዒድ ሙባረክ!

"በጀግንነት እንጠብቃለን፣ በሰብአዊነት እናገለግላለን!"
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ

Address

Dire Dawa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa Police posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Dire Dawa Police:

Share