ምዕራብ ጎጃም ዞን የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት

ምዕራብ ጎጃም ዞን የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት The zone works diligently to ensure citizens' right to live in clean and unpolluted areas.

"ፅዱ ኢትዮጵያ ለተተኪው ትውልድ"በሚል መሪ ቃል የጽዳት ንቅናቄ ተካሄደ።በምዕራብ ጎጃም ዞን የጃቢ ጠህናን ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት “ፅዱ ኢትዮጵያ ለተተኪው ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በማ...
19/08/2026

"ፅዱ ኢትዮጵያ ለተተኪው ትውልድ"በሚል መሪ ቃል የጽዳት ንቅናቄ ተካሄደ።

በምዕራብ ጎጃም ዞን የጃቢ ጠህናን ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት “ፅዱ ኢትዮጵያ ለተተኪው ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በማንኩሳ ከተማ የጽዳትና አካባቢ ጥበቃ ንቅናቄ መድረክ እያካሄደ ነው።

ንቅናቄው የከተማዋን ንጽህና ለማስጠበቅ፣ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስና የህብረተሰቡን የንጽህና ባህል ለማጠናከር ያለመ ነው።

የጃቢ ጠህናን ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ታደሰ እንደገለፁት አካባቢን ከብክለት መጠበቅና ንጽህናን ማስጠበቅ የጤና፣ የውበትና የዘላቂ ልማት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። ህብረተሰቡ ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ፣ የጋራ ቦታዎችን በመጠበቅና የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎችን በመደገፍ የራሱን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ዳኛቸው አክለውም፣ የንጽህናና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ የአንድ ቀን ዘመቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው የሁሉም የጋራ ተግባር መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። በመሆኑም የአሁኑ ትውልድ ለተተኪው ትውልድ ንጹህ፣ ጤናማና ተስማሚ አካባቢ ለማስረከብ በቁርጠኝነት መሥራት እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመድረኩ የጃቢ ጠህናን ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሆድአዲስ አማረ እንደገለጹት፣ ንጹህና ለኑሮ ምቹ አካባቢ መፍጠር የመንግሥትና የአንድ ተቋም ብቻ ኃላፊነት ሳይሆን የሁሉም ዜጋ የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ጠቁመዋል።

በተለይም ማኅበረሰቡ በንጽህና ሥራዎች በንቃት በመሳተፍ የከተማውን ውበትና ንጽህና ለመጠበቅ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ አሳስበዋል።

ወ/ሮ ሆድአዲስ አክለውም፣ “ፅዱ ኢትዮጵያ ለተተኪው ትውልድ” የሚለው መሪ ቃል ንጽህናን የዕለት ተዕለት ተግባርና የኑሮ ባህል ማድረግ እንደሚገባ የሚያስገነዝብ መሆኑን ገልጸው፣ ከቤተሰብ ጀምሮ በማኅበረሰብ ደረጃ የንጽህና ባህልን ማጎልበት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የውይይት ሰነዱ በጃቢ ጠህናን ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት የአካባቢ ትምህርትና ግንዛቤ ማስፋፊያ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ሀብታሙ ደምሴ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በመጨረሻም የጽዳትና አካባቢ ጥበቃ ሥራው በአንድ ቀን ንቅናቄ የሚጠናቀቅ ሳይሆን በየጊዜው በመቀጠል ዘላቂ የሆነ የንጽህና ባህል መፍጠር እንደሚገባ ተጠቁሟል። “ፅዱ ኢትዮጵያ ለተተኪው ትውልድ” የሚለው መሪ ቃልም አሁን ያለው ትውልድ ለሚመጣው ትውልድ ንጹህ፣ ጤናማና ተስማሚ አካባቢ የማስረከብ ኃላፊነትን የሚያሳስብ መልዕክት መሆኑ ተገልጿል።

የበለጠ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮችን ሊንክ ይጫኑ !!

Facebook http://facebook.com/westgojjamenvironmental
Telegram https://t.me/Westgojamzoneenvirometalprotecti
You Tube https://www.youtube.com/
titoki www.tiktok.com/

በፍኖተ ሰላም ከተማ የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የከተማ ጽዳት ንቅናቄ ተካሄደ።  ነሀሴ 13/2018 ዓ.ም ፍ/ሰላም ኮሙኒኬሽን በምዕራብ ጎጃም ዞን በፍኖተሰላም ከተማ "ፅዱ ኢትዮጵያ ለትው...
19/08/2026

በፍኖተ ሰላም ከተማ የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የከተማ ጽዳት ንቅናቄ ተካሄደ።

ነሀሴ 13/2018 ዓ.ም ፍ/ሰላም ኮሙኒኬሽን
በምዕራብ ጎጃም ዞን በፍኖተሰላም ከተማ "ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል የአካባቢ ብክለትን ለመከለል ፣ የከተማዋን ጽዳትና ውበት ለማስጠበቅ ያለመ የከተማ ጽዳት ንቅናቄ ተካሄደ።

በንቅናቄው የተለያዩ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች ፣ ሰራተኞች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና ሌሎች የማህበረሰብ አባላት በመሳተፍ የጎርፍ ማፋሰሻዎችን ፣ የህዝብ መገልገያ ስፍራዎችንና አካባቢዎችን በማጽዳት የከተማዋን ንጽህና ለመጠበቅ ሰፊ ስራ ተሰርቷል ።

በፅዳት ንቅናቄ ዘመቻው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፋት የፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጊዜው ደግአረገ ንጽህናን መጠበቅ በመንግስት ብቻ ስለማይቻል ህዝባዊ ለማድረግ የተጀመረ ስራ በሚፈለገው ልክ ባይሆንም መሻሻሎች አሉ ብለዋል።

ፅዳት ባህል እንዲሆን የሁሉም ነዋሪ በህብረት መሳተፍ ግዴታ መሆኑን በመግለጽ፣ ከተማ ፅዱና ማራኪ ሲሆን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፋ ጥሩ እንቅስቃሴ እንደሚኖርና ኢንቨስትመንት እደሚስፋፋ ተናግረዋል ።

ፅዳቱን በአስተባባሪነት የመሩት የፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወርቁ በላይ "ከተማና ህፃን እንክብካቤ ይፈልጋሉ" በማለት ንጹህና ውብ ከተማ ለመፍጠር የአንድ ቀን ንቅናቄ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ግንዛቤ በመፍጠር ቀጣይነት እንዲኖረውና በዘላቂነት በማስቀጠል ተላላፊ በሽታዎችን መከላከል ይቻላል ብለዋል።

ነዋሪዎች ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድና የአካባቢያቸውን ንጽህና በመጠበቅ በየቀኑ የሚፈፅሙት ተግባራዊ መሆን እንዳለበት አሳስበዋል ።

በፅዳት ዘመቻው ሲሳተፉ አግኝተን ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች አቶ አየነው ላቀ እና መሪም ሙሀመድ አካባቢ በቆሻሻ ሲበከል ለተለያዩ በሽታዎች እንጋለጣለን ፤ ይህ እንዳይሆን ከተማችንን በማፅዳት ውብና ማራኪ ማድረግእንዳለባቸወና ስራው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል።

Finote Selam City Communications

19/08/2026
ለኑሮ ምቹና ውብ የሆነች ፍኖተ ሰላምን ለመፍጠር ቋሚ የጽዳት ዘመቻ ተጀመረ።«ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ» በፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ውብና ንጹህ አካባቢን ለመፍጠር የጽዳት ዘመቻ ተጀመረ።«...
19/08/2026

ለኑሮ ምቹና ውብ የሆነች ፍኖተ ሰላምን ለመፍጠር ቋሚ የጽዳት ዘመቻ ተጀመረ።

«ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ» በፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ውብና ንጹህ አካባቢን ለመፍጠር የጽዳት ዘመቻ ተጀመረ።

«ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ» በሚል ሀገራዊ መሪ ሀሳብ ጽዱ፣ ውብ እና ለኑሮ ምቹ የሆነች ፍኖተ ሰላም ከተማን ለመፍጠር በዓሉን በመጽዳት ዘመቻ ማክበር መጀመሩን ከተማ አስተዳደሩ ገልጿል።

ጽዱ ከተማን ለትውልድ ለማስረከብ እንዲሁም የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል የሚደረገው ሁለንተናዊ ርብርብ በከተማው ተጠናክሮ መቀጠሉን በጽዳት ዘመቻ መክፈቻ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የገለጹት የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጊዜው ደግአረገ፤ የከተማውን የአካባቢ ሥነ-ምህዳር በመጠበቅ ለነገው ትውልድ ጤናማና አረንጓዴ ምድርን ማውረስ የዕለት ተዕለት ኃላፊነታችን ሊሆን ይገባል ብለዋል።

የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮናስ ሞላ በበኩላቸው ጽዳትና ውበት የመንግሥትና የፓርቲ ኢኒሼቲቭ ተግባር በመሆኑ በከተማ አስተዳደሩ የተጀመረውን የጽዳት ዘመቻ አጠናክሮ በውጤታማነት በመቀጠል በዚህ በጀት አመት አራት ሞዴል መንደር ለመፍጠር ታቅዶ ሥራ መጀመሩንም በፕሮግራሙ ላይ ይፋ አድርገዋል።

በጽዳት ዘመቻው በክብር እንግድነት ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የምዕራብ ጎጃም ዞን የአካባቢ ጥበቃ የመምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መዓዛ ገበየሁ በበኩላቸው፤ የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ጽዱና ለኑሮ የተመቸ አካባቢን መፍጠር የአንድ ቀን ሥራ ብቻ ሳይሆን በዘላቂነት ማህበረሰቡ አሁን የጀመረውን መልካም ሥራ አጠናክሮ በማስቀጠል ለቀጣዩ ትውልድ ጤናማ አካባቢን ማስረከብ ያስፈልጋል ብለዋል።

በዚህ አገር አቀፍ የጽዳት ዘመቻ የከተማ አስተዳደሩ ነዋሪዎች፣ የድርጅትና የሆቴል ባለቤቶች፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በንቃት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

«ድንቅ ምልዑ ሀገር ለትውልድ መሠረት ነው!»

የአካባቢ ብክለትን በመከላከል ጽዱ ኢትዮጵያን ለትውልድ እናስተላልፍ!

የበለጠ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮችን ሊንክ ይጫኑ !!

Facebook http://facebook.com/westgojjamenvironmental
Telegram https://t.me/Westgojamzoneenvirometalprotecti
You Tube https://www.youtube.com/
titoki www.tiktok.com/

🌿🇪🇹 “ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ” 🇪🇹🌿3ኛው ዙር የ“ፅዱ ኢትዮጵያ” ንቅናቄ መድረክ በቋሪት ወረዳ ተካሄደበምዕራብ ጎጃም ዞን በቋሪት ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽ/ቤት “ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውል...
18/08/2026

🌿🇪🇹 “ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ” 🇪🇹🌿

3ኛው ዙር የ“ፅዱ ኢትዮጵያ” ንቅናቄ መድረክ በቋሪት ወረዳ ተካሄደ

በምዕራብ ጎጃም ዞን በቋሪት ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽ/ቤት “ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው 3ኛው ዙር የ“ፅዱ ኢትዮጵያ” ንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የምዕራብ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ መዝገቡ ውቤ፣ የቋሪት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መኳንንት ወርቅነህ፣ የወረዳው አመራሮች፣ የመንግሥት ሰራተኞች፣ ባለድርሻ አካላት እና የተመረጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

በመድረኩ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል። በተጨማሪም የወረዳውን አካባቢ ከቆሻሻ ነፃ ለማድረግ በሚቻልበት መንገድ ላይ ውይይትና ምክክር ተካሂዷል።

በውይይቱም ወረዳችንን ከቆሻሻ ፅዱ ማድረግ የመንግስት ተቋማት ብቻ ኃላፊነት ሳይሆን የሁሉም የማህበረሰብ የጋራ ኃላፊነት መሆን እንዳለበት ተጠቁሟል። እያንዳንዱ ዜጋ በየአካባቢው ንፅህናን በመጠበቅ፣ ቆሻሻን በአግባቡ በመለየትና በማስወገድ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

እንዲሁም ለዘላቂ ውጤት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተጠናክረው በቀጣይነት መቀጠል እንዳለባቸው አፅንዖት ተሰጥቷል። ለቀጣይም በወረዳው ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ያሳተፈ አጠቃላይ የፅዱ ኢትዮጵያ ዘመቻ ለማካሄድ አቅጣጫ ተቀምጧል።

🌱 ፅዱ ወረዳ — ጤናማ ማህበረሰብ — የተሻለ ትውልድ!

🇪🇹 “ፅዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ”

17/08/2026
ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመያዝና በማስወገድ ፅዱ አካባቢን ለመፍጠር መረባረብ እንደሚገባ ተገለፀ***በምዕራብ ጎጃም ዞን ወምበርማ ወረዳ ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመያዝና በማስወገድ ፅዱ አካባ...
17/08/2026

ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመያዝና በማስወገድ ፅዱ አካባቢን ለመፍጠር መረባረብ እንደሚገባ ተገለፀ
***
በምዕራብ ጎጃም ዞን ወምበርማ ወረዳ ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመያዝና በማስወገድ ፅዱ አካባቢን ለመፍጠር መረባረብ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

የወረዳው አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽህፈት ቤት ‹‹ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ ›› በሚል መሪ ቃል በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም አካሂዷል፡፡በዚህም ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመያዝና በማስወገድ ፅዱ አካባቢን ለመፍጠር መረባረብ እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡

የህዘብ ቁጥር እየጨመረ የከተማ እድገት በሰፋ ቁጥር ማህበረሰቡ የሚጠቀማቸውና የሚጥላቸው ቆሻሻዎች እየጨመሩ በመምጣታቸው ለጤና እክል ምክንያት ሲሆኑ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ በማዘጋጀት እና በአግባቡ በማስወገድ ፅዱ አካባቢን ልንፈጥር ይገባል ሲሉ ተሳታፊዎች አንስተዋል፡፡
የአካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ትምህርቴ ምናሉ እንደተናሩት ደረቅ ቆሻሻ በየቦታው እንዳይጣልና የአካባቢ ብክለት እንዳይከሰት ለመከላከል የግንዛቤ መድረክ የተካሄደ ሲሆን ይህም ፅዱ አካባቢን በመፍጠር ጤናን ለመጠበቅ ያግዛል ብለዋል፡፡

የወረዳው ብልፅግና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አስማረ መኮነን እንዳስረዱት ለአካባቢያችን እንክብካቤ ባለማድረጋችን በቶሎ የማይቀለበስ የተፈጥሮ አደጋ እን የጤና ጠንቅ እንዲከሰት ምክንያት ሲሆን በአካባቢያዊ ሁለንተናዊ ነገር ቀድሞ በመዘጋጀት፤ የራስን ድርሻ በመውሰድ ቆሻሻን ከምንጩ በመለየት እና በየቦታው የሚጣለውን በመከላከል ፅዱና ተስማሚ አካባቢ ለመፍጠር ጥረት መደረግ አለበት ብለዋል፡፡

የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብዩ ጌቴው በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳስረዱት የማይበገር አረንጓዴ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚደረግ አንዱ ጥረት ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝ ችግር በብከለት ምክንያት የጤና እክል እየተፈጠረ የመጣ ሲሆን ከፕላስቲክ ከረጢት ጀምሮ እስከ ደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ በማስወገድ አካባቢንና ጤናን መጠበቅ ይገባል ብለዋል፡፡

የበለጠ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮችን ሊንክ ይጫኑ !!

Facebook http://facebook.com/westgojjamenvironmental
Telegram https://t.me/Westgojamzoneenvirometalprotecti
You Tube https://www.youtube.com/
titoki www.tiktok.com/

16/08/2026

ውሃ አዘል መሬት ምንድን ነው ?

ውሃ አዘል መሬት (Wetland) ማለት ውሃ መሬቱን ወይም አፈሩን ለረጅም ጊዜ ወይም በየወቅቱ የሚያጥለቀልቅበትና የተለየ የተፈጥሮ ሥርዓተ-ምሕዳር የሚፈጥርበት ቦታ ነው። እነዚህ ሥፍራዎች ረግረጋማ ቦታዎች፣ የደለል ሜዳዎች፣ የሐይቆችና የወንዞች ዳርቻዎች እንዲሁም ረግረጋማ ደኖችን ያካትታሉ።

የውሃ አዘል መሬቶች ተፈጥሯዊ ፋይዳዎች እና አገልግሎቶች እንደሚከተለው ተደራጅተዋል፡-

የውሃ ማጠራቀሚያና ማጣሪያ፡ ጎርፍን በመቆጣጠር ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ። ከመጠን በላይ የሆነ ውሃን በመሰብሰብ እንዲሁም መሬት ውስጥ እንዲሰርጽ በማድረግ የከርሰ ምድር ውሃን ይሞላሉ። በተጨማሪም በውሃ ውስጥ የሚገኙ አላስፈላጊ ነገሮችንና ቆሻሻዎችን በማጣራት የውሃውን ጥራት ይጠብቃሉ።

የብዝኃ ሕይወት መኖሪያ፡ ለበርካታ የዓሣ፣ የዱር እንስሳት፣ አምፊቢያን እና አእዋፍ (በተለይ ስደተኛ ወፎች) ዋና መኖሪያና መራቢያ ናቸው።

የአየር ንብረት መቆጣጠሪያ፡ ከፍተኛ መጠን ያለው ካርቦን ጋዝ በመመጠጥ (Carbon sink) ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።

የአካባቢና ማኅበራዊ ፋይዳ፡ ለእንስሳት መኖ (ሣር)፣ ለባህላዊ ግንባታ (እንደ ቄጤማ/ፓፒረስ ያሉ) እና ለመስኖ እርሻ አገልግሎት ይሰጣሉ።
የውሃ አዘል መሬቶች በኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ሀብታም የሆኑ የውሃ አዘል መሬቶች አሏት። ከእነዚህም መካከል በባሮ-አኮቦ፣ በኦሞ-ጊቤ፣ በአዋሽ ሸለቆ፣ በጣና ዙሪያ (ፎገራ)፣ በደብረ ዘይት ሐይቆች እንዲሁም በባሌ ተራሮች የሚገኙ ረግረጋማ ሥፍራዎችና ሐይቆች ተጠቃሾች ናቸው። በአገሪቱ ውስጥ ያሉት የውሃ አዘል መሬቶች ወደ 2 በመቶ የሚሆነውን የአገሪቱን የቆዳ ስፋት ይሸፍናሉ። ይሁን እንጂ የእርሻ ቦታዎችን ማስፋፋት፣ የከተሞች መስፋፋት፣ የኢንዱስትሪ ፍሳሽ እና ከመጠን በላይ የግጦሽ አጠቃቀም ለእነዚህ ስሱ ሥርዓተ-ምሕዳሮች ትልቅ ሥጋት እየሆኑባቸው ይገኛል።

የበለጠ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮችን ሊንክ ይጫኑ !!

Facebook http://facebook.com/westgojjamenvironmental
Telegram https://t.me/Westgojamzoneenvirometalprotecti
You Tube https://www.youtube.com/
titoki www.tiktok.com/

16/08/2026
"አረንጓዴ አሻራ በጋራ የምንጽፈው የወል ታሪክና ለትውልድ የሚተርፍ ቅርስ ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
16/08/2026

"አረንጓዴ አሻራ በጋራ የምንጽፈው የወል ታሪክና ለትውልድ የሚተርፍ ቅርስ ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Address

Finote Selam
Finote Selam

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ምዕራብ ጎጃም ዞን የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share