Samuel Fola

Samuel Fola Wolaita zone Chief Administrator I am a hardworking politician in Sodo, Wolaita, Ethiopia. and for more information use my telegram link
https://t.me/sami091206
(1)

I have 20+ years of experience in leadership and I am skilled in handling complex political situations. My main goal is to serve the people I represent, by communicating with them regularly and listening to their opinions, needs and concerns. My policies are designed to address these issues and improve their lives. I believe that being a politician should be about helping people, not just getting power.

15/08/2026
13/08/2026
12/08/2026
10/08/2026
04/08/2026

በተሻሻለው የኅብረት ሥራ አዋጅ የተሻሻሉ እና የተካተቱ አንቀፆች እና ንዑስ አንቀፆች
******
የተሻሻለው የኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ በተወካዮች ምክርቤት፣ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክረሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ-መንግስት አንቀጽ 55(6) መሰረት ተሻሽሎ መታወጁ ይታወቃል፡፡

አዋጁን ለማሻሻልም የኅብረት ሥራ ማህበራት ዕድገትና ተወዳዳሪነት ማሻሻያ ሪፎርም ተግባራዊ ለማድረግ ማነቆ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል የሕግ ክፍተት አንዱ እንደነበረ በጥናት ተለይቷል፡፡ እነዚህም፡-

- ከልካይ ሆነው አላሰራ ያሉ የአዋጁ ድንጋጌዎች፣
- ፈቃጅ ሆነው አላሰራ ያሉ የአዋጁ ድንጋጌዎች፣
- እንዲሁም ከለውጦች አንጻር በአዲስ የሚካተቱ ድንጋጌዎች በረቅቁ ተሻሽሎ ተዘጋጅቷል፡፡

አዋጁም በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ የታተመ ሲሆን፣ የተሻሻሉ እና አዲስ የተጨመሩ አንቀፆችን እና ንዑስ አንቀፆችን ከዚህ በታች በዝርዝር ተቀምጠዋል።

#1/ የአዋጁ አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ (10) ተሰርዞ በአዲስ ንዑስ አንቀፅ (10) ተተክቷል:-

10/ “አባል” ማለት በኅብረት ሥራ ማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት እንደኅብረት ሥራ ማህበሩ አይነት የተደነገጉትን የአባልነት መመዘኛዎችን በማሟላት ለአባልነት ጥያቄ አቅርቦ ተቀባይነት ያገኘ ግለስብ ወይም መሰረታዊ የኅብረት ስራ ማህበር ወይም የኅብረት ስራ ማህበራት ዩኒዬን ወይም የኅብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ወይም ህጋዊ ሰውነት ያለው ተቋም ነው፡፡

#2/ የአዋጁ አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ (20) ተሰርዞ በአዲስ ንዑስ አንቀፅ (20) ተተክቷል:-

20/ ‘’አግባብ ያለው ባልስልጣን’’ ማለት የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ወይም በክልል የኅብረት ሥራ ማህበራትን አዋጅ ለማስፈጻም፣ ዘርፉን ለመምራትና ለመቆጣጠር የተቋቋመ አካል ነው።

#3/ የአዋጁ አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ (21) ተሰርዞ በአዲስ ንዑስ አንቀፅ (21) ተተክቷል:-

21/ “ክልል” ማለት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 47 የተመለከተው ማንኛውም ክልል ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የድሬዳዋ አስተዳደርን ይጨምራል፤

#4/ ከአዋጁ አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ 23 ቀጥሎ አዲስ ንዑስ አንቀጽ 24፣ 25፣ 26 ተጨምሯል፣ ነባሮቹ ንዑስ አንቀጽ 24 እና 25 እንደቅድም ተከተላቸው 27 እና 28 በመሆን ተሸጋሽጓል፡፡

24. “መቀላቀል” ማለት አንድን የኅብረት ሥራ ማህበር አስፈላጊውን መስፈርት አሟልቶ ሲገኝ ከሌላ ተመሳሳይ ዓላማና ተግባር ካለው የኅብረት ሥራ ማህበር ጋር አንድ እንዲሆን በማድረግ የአንዱን ኅብረት ሥራ ማህበር ህልውና ማሳጣት ነው ፡፡

25. ‘’በልዩ ሁኔታ የሚደረግ ኦዲት’’ ማለት የኅብረት ሥራ ማህበር የኦዲት ወጪ መሸፈን እንደማይችል ሲታመን ወይም እንዲፈርስ ሲወሰን ወይም የተደረገውን ኦዲት ለማረጋገጥ ሲያስፈልግ ወይም በፍርድ-ቤት ሲታዘዝ ወይም ስጋትና ጥቆማ ሲኖር አግባብ ያለው ባለስልጣን የኦዲት ወጪውን ሸፍኖ በልዩ ሁኔታ ኦዲተር መድቦ ኦዲት ማድረግ ነው።

26. “ተቋም” ማለት የአባልነት መስፈርት አሟልቶ የመሠረታዊ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር አባል ሊሆን የሚችል ሕጋዊ ሰውነት ያለው መንግስታዊ ያልሆነ አገልግሎት ሰጪ ወይም አምራች ነው።

#5/ አንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ (5) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ (5) ተተክቷል ፡፡ አዲስ ንዑስ አንቀጽ (6) ፣ (7) ፣ (8) ፣ (9) ተጨምሯል፤

5/ ማንኛውም መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማህበር እንደ ኅብረት ስራ ማህበራቱ ዓይነት ወይም የስራ ባህሪ እና የኢኮኖሚያዊ አዋጭነት በቀበሌ ወይም በተቋም ወይም በወረዳ፣ በዞን ወይም በክልል ወይም በፌዴራል ደረጃ ይደረጃሉ፤

6/ በተመሳሳይ ተግባር ላይ የተደራጁ መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማህበራት ወይም ዩኒዬኖች ወይም ፌዴሬሽኖች ሊቀላቀሉ ይችላሉ፡፡

7/ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 5 እና 6 ስለሚደራጁበትና ስለሚቀላቀሉበት ሁኔታ ዝርዝር መመሪያ ሊወጣ ይችላል፡፡

8/መሰረታዊ የኅብረት ሥራ ማህበራት አደረጃጃት በዚህ አዋጅ አንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ 2(ሀ) ላይ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ሴቶች ወይም አካል ጉዳተኞች ወይም ወጣቶች ያለባቸውን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህላዊ ችግሮቻቸውን ለመፍታት ከሚሰሩት ልዩ ሥራ ባህሪ በመነሳት በሴት አባላት ወይም በአካል ጉዳተኞች ወይም ወጣቶች ብቻ ኅብረት ሥራ ማህበር ሊመሰረቱ ይችላሉ፡፡

9/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 8 የተጠቀሰው ቢኖርም አባልነት ለሁሉም ሰው ክፍት መሆኑን በኅብረት ሥራ ማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መወሰን አለበት፡፡

#6/ የአዋጁ አንቀጽ 9 ርዕስ እንደሚከተለው ተሻሽሏል፡፡

9. የኅብረት ሥራ ማህበር ሥም እና የሥራ ክልል፣

#7/ የአዋጁ አንቀጽ 9 ከንዑስ አንቀጽ 5 ቀጥሎ አዲስ ንዑስ አንቀጽ 6 ፣7 እና 8 ተጨምሯል፡፡

6/ ማንኛውም የኅብረት ሥራ ማህበር በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ የተወሰነ የራሱ የሥራ ክልል ይኖረዋል፡፡

7/ ማንኛውም የኅብረት ሥራ ማህበር የሥራ ክልላቸውን ማሻሻል ሲፈልጉ አግባብ ያለው ባለስልጣን በማስፈቀድ የሥራ ክልሉን ማሻሻል ይችላሉ፡፡

8/ የኅብረት ስራ ማህበራት በስራ ክልላቸው ውስጥ ወይም ከስራ ክልላቸው ውጪ ቅርጫፍ ለመክፈት ሲፈልጉ አግባብ ያለው ባለስልጣንን በማስፈቀድ መክፈት ይችላሉ፡፡ ዝርዝር አፈጻጸሙ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሚያወጣው በመመሪያ ይወሰናል፡፡

#8/ በአዋጁ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ (2) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ (2) ተተክቷል፡፡

2/ ማንኛውም የኅብረት ሥራ ማህበር ዩኒዬን እንደ ኅብረት ስራ ማህበራቱ ዓይነት ወይም የስራ ባህሪ እና የኢኮኖሚያዊ አዋጭነት እየታየ በዞን ወይም በክልል ወይም በፌዴራል ደረጃ ይደራጃሉ፤

#9/ የአዋጁ አንቀጽ 21 ንዑስ አንቀጽ (4) ፊደል ተራ (ሀ) ተሰርዞ በአዲስ ፊደል ተራ (ሀ) ተስተካክሎ ቀርቧል፡፡

ሀ) ለአባል ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒዬኖች የኦዲት አገልግሎት ማመቻቸት፣

#10/ የአዋጁ አንቀጽ 21 ከንዑስ አንቀጽ (10) ቀጥሎ አዲስ ንዑስ አንቀጽ (11) ተጨምሯል፡፡

11/ የኅብረት ሥራ ማህበራት የሥራ አመራር ኮሚቴ የሚያማክሩ አማካሪ ባለሙያዎችን ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡ ዝርዝር አፈጻጸሙን በተመለከተ መመሪያ ይወጣል፡፡

#11/ የአዋጁ አንቀጽ 23 ርዕስ እንደሚከተለው ተሻሽሏል፡፡
ከአባላት ውጭ ስለሚሰጥ አገልግሎት እና የጋራ ኢንቭስትመንት ስለመግባት

#12/ ከአዋጁ አንቀጽ 23 ንዑስ አንቀጽ (1) ቀጥሎ አዲስ ንዑስ አንቀጽ (2) ፣ፊደል ተራ (ሀ)፣ (ለ)፣ (ሐ)፣ (መ)፣ (ሠ) እና ንዑስ አንቀጽ (3) ተጨምሯል፣ ንዑስ አንቀጽ (2) ንዑስ አንቀጽ (4) ሆኖ ተሸጋሽጓል፡፡

2/ የኅብረት ሥራ ማህበራት ከግሉ ዘርፍ ጋር የሚያደርጉት የጋራ ኢንቨትመንት በጠቅላላ ጉባዔ ልዩ ውሳኔ እና የተቋቋሙበትን ዓላማና ተግባር መሠረት በማድረግ በሚከተሉት የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ ይሆናል፡፡

ሀ) በግብርና ምርት ማምረት ወይም ግብይት ወይም ማቀነባበር ወይም ፋብሪካዎች ወይም ሜካናይዘሽን ዘርፍ፣

ለ) በትራንስፖርት ወይም መሰረተ-ልማት ወይም ፋይናንስ ዘርፍ፤
ሐ) በኢነርጂ አቅርቦት ወይም ኮንስትራክሽን ወይም በማዕድን ዘርፍ፤ መ) በማህበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ወይም የአየር ንብርት ለወጥ ወይም በቱሪዘም አገልግሎት፤ ሠ/ አግባብ ያለው ባለስልጣን በጥናት በሚለያቸው የኢንቭስትምነት ዘርፎች ሊሳተፉ ይችላሉ፡፡

3/ የኅብረት ሥራ ማህበራት ከግሉ ዘርፍ ጋር ስለሚያደርጉት የጋራ ኢንቨስትመንት የኅብረት ስራ ማህበራት ድረሻ ስልሳ ከመቶ እና የኢቨሰተሮች ድረሻ አርባ ከመቶ መብለጥ የለበትም፤ ስምምነቱም በሰነድ አረጋጋጭ አካል በተመዘገበ ውል ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት።

#13/ ከአዋጁ አንቀጽ 24 ንዑስ አንቀጽ (2) ቀጥሎ አዲስ ንዑስ አንቀጽ (3) ተጨምሯል፣ ንዑስ አንቀጽ (3) ንዑስ አንቀጽ (4) ሆኖ ተሸጋሽጓል፡፡

3/ ተቋማት የመሰረታዊ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አባላት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ስለአፈጻጸሙ ዝርዝር መመሪያ ይወጣል፡፡

#14/ የአዋጁ አንቀጽ 27 ከንዑስ አንቀጽ (9) ቀጥሎ አዲስ ንዑስ አንቀጽ (10) እና (11) ፊደል ተራ (ሀ) ፣ (ለ)፣(ሐ)፣(መ)፣(ሠ) ተጨምሯል፡፡

10/ ማንኛውም የኅብረት ሥራ ማህበር ካፒታል ለማሳደግ አባል ላልሆነ ሰው ዕጣ መሸጥ ይችላል፡፡ ሆኖም የሚሸጠው ዕጣ ከታወጀው ጠቅላላ ዕጣ ከአስር ከመቶ መብለጥ የለበትም።

11/ የኅብረት ሥራ ማህበር ዕጣ የገዛ አባል ያልሆነ ሰው የሚከተሉት መብትና ግደታዎች ይኖሩታል፡፡

ሀ) በገዛው የዕጣ መጠን መሠረት የትርፍ ክፍፍል ያገኛል፤ ለ) የኅብረት ሥራ ማህበሩ ከከሰረ የኪሳራው ተጋሪ ሊሆን አይችልም፤
ሐ) የገዛው እጣ እንዲሰጠው በጠየቀ 6 ወር ውስጥ የማግኘት፤ መ) የመምረጥና የመመረጥ መብት አይኖረውም፤ ሠ) የኅብረት ስራ ማህበሩን ህልውና የሚያሳጣ ስራ ያለመስራት፤

#15/ የአዋጁ አንቀጽ 33 ንዑስ አንቀጽ (1) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (1) ተተክቷል፡፡

1/ ማንኛውም የኅብረት ሥራ ማህበር ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ የጠቅላላ ጉባዔ ማድረግ አለበት።

#16/ የአዋጁ አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 7 እንደሚከተለው ተሻሽሏል፤ ከድንጋጌው ቀጥሎም ሁለት አዲስ ንዑስ አንቀጾች (8) እና (9) ተጨምረዋል፡፡

7/ ቁጥራቸው የሚፈቅድ አባል ሴቶች በሚገኙበት ማንኛውም የኅብረት ስራ ማህበር ውስጥ ቢያንስ 50 ከመቶ አመራር በሴት አባላት መያዝ አለበት፡፡

8/ ቁጥራቸው የሚፈቅድ አባል ወጣቶች በሚገኙበት ማንኛውም የኅብረት ስራ ማህበር ውስጥ ቢያንስ 10 ከመቶ አመራር በወጣቶች አባላት መያዝ አለበት፡፡

9/ ቁጥራቸው የሚፈቅድ አባል አካል ጉዳተኞች በሚገኙበት ማንኛውም የኅብረት ስራ ማህበር ውስጥ ቢያንስ 10 ከመቶ አመራር በአካል ጉዳተኛ አባላት መያዝ አለበት፡፡

#17/ የአዋጁ አንቀጽ 39 ንዑስ አንቀጽ (3) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (3) ተተክቷል፡፡

3/ ሥራ አስኪያጁ የኅብረት ሥራ ማህበሩን የዕለት ተዕለት ተግባራት መምራት፤ በተሰጠው የሥራ ዝርዝር እና ውክልና መሠረት በሥራ አመራር ኮሚቴ የሚሰጡትን ሥራዎች በግልጸኝነት፣ በተጠያቂነት እና በሙሉ ኃላፊነት ማከናወን አለበት፡፡

#18/ የአዋጁ አንቀጽ 45 ንዑስ አንቀጽ (2) ተሰርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀፅ (2) ተተክቷል፡፡

2/ ለመጠባበቂያ ከተቀነሰ በኃላ የተጣራ የትርፍ ክፍፍል 3 ከመቶ ለኅብረት ሥራ ፈንድ የሚውል ሲሆን ቀሪው 67 ከመቶ የኅብረት ሥራ ማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ በሚወስነው መሰረት የሚከፋፈል ይሆናል።

#19/ የአዋጁ አንቀጽ 50 ንዑስ አንቀጽ (1) ተሰርዞ የሚከተሉት አዲስ ንዑስ አቀጽ (1)፣(2) ፣(3) እና (4) ተጨምረዋል፣ ነባሮቹ ንዑስ አንቀጽ (2)፣(3)፣(4) እና (5) በቅድም ተከተላቸው (5)፣ (6)፣ (7) እና (8) ሆነው ተሸጋሽገዋል፡፡

1/ ማንኛውም የኅብረት ሥራ ማህበር ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ የኦዲት ወጪውን ሸፍኖ ሂሳቡን ኦዲት ማስደረግ አለበት።

2/ የኅብረት ሥራ ማህበራት ሂሳብ ኦዲት የሚደረገዉ በኅብረት ሥራ ሊግ ወይም በኦዲት ሙያ በተደራጁ የኅብረት ሥራ ማህበር ወይም ህጋዊ የኦዲት ፈቃድ ባለው ሰው ነዉ፡፡

3/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) የተደነገገዉ ቢኖርም አግባብ ያለው ባለስልጣን በልዩ ሁኔታ የኅብረት ሥራ ማህበራት ሂሳብ ኦዲት ማድረግ ይችላል።

4/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ አግባብ ያለው ባለስልጣን ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው ኦዲተሮችን ይለያል፣ የኦዲት ሂደትን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣ በትክክል መሰራቱን ያረጋግጣል ፣ ስህተት ሲኖር ማስተካክያ እርምጃ ይወስዳል፣ ለጉባኤ አስቀርቦ እንዲጸድቅ ያደረጋል ፣ ስለ አፈጻጸሙ ዝርዝር መመሪያ ያወጣል፡፡

#20/ ከአዋጅ አንቀጽ 52 ንዑስ አንቀጽ (4) ቀጥሎ የሚከተሉት አዲስ ንዑስ አንቀጽ (5) እና (6) እና (7) ተጨምሯል።
5/ የቁጠባና ብድር የኅብረት ሥራ ማህበራት የፋይናንስ እንቅስቃሴዎችን አግባብ ባለው ባለስልጣን በሚወጣ መለኪያ ስታንዳርድ ኢንስፔክት ይደረጋል፡፡

(6) የኅብረት ሥራ ማህበራት ኢንስፔክት ሲደረግ አዋጁን፣ ይህንን አዋጅ ለማስፈጸም የሚወጡ ደንብና መመሪያዎችን ተላልፈው በሚገኙ ኅብረት ስራ ማህበራት ፤ የኅብረት ስራ ማህበራት አመራር ኮሚቴ፣ ስራ አስኪያጆች፣ ቅጥር ሰራተኞች ላይ አግባብ ያለው ባለስልጣን አስተዳደራዊ ማስተካከያ እርምጃ ይወሰዳል፡ ዝርዝር አፈጻጸሙም በሚኒስትሮች ምክር ቤት በሚወጣ ደንብ ይወሰናል፡፡

7/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 6 ያለው እንደተጠበቀ ሆኖ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ሌሎች አካላት ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰዱ ይደረጋል፡፡

#21/ የአዋጁ አንቀጽ 70 ንዑስ አንቀጽ 1 እንደገና ተሻሽሎ ቀርቧል፤ በተጨማሪም አዲስ ሁለት ንዑስ አንቀጾች (2) እና (3) ሆነው የገቡ ሲሆን ሌሎቹ ንዑስ አንቀጾች በቅደም ተከተላቸው ተሸጋሽገዋል፡፡

1/ የኅብረት ስራ ማህበትን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያደራጃል፣ ያጠናክራል ዲጀታላይዝ በሆነ ሥርዓት ይመዘግባል፣ ያድሳል፣ ይቆጣጠራል ፣ ይሰርዛል፡፡

2/ የኢትዮጵያ ኅብረት ስራ ኮሚሽን ሀገር አቀፍ ተፈፃሚነት ያለው የኅብረት ስራ ማህበራት ሀገረዊ መረጃዎችን ለመያዝ ዲጅታላይዝ መረጃ ማዕከል ያቋቁማል፣ ያስተዳድራል፣ መረጃዎችን ይተነትናል ለህዝብ ክፍት እንዲሆንም ያደርጋል፡፡

3/ አግባብ ያለው የክልል ባለስልጣን የኅብረት ስራ ማህበራትን የምዝገባ ምስክር ወረቀት ምዝገባ ፣ እድሳት፣ ስረዛ ያከናውናል መረጃዎችን በዲጅታላይዝ የመረጃ ማዕከል የመረጃ ቋት ያስገባል፡፡ ስለዝርዝር አፈጸጸሙ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሚያወጣው መመሪያ ይወሰናል፡፡

- አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ
ይህ አዋጅ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡
አዲስ አበባ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም
ታዬ አጽቀስላሤ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ
ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት

ይህ አዋጅ ከነባሩ (ማሻሻያ ካልተደረገባቸው አንቀጾች) አዋጅ ቁጥር 985/2009 ጋር ስራ ላይ የሚውል ሲሆን፣ ሙሉ የአዋጁን ክፍል በኮሚሽኑ ድረ-ገፅ ወይም ቴሌግራም ገፅ በመግባት ወይም በአስተያየት መስጫ ላይ በምናስቀምጠው ሊንክ ገብታችሁ መመልከት ትችላላችሁ።



----------
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ስለኅብረት ሥራ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት👇

✅ ድረ-ገጽ፦ www.fca.gov.et
**
✅ ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/share/r/1EYk9baDd3/
**
✅ ዩቲዩብ፦https://www.youtube.com/
**
✅ ቴሌግራም፦https://t.me/ethiocoopnews

✅ ትዊተር (X)፦https://x.com/Ecccoop

03/08/2026

ዛሬ እያካሄድን ባለው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር፣ ሁላችንም በጋራ በመቆም ለተሻለችና ለአረንጓዴ ሀገር መሠረት እየጣልን እንገኛለን።

ይህ ዘመቻ የምድርን ውበት የመመለስና የተፈጥሮ ሀብታችንን የመንከባከብ ጥረት ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ አስተማማኝ ተስፋን የመትከል ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ ነው።

በእያንዳንዱ በምንተክለው ችግኝ ውስጥ የተሻለ ነገን የመገንባት ቁርጠኝነታችንና አንድነታችን በግልጽ ይታያል።
በመሆኑም የተቀመጠውን ዕለታዊ ግብ በተሳካ ሁኔታ ለመፈፀምና የታለመውን አረንጓዴ ልማት እውን ለማድረግ በሙሉ ተነሳሽነት ወደፊት መራመዳችንን እንቀጥላለን።

አሁን የምናስመዘግበው ስኬት የሁላችንንም የተቀናጀ ጥረት የሚጠይቅ በመሆኑ፣ በተከታታይነትና በፅናት በመስራት የጀመርነውን የታሪክ ዐሻራ በላቀ ውጤት እናጠናቅቃለን።

03/08/2026

በኅብረት የተስፋ አሻራችንን በማኖር ዳግም ታሪክ መስራት ችለናል!

ዛሬ ሐምሌ 27/2018 ዓ/ም በሀገራዊው የአረንጓዴ አሻራ የአንድ ጀንበር ተከላ በክልላችን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን 69 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል አቅደን፤ ተፈጥሮን መጠበቅ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በውል በተረዳው የክልላችን ህዝብ ንቁ ተሳትፎ ለመጪው ትውልድ የተስፋ አሻራችንን ለማኖር በጋራ ባደረግነው ርብርብ ከዕቅድ በላይ 76 ሚሊዮን ችግኞች በመትከል እንደ ሀገር ዳግም ለአለም ተምሳሌት የሆነ ታሪክ መስራት በመቻላችን የተሰማኝን ልባዊ ደስታ እየገለጽኩ ለመላው የክልሉ ህዝብ የላቀ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡

በዕለቱ በመላዉ የክልላችን ህዝቦች ፅናት እና ትጋት ለተመዘገበው ስኬት በማስተባበርና በመምራት ጉልህ አስትዋጽኦ ላበረከታችሁ እንዲሁም ከማለዳ እስከ ምሽት በትጋት ለተከላችሁ በሙሉ ዳግም ልባዊ ምስጋናዬን እያቀረብኩ፤ በቀጣይ የተተከሉትን በመንከባከብና በመጠበቅ ደህንነቱ የተጠበቀ አረንጓዴ ከባቢን ለትውልድ ለማሻገር እንድንተጋ ከአደራ ጭምር አሳስባለሁ፡፡

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!!

Address

Wolaita Sodo, Ethiopia, Arba Mintch, Ethiopia , Addis Ababa, Ethiopia, 1000
Ethiopia

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Samuel Fola posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Samuel Fola:

Shortcuts

Share