የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Durame
  • የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የዞናችን ሕዝቦች በላቀ መረጃ በልጽገው የጋራ ውሳኔ ሰጪነታቸውን ማረጋገጥ
(1)

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህል ሆኖ እንዲቀጥል የወጣቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የሀዲያ ዞን እና...
05/09/2026

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህል ሆኖ እንዲቀጥል የወጣቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የሀዲያ ዞን እና የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ አመራር አካላት 'በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!' በሚል መሪ ቃል በከምባታ ዞን ዱራሜ ከተማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካሂደዋል፣

በመርሃግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጠችሁ መልዕክት ያስተላለፊት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩም እንደገለጹት ክልሉ ከተመሰረተ አጭር ቆይታ ቢሆንም በሁሉም መስኮች የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆኑንና ጠቅሰው በበጎ ፈቃድ አገልግሎትም በርካታ ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፣

አቶ ተክሌ ስዩም አክለውም ወጣቶች ነገ የተሻለች ለሁም የምትመች ጠንካራ ሀገር ለመገንባት ወጣቶች በጎ ስራቸው ገዥ ትርክት በመገንባት የእርስ በእርስ ትስስርን፣ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ማጠናከር ተገቢነት እንዳለው ገልጸው በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታና እድሳት፣ ለተማሪዎች የቁሳቁስ ድጋፍ፣ የአረንጓዴ አሻራ ስራዎችን ጨምሮ በርካታ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፣

በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱ ዲንቁ እንደገለጹት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህል ሆኖ እንዲቀጥል ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፣

አቶ አብዱ ዲንቁ አክለውም የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በማህበራዊ ዘርፍ በህዝቦች አንድነትና አብሮነት ለማጠናከር አጋዥ መሆኑንና በሌሎችም በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካው ዘርፎች ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል፣

በመርሃግብሩ ወቅት በጎ ወሰን ተሻጋሪ ፈቃደኛ ወጣቶችን እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላቱ ማቴዎስ በበኩላቸው ወጣቶ ያላቸውን ዕውቀትና ጉልበት የበጎ ፈቃድ ስራ በመስራት ለሀገር ግንባታ ለዜጎች ተጠቃሚነት ምክንያታዊና አሳማኝ በሆነ መንገድ ማበርከት ይገባል ስሉ ገልጸዋል፣

በመርሃግብሩ ለአቅመ ደካማ እናት የቤት ግንባታ የሚሆን የቆርቆሮና የምስመር ድጋፍ፣ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ልጆች የትምህት መማሪያ ደብተርና እስክብርቶ፣ የእህልና የምግብ ዘይት ድጋፍ በማድረግ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሰርቷል።

ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

ዊማ ኢንተርናሽናል (WEEMA International) ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ግብዓቶችን ለጤና ተቋማት ድጋፍ አደረገ ዊማ ኢንተርናሽናል (WEEMA International) ...
05/09/2026

ዊማ ኢንተርናሽናል (WEEMA International) ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ግብዓቶችን ለጤና ተቋማት ድጋፍ አደረገ

ዊማ ኢንተርናሽናል (WEEMA International) ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያከናውናቸው ሁለንተናዊ የጤና ተግባራት አካል የሆነውን እና በገንዘብ ሲተመን ከ3 ሚሊዮን 46 ሺህ ብር በላይ ግምት ያለው የመድኃኒትና የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ።

ድርጅቱ ይህንን ሰፊ ድጋፍ ያደረገው በዳምቦያ ወረዳ እና በዳምቦያ ከተማ አስተዳደር ተግባራዊ እያደረገ በሚገኘው የ"ትራይፌክታ" (Trifecta) ፕሮጀክት አማካይነት ሲሆን፤ ግብዓቶቹም በሁለቱ መዋቅሮች ስር ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎችና ጤና ኬላዎች በይፋ ርክክብ ተደርጓል።

የህክምና ግብዓቶቹን ለጤና ተቋማቱ ያስረከቡት በድርጅቱ የፕሮጀክቱ ማህበረሰብ አስተባባሪ (Community Office Manager) አቶ አለሙ ሙላቱ እንደገለጹት፤ ድጋፉ በዋናነት የእናቶችን ጤና ምርመራና የህክምና አገልግሎት ጥራት ለማሻሻል ትልቅ አቅም ይፈጥራል።

ከዚህም ባሻገር ከጊዜ ወደ ጊዜ ስርጭቱ እየጨመረ የመጣውን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመግታት፣ በተለይም በጤና ኬላዎች የስኳር በሽታ የምርመራ አገልግሎትን በይፋ ለማስጀመር የሚያስችሉ ወሳኝ መመርመሪያ ግብዓቶች በድጋፉ መካተታቸውን ኃላፊው አብራርተዋል።

ይህንን ማህበረሰብ ተኮር የሆነ ከፍተኛ ድጋፍ የተረከቡት የየመዋቅሮቹ የጤና ጽህፈት ቤት ተወካዮች በበኩላቸው፤ ዊማ ኢንተርናሽናል የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅና የህክምና አገልግሎትን ለማዘመን እያደረገ ላለው ተከታታይና አጋርነት የተሞላበት ድጋፍ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የጤና ተቋማቱም የተበረከቱላቸውን ቁሳቁሶችና መድኃኒቶች ለታለመላቸው የህብረተሰብ ክፍል በማዋል ህዝቡን በተሻለ ጥራት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የመሬት ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደርና በአጠቃቀም ላይ ተገቢውን አቅጣጫ በመከተል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።የከምባታ ዞን ግብርና መምሪያ የመሬት አስተዳደ...
05/09/2026

የመሬት ሀብትን በአግባቡ በማስተዳደርና በአጠቃቀም ላይ ተገቢውን አቅጣጫ በመከተል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።

የከምባታ ዞን ግብርና መምሪያ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማ ዙሪያ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በዱራሜ ከተማ አካሂዷል።

የከምባታ ዞን ግብርና መምሪያ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደነቀ ላምቤቦ መሬት የማኅበረሰብና የሀገር የጋራ ሀብት በመሆኑ፣ በሕግና በአሠራር መርሆች መሠረት በአግባቡ ማስተዳደርና ለተሻለ ልማት ማዋል የሚጠይቀው ኃላፊነት ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።

ባለፉት ዓመታት በዞኑ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀምን ለማዘመን በተሰራው ስራ አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ያብራሩት ኃላፊው በዚህም የመሬት አጠቃቀም ሥርዓትን ማሻሻል፣ የመሬት ሀብትን ከብክነትና ተገቢ ካልሆነ አጠቃቀም መጠበቅ እና መሬትን ለምርታማነትና ለዘላቂ ልማት ማዋል ጠንካራ ቅንጅት መፍጠርን ይጠይቃል ብለዋል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ደነቀ ላምቤቦ አክላውም የዓመቱን አፈጻጸም መገምገም ያለፈውን ሥራ በቁጥር ለማስቀመጥ ብቻ ሳይሆን፣ ጠንካራ አፈፃፀሞችን ይበልጥ ለማስቀጠልና የቀጣዩን ዓመት ሥራ በተሻለ አቅጣጫ ለመምራት ከወዲሁ መዘጋጀት ይገባልም ነው ያሉት።

በየአካባቢው ያሉትን የእርሻ፣ የደን እና ሌሎች ክፍት መሬቶች በአግባቡ በመለየትና ካርታ በማዘጋጀት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለኢንቨስትመንትና ለህብረተሰቡ ጥቅም ማዋል እንደሚያስፈልግም በመግለጽ በሁሉም እርከን የሚገኙ አመራሮችና ባለሙያዎች መሬትን ከዲጂታል ፕሮፋይል ጋር ከማስተሳሰር አኳያ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

አቶ ደነቀ አክለውም፣ የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ሲዘጋጅ ከወረዳ መዋቅሮችና ከዘርፉ አመራርና ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመምከር፣ በተጨባጭ የሥራ ሁኔታ ላይ በመመሥረትና የቀደሙ አፈጻጸሞችን በመተንተን ሊፈጸሙ የሚችሉ ግልጽ ግቦችን መያዝ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የመሬት አስተዳደር ሥራ በጽ/ቤት ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን ከወረዳና ቀበሌ መዋቅሮች፣ ከባለሙያዎችና ከማኅበረሰቡ ተሳትፎ ጋር በተቀናጀ መልኩ መመራት እንዳለበትም አቶ ደነቀ አስገንዝበዋል።

በሁሉም ወረዳዎች የተዘረጋ ዲጂታል ትራንዛክሽን (Digital Transaction) ወጥ የሆነ አፈፃፀም እንዲኖር ማድረግና እየተስተዋሉ ያሉ ውስንነቶችን በአስቸኳይ በመገምገም መስተካከል እንዳለበትም ጭምር ነው አቶ ደነቀ ያሳሰቡት።

የመሬት ወረራን በአግባቡ በመከላከል አርሶ አደሩ ከመሬቱ ጋር በተያያዘ ተጠያቂ እንዳይሆን አሠራሩን ያልጠበቀ የይዞታ ማረጋገጫ ተያይዞ የሚነሱ ቅሬታዎችን በቅርበት በመከታተልና በመፍታት የመሬት ዋስትናውን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም የተቀመጡ ግቦችን በጊዜና በጥራት ማሳካት እንዲቻል የክትትልና የድጋፍ ሥርዓትን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ከወረዳ መዋቅሮች ጋር በመምከር የ2019 በጀት ዓመት የጋራ ግቦች ተለይተው፣ የግብ ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን ይህም የዞኑን የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ሥራ በተቀናጀ አመራር፣ በግልጽ ኃላፊነትና በውጤት ተኮር አሠራር ለመምራት ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑም ተመላክቷል።

በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም በመገምገም የተሻሉ ተሞክሮዎች እንዲስፋፉ፣ የታዩ ክፍተቶች እንዲስተካከሉና በ2019 በጀት ዓመት ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

በከምባታ ዞን በዳምቦያ ወረዳና በቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ በባህላዊ የንብ ቀፎ አሠራር ዙሪያ በ' ' የተሰኘ ፕሮጀክት  የተሠራ የዶኩመንታሪ ፊልም ነው!
05/09/2026

በከምባታ ዞን በዳምቦያ ወረዳና በቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ በባህላዊ የንብ ቀፎ አሠራር ዙሪያ በ' ' የተሰኘ ፕሮጀክት የተሠራ የዶኩመንታሪ ፊልም ነው!

The documentary featured: Beehive weavers from Minaatofa in the H...

የሕጋ ሞዴል አዳሪ ትምህርት ቤት በክልሉ ከሚገኙ ሞዴል አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሁለተኛ ደረጃ የማበረታቻ ሽልማት አገኘ። በሆሳዕና ከተማ በተካሄደው 3ኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የትምህርት ጉባኤ...
04/09/2026

የሕጋ ሞዴል አዳሪ ትምህርት ቤት በክልሉ ከሚገኙ ሞዴል አዳሪ ትምህርት ቤቶች የሁለተኛ ደረጃ የማበረታቻ ሽልማት አገኘ።

በሆሳዕና ከተማ በተካሄደው 3ኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የትምህርት ጉባኤ፣ በ2018 የትምህርት ዘመን በትምህርት ዘርፍ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎችና ትምህርት ቤቶች የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል።

በዚህ የስኬት መድረክ የከምባታ ሕዝብ ልማት ማኅበር ሕጋ ሞዴል አዳሪ ትምህርት ቤት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሚገኙ ሞዴል አዳሪ ትምህርት ቤቶች መካከል በሁለተኛ ደረጃ በመሆን የማበረታቻ ሽልማት አግኝቷል።

ትምህርት ቤቱ በ2018 የትምህርት ዘመን ያስፈተናቸውን ሁሉንም ተማሪዎች በማሳለፍ ያስመዘገበው አመርቂ ውጤት ለዚህ እውቅና ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በመሆኑም ትምህርት ቤቱ የዋንጫና የሰርቲፊኬት ሽልማት ተበርክቶለታል።

በተጨማሪም ከትምህርት ቤቱ ተማሪዎች መካከል 566 ነጥብ በማስመዝገብ ከፍተኛ ውጤት ያመጣው ተማሪ በረከት ደሳለኝ የታብሌትና የሰርቲፊኬት የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶለታል።

የትምህርት ቤቱን የማበረታቻ ሽልማት ርዕሰ መምህሩ አቶ ተመስገን ዳንኤል ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እጅ ተቀብለዋል።

በ3ኛው የትምህርት ጉባኤ ከከምባታ ዞን የተውጣጡ 10 ተማሪዎችና 3 ትምህርት ቤቶች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ላስመዘገቡት ከፍተኛ ውጤት የእውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ማግኘታቸውም ተገልጿል።

የከምባታ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ዳዊት አሹሮ ይህ አበረታች ውጤት ሊመዘገብ የቻለው በመምህራን፣ በወላጆች፣ በተማሪዎችና በሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት፣ ትጋትና የጋራ ርብርብ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ ስኬት ለከምባታ ሕዝብ ልማት ማኅበር፣ ለሕጋ ሞዴል አዳሪ ትምህርት ቤት፣ ለመምህራን፣ ለተማሪዎችና ለወላጆች የላቀ ኩራት የሚሰጥ ሲሆን፣ በቀጣይም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ይህ የተቀናጀ ጥረት ይበልጥ የሚያነሳሳ ነው።

የከምባታ ሕዝብ ልማት ማኅበር ለዚህ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ ከፍተኛ ምስጋናና አድናቆቱን ያቀርባል።

#መረጃው የከምባታ ህዝብ ልማት ማህበር ነው!

በኢትዮጵያ የኢትዮሼፕ የጃፓን የሥራ ኃላፊዎች በከምባታ ዞን አዲሎ ወረዳ ሀሚዶ ጎፎሮ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር የመስክ ምልከታ አደረጉ።የመስክ ምልከታው በክልሉ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የፕ...
04/09/2026

በኢትዮጵያ የኢትዮሼፕ የጃፓን የሥራ ኃላፊዎች በከምባታ ዞን አዲሎ ወረዳ ሀሚዶ ጎፎሮ ቀበሌ የገጠር ኮሪደር የመስክ ምልከታ አደረጉ።

የመስክ ምልከታው በክልሉ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የፕሮግራሙ ዓመታዊ አፈጻጸም በክልሉ ዱራሜ ከተማ ከተገመገመ በኋላ የተካሄደ ነው።

የመስክ ምልከታውን የመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፣ በመስክ ምልከታው ለሥራ ኃላፊዎቹ ገለጻ አድርገዋል።

ግብርናን ከተለመደው የምርት አቀራረብ በማሻገር ገበያ ተኮር፣ ቴክኖሎጂ ተኮርና ውሃ ተኮር ግብርና እንዲሆን በተለይም “ምን ይመረታል? ለማን ይመረታል? መቼ ይመረታል?” በሚሉ ቁልፍ ጥያቄዎች ላይ ተመሥርቶ መሥራትን ትኩረት አድርጎ በመሥራት በአጭር ጊዜ ውጤት የመጣበት አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል።

በወጣቱ ሞዴል አርሶ አደር አብነት ዲላሞ የተሠራውን ሥራ አረንጓዴው ቡቲክ ያሉት አቶ ኡስማን ሱሩር፣ ተግባሩ አዳዲስ ልምምዶች እንዲፈጠሩ ስለማድረጉ ገልጸዋል።

በተለይም በአጭር ጊዜ በፍራፍሬ፣ በቡናና ቅመማ ቅመም ሥራዎች ከክልል አልፎ ለተለያዩ አካባቢዎች ተሞክሮ መቀየር የሚያስችል ስለመሆኑ ኃላፊው ገልጸዋል።

ይህ የወጣት አብነት ትጋት በግለሰቦች ጥረት አካባቢን መቀየር እንደሚያስችል የሚያረጋግጥ እውነተኛ ማሳያ ከመሆን አልፎ ጠንካራ አስተማሪ ተሞክሮ መሆኑን ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው ወቅት አስተያየት የሰጡት የኢትዮሼፕ የኢትዮጵያ ፕሮግራም አስተባባሪ ያሱዩዩኪ ዩሲሙራ፣ ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም የተለያዩ ቦታዎችን የመስክ ምልከታ ማድረጋቸውንና በገጠር ደረጃ በዚህ ልክ ጥራት ያላቸው ሥራዎችን ሌሎችም አካባቢዎች እንዲማሩባቸው ጥሪ አቅርበዋል።

ወጣት አርሶአደር አብነት ዲላሞ በበኩሉ የተሻለ ነገር ሰርቶ በግብርናው ዘርፍ ተጠቃሚ መሆንና የተቀናጀ የግብርና ልማትን ውጤታማ በማድረግ ድህነት ማሸነፍ እንደሚቻል ሃገራዊ ምሳሌ ለመሆን እየተጋ እንደሚገኝ ገልጿል።

በመስክ ምልከታው የፕሮግራሙ ዓለም አቀፍ አስተባባሪዎች፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፕሮግራምና ፕሮጀክት አስተባባሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

Central Ethiopia Region Bureau of Agriculture

በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው 3ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ፣ ከከምባታ ዞን የተውጣጡ አስር (10) ተማሪዎች እና ሶስት (3) ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ የትምህርት ውጤት በማስመዝገባቸው የ...
04/09/2026

በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው 3ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ፣ ከከምባታ ዞን የተውጣጡ አስር (10) ተማሪዎች እና ሶስት (3) ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ የትምህርት ውጤት በማስመዝገባቸው የእውቅና እና የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ተሸላሚዎቹ ላስመዘገቡት የላቀ አፈጻጸም የገንዘብ፣ የታብሌት እና የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት) ሽልማት አግኝተዋል።

ይህ አበረታች ውጤት ሊመዘገብ የቻለው በመምህራን፣ በወላጆች እንዲሁም በሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት እና የጋራ ርብርብ መሆኑን የከምባታ ዞን ትምህርት መምሪያ ገልጿል።

መምሪያው ለዚህ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በሙሉ የላቀ ምስጋናውን እያቀረበ፣ በቀጣይም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ይህ የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስቧል።

የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ እጩ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር ይፋ ሆነ*********************መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በሚካሄደው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኘሬዝዳንታዊ...
04/09/2026

የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ እጩ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር ይፋ ሆነ
*********************

መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም በሚካሄደው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኘሬዝዳንታዊ ምርጫ በዕጩ ፕሬዝዳንታዊ ተወዳዳሪ አቶ ኢሳያስ ጅራ የቀረቡ እጩ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና ተጠባባቂ አባላትን ስም ዝርዝር ፌዴሬሸኑ ይፋ አደርጓል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በወሰን፣ በብሔር፣ በኃይማኖት እና በሌሎችም ጉዳዮች ያልተገደበ በንጹህ ህሊና ያለ ክፍያ በእውቀት፣ በጉልበትና በዓይነት የምሰጥ አገልግሎት ነው - ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ሽመ...
04/09/2026

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በወሰን፣ በብሔር፣ በኃይማኖት እና በሌሎችም ጉዳዮች ያልተገደበ በንጹህ ህሊና ያለ ክፍያ በእውቀት፣ በጉልበትና በዓይነት የምሰጥ አገልግሎት ነው - ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ሽመልስ

''በጎነት ለእህትማማችነት ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት' በሚል መሪ ቃል የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በተለያዩ መርሃግብሮች አካሂደዋል፣

በመርሃግብሩም ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ሽመልስ እንደገለጹት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በወሰን፣ በብሔር፣ በኃይማኖት እና በሌሎችም ጉዳዮች ያልተገደበ በንጹህ ህሊና ያለ ክፍያ በእውቀት፣ በጉልበትና በዓይነት የምሰጥ አገልግሎት ነው ብለዋል፣

ወ/ሮ ኤልሳቤጥ ሽመልስ አክለውም የብልጽግና ፓርቲ ሰዎች እርስ በእርስ አንዱ ሌላውን የመደገፍና የከበደውን በማገዝ ችግር ለመፍታት ሰው ተኮር ተግባራትን ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፣

በአረንጓዴ ችግኝ ተከላ፣ በደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞችን ቤት በመገንባትና በማደስ፣ ማዕድ በማጋራት፣ በሰላም እሴት ግንባታ ስራ፣ በግብርና በትምህርት እና ጤና ዘርፎች በርካታ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አቅመ ደካሞችን ከመርዳት በተጨማሪ የህዝቦችን እርስ በእርስ አብሮነትና አንድነት ያጠናክራልም ብለዋል፣

በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት አቶ ሰለሞን ገ/መስቀል እንደገለጹት በጎነት በማህበረሰባችን ውስጥ እየተሰራ የሚገኝ የቆዬ ባህል በመሆን ይህንን ከዞን ወደ ዞን በማስተሳሰር አቅም የሌላቸውን የማህበረሰብ አካላትን ከወሰን ባሻገር መረዳዳት አንድነትን ያጠናክራልም ብለዋል፣

የነጠለ ትርክት ለማክሰም እና ገዥና አሰባሳብ ትርክት ለማጽናት የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ያለው ሚና በጣም ትልቅ በመሆኑ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በኃላፊነት ሁሉም አካል መስራት እንዳለበት አቶ ሰለሞን ገ/መስቀል ገልጸዋል፣

በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብዙነሽ ታዴዎስ በበኩላቸው የብልጽግና ፓርቲ እሳቤ የሆነውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ወደ መሬት እንዲወርድ የሴቶች ተሳትፎ ከፍ ያ ሚና እንዳለው ገልጸው በወሰን ተሻጋር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ይህንን ለማጠናከር አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል፣

በመደጋጋፍ አቅመ ደካማ የሆኑትን ተማሪዎችን፣ እናቶችንና አባቶችን መርዳት በማህበረሰባችን ውስጥ የመተማማን ባህልን ያጎለብታል ያሉት ወ/ሮ ብዙነሽ ታዴዎስ በስልጤ ዞን የተደረገው ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተማሪዎች ከት/ቤት እንዳይቀሩ የቁሳቁስ ድጋፍ፣ የዱቄትና የእህል ዘይት ድጋፍ እና ለአንድ አቅመ ደካማ ቤተሰብ የቤት ግንባታ የሚሆን የቆሮቆሮ ቅጠልና ምስማር ድጋፍ መደረጉንም ገልጸዋል፣

የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አማን ከዲር እንደገለጹት ዜጎችን ያለ ክፍያ ያለ ዕውቅና በበጎ ፈቃድ ማገልገል በሰው ዘንድ ሞራላዊ ድጋፍ የሚሰጥ መሆኑን በመግለጽ በዚህ ቅዱስ ተግባር የተሳተፉ የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት አባላትን አመስግነው እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፣

አቶ አማን ከዲር አክለውም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በገንዘብ ከሚተመን በላይ አበርክቶ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ይህም በማህበረሰቡ ውስጥ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፣

የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ጀሚላ እብርህም እንደገለጹት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቤት ግንባታና እድሳት በማድረግ፣ ማዕድ በማጋራት፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ፣ የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ በማሰራጨትና በሌሎችም በግብርና ስራ፣ በከተማ ውበትና ጽዳት ስራዎች አገልግሎቱ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፣

የፓርቲ እሴት የሆነውን እህትማማችነትን ለማጠናከር የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሚናው የጎላ መሆኑን ወ/ሮ ጀሚለ እብርህም አክለው ተናግረዋል።

#የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ!

የኢፌዴሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች በ2019 ዓ/ም የከምባታ ብሔር የዘመን መለወጫ 'መሳላ' በዓል ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ተደረገ፣ከከምባታ ዞን አስተዳደር የተወከሉ አካላት መስከረም 12...
04/09/2026

የኢፌዴሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች በ2019 ዓ/ም የከምባታ ብሔር የዘመን መለወጫ 'መሳላ' በዓል ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ተደረገ፣

ከከምባታ ዞን አስተዳደር የተወከሉ አካላት መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ/ም በተለያዩ ዝግጅቶች በአደባባይ በሚከበረው የመሳላ ክብረ በዓል ላይ በኢፌዴሪ የቱሪዝም ሚኒስቴር ክብርት ሚኒስትር የሚመራ የሚኒስቴር መ/ቤቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲታደሙ ጥሪ አድርሰዋል።

የጥሪ መልዕክቱን የሚኒስትሯ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ንጉሤ ክብሩ ተቀብለዋል።

Address

Karl Henz Street
Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ:

Shortcuts

Share