የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ

የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ, Government Organization, Finote Selam, Finote Selam.

09/04/2026

የ2018 ዓ/ም የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት እየተሰራ ነዉ፡፡             =*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=የምዕ/ጎጃም ዞን ን...
08/04/2026

የ2018 ዓ/ም የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት እየተሰራ ነዉ፡፡
=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=*=
የምዕ/ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ መጭውን የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት እየሰራ እንደሆነ የምዕ/ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አለልኝ አሠፋ ገልፀዋል፡፡

ገበያውን በማረጋጋት ሸማቹ ከደላላ ነፃ በሆነ መንገድ ከአምራቹ ግብይቱን እንዲፈጽም ለማድረግ መምሪያው ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል ።

በተለይ ማህበረሠቡ ከሚጠቀምባቸው ምርቶች መካከል ሠንጋ፣ዶሮ፣እንቁላል፣ሽንኩርት፣ ዘይት፣ ዱቄት ምርቶች በሠፊው ለሸማቹ በማቅረብ ገበያውን የማረጋጋት ስራ እየተሠራ ሲሆን በተለይ በነዳጅ እጥረት ምክንያት በምርት ላይ ያልተገባ የዋጋ መጨመር ተከስቶ የነበረ ቢሆንም በጋራ ጥረት አምራቹን እና ሸማቹን በቀጥታ የማገናኘት ስራ በመሠራቱ ገበያውን የማረጋጋት ተግባር ተፈጽሟል ።
ከመደበኛው ገበያ ውጭ በዓሉን መሠረት በማድረግ ገበያውን ለማረጋጋት የቀረበውን ምርት
#በሸማቾች
#በሱፐርማርኬት
#በፌቤላ ፋብሪካ ወኪል ዳሞት ዮኒየን በሠፊው ምርት የማቅረብ ስራ ተሠርቷል ።

 ።የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ከዞኑ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያና ማደራጃ ጽህፈት ቤት ጋር በጋራ በመተባበር የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ ለዞን መንግስት ሰራተኞች በ...
08/04/2026



የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ከዞኑ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያና ማደራጃ ጽህፈት ቤት ጋር በጋራ በመተባበር የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ ለዞን መንግስት ሰራተኞች በረጅም ጊዜ ክፍያ የቀለብ ጤፍ ማሰራጨቱን ገልጸዋል።

ይህ ተግባር በበዓል ወቅት የሚጨምሩ የኑሮ ወጪዎችን ለመቀነስና ለሰራተኞች እፎይታ ለመፍጠር ያለመ ነው።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ አለልኝ አሰፋ በዚህ ወቅት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን ከቦታ ቦታ ለማንቀሳቀስ እንደ አለማቀፍ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን ጠቅሰዉ በዚህ ችግር ዉስጥም ሆኖ መምሪያዉ የኑሮ ዉድነቱን ለማረጋጋት ታሳቢ በማድረግ በተለይም ለእንደዚህ አይነት ተግባራቶች የቅድሚያ ቅድሚ በመስጠት ነዳጅ የሚያገኙበትን መንገድ በማመቻቸት መኪኖች ምርት ካለበት ቦታ ድረስ ሄደዉ እንዲያመጡ መምሪያዉ ብዙ ጥረት አድርጓል ነዉ ያሉት።
የምዕራብ ጎጃም ዞን ህ/ስራ ጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወ/ሪት አማረች ነግሬው አክለዉ ከ350 ኩንታል በላይ ጤፍ ለዞን ተቋማት የመንግስት ሰራተኞች ተሰራጭቷል።

ምርቱም በዳሞት ዩንየን በኩል በኩንታል 9 ሺህ 500 ብር የቀረበ ሲሆን ከመደበኛው ገበያ እስከ 2 ሺህ ብር ድረስ ቅናሽ እንዳለው ገልጸዋል።

ይሁን እንጅ እነዚህ ተቋማት የገበያ ማረጋጋት ስራውን በትኩረት እየሰሩ ያሉ ሲሆን፣ ባለፉት 9 ወራት ከ103 ሚሊዮን ብር ተዘዋዋሪ በጀት በመመደብ ከ4 ሺህ 300 ኩንታል በላይ የኢንዱስትሪ ምርቶችን እና እንደ ዘይት፣ ስኳር፣ መኮሮኒና ፓስታ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች ማቅረብ መቻሉን አንስተዋል።

ተጠቃሚዎች በበኩላቸው በበዓሉ ወቅት ምርቱ መቅረቡ የቤተሰብ ወጭዎችን ቀንሶልናል ብለዋል።

በተለይም የቀረበው ጤፍ በ6 ወር የእፎይታ ጊዜ የሚከፈል መሆኑ፣ ዝቅተኛ ተከፋይ ሰራተኞች የበለጠ ተጠቃሚ የሚያደርግ ተግባር ነዉ።




#ቅድሚያ
#ትኩረት

በምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የደምበጫ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመንግስት ሰራተኞች የሽንኩርት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ አቀረ...
08/04/2026

በምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የደምበጫ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመንግስት ሰራተኞች የሽንኩርት ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ አቀረበ።

በዚህም በበዓል ጊዜ የሚጨምር የሽንኩርት ዋጋ ጫናን ለመቀነስ ታስቦ የተደረገ ነው።

የደምበጫ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላይ ዘሪሁን እንደገለጹት ይህ እቅድ በበዓል ወቅት ለሰራተኞች የሚፈጠር የኑሮ ውድነት ጫና ለመቀነስ የተዘጋጀ ነው።
ከተማ አስተዳደሩ ለበዓል ዝግጅት ሌሎች አስፈላጊ የምግብ እቃዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በበዓል ሰሞን ሊከሰት የሚችልን  የዋጋ ጭማሬ ለማረጋጋት እየሰራ እንደሆነ ገለፀ‎‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት መጪው...
07/04/2026

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በበዓል ሰሞን ሊከሰት የሚችልን የዋጋ ጭማሬ ለማረጋጋት እየሰራ እንደሆነ ገለፀ

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት መጪው የትንሳኤ በዓል ምክነያት በማድረግ ለመንግስት ሰራተኞች ሽንኩርትና ዘይት አቅርቧል።

‎ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤቱ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክነያት በማድረግ መንግስት ሰራተኞች በቀጥታ ከአምራቾች የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን እያቀረበ እንደሆነ የወረዳው ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጥሩ መኩሪያ ተናግረዋል።

‎ወ/ሮ ጥሩ መኩሪያው አክለውም የኑግ ዘይት ከሊትር 30ብር ቅናሽና እና ሽንኩርት ከ25 እስከ 30ብር ቅናሽ በማድረግ እያሰራጨን ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

‎እንደ ሃላፊዋ ገለፃ ጽ/ቤቱ ያቀረበው ምርት በበዓል ገበያ ሊከሰት የሚችለውን የዋጋ ጭማሬ ለማረጋጋት ያግዛል ነው ያሉት።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ::==============================መጋቢት 25/2018 ዓ/ምፍ/ሠላም፣የምዕራብ ጎጃም ዞን ...
07/04/2026

የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የ9 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ::
==============================
መጋቢት 25/2018 ዓ/ም
ፍ/ሠላም፣
የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ አለልኝ አሰፋ በመክፈቻ ንግግራቸዉ የንግድ መሠረቱን በማስፋፋት፣ህጋዊ የንግድ ሽፋንን በማጠናከር፣የሸማቹን መብት በማስከበር፣ የገበያ መሠረተ ልማቱን በማስፋፋት፣ የግብይት ስርዓቱን በማዘመንና ሰንሰለቱን በማሳጠር፣ የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት እና የኤክስፖርት ግብይትን ማሳደግ ይገባል ብለዋል፣ በዚህም
ከንግድ ፈቃድ አገልግሎቶች አኳያ:-
አዲስ ምዝገባ ማድረግ፡- ዕቅድ 7,000 ክንዉን 4695 አፈፃፀም ከአመቱ 67.07%፣
አዲስ ፈቃድ መስጠት፡- ዕቅድ 9,000 ክንዉን 6323 አፈፃፀም ከአመቱ 70.26%፣
ፈቃድ እድሳት፡- ዕቅድ 13,746 ክንዉን 11111 አፈፃፀም ከአመቱ 80.83% ማከናወን የተቻለ ሲሆን
19,407 ድርጅቶች ላይ የአስተያየት መስጫ ደብተር በማስቀመጥ ነጋዴዎች የንግድ ሪፎርሙን እንዲያሟሉ የድጋፍና የክትትል ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
19407 ድርጅቶችን በመጎብኘት የንግድ ህግ የሚጥሱትንና ሸማቹን የሚጐዱትን የንግዱን ማህበረሰብ ከህገ-ወጥ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ እየተሰራ ይገኛል፣በዚህም 1437 ጉድለቶች ተገኝተው 1430ቱን እንዲስተካከሉ የተደረገ ሲሆን፣638 የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት፣792 ደግሞ በማሸግ፣እንዲሁም 2 እገዳና 7 በፍርድቤት ክስ በመመስረት እዲስተካከሉ ተደርጓል፡፡
በህገ ወጥ መንገድ የተያዘ መሠረታዊ ምርት
 በህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር የህጋዊ ነጋዴዉ ተባባሪነትና በአካል በመጠቆምና በመታገል እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም 1305 ድርጅቶች ካለ ፍቃድ ሲነግዱ ተገኝተው 1295ቱ አዲስ ፍቃድ እንዲያወጡ ተደርጓል፣
 እንዲሁም መሰረታዊ ምርት - ስኳር 6.5 ኩ/ል፣ነዳጅ 6327 ሊትር፣ 180.5 ኩ/ል የአፈር ማዳበሪያ፣100 ቀረጢት ከሰል፣52 ኩ/ል በቆሎ፣151 የጎዳና ላይ ነጋዴዎችን ከጎዳና ላይ በማስነሳት ህጋዊ ሆነው እዲሰሩ በማድረግ፣18 ኩ/ል በርበሬና 50 ኪ/ግ ዱቄት፣ 280 ኪ/ግራም ማር በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ ተገኝቶ ምርቱ ተይዞ በሞዴል 85 ወደ መንግስት ካዘና እንዲገባና ሌሎች ምርመራ ላይ ያለ መሆኑ፣
 13,767 ድርጅቶች ደረሰኝ እንዲሰጡና 18984 ድርጅቶች ላይ የዋጋ ዝርዝር እንዲለጥፍ በማድረግ እየተሰራ ይገኛል፣
 ጊዜ ያለፈባቸውንና መገለጫ የሌላቸውን ምርቶች በድርጅቶች ክትትል በማድረግና በማስወገድ የሸማቹን ጤንነትና ደህንነት መጠበቅ፣
 11,593 ድርጅቶች የተሟላ የንግድ እቃ መግለጫ እንዲኖራቸዉ በማድረግ እና 11,593 የአገልግሎት ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶች መከታተልና ማስወገድ ስራ በእቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል፣
 በዋጋ ሲተመን 201123 ብር የሚያወጣ ምርት 1,070.4 ኪ/ግ በጠጣር እና 562 ሊትር በፈሳሽ የመጠቀሚያ ጊዜዉ ያለፈበት ምርት ተይዞ በቴክኒክ ኮሚቴ አማካኝነት እንዲወገድ ተደርጓል፡፡
የመሰረታዊ ምርት አቅርቦትና ስርጭት፡-
ስኳር አቅርቦትና ስርጭት፡- የቀረበ 4,000 የተሰራጨ 4,000 አፈጻጸም እስከዚህ 100%፣
ምግብ ዘይት ስርጭት፡- የቀረበ 200,000 የተሰራጨ 200,000 አፈጻጸም እስከዚህ 100%፣
380279 ኩ/ል የሃገር ዉስጥ የሰብል ምርት ግብይት ትስስር መፈፀም ተችሏል፡፡
118552 ኩ/ል የስንዴና በቆሎ ተኪ የግብርና ምርት ማቅረብ ተችሏል፣
በግብርና ምርት (በሰብል፣አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በእንስትና እንስሳት ተዋፅኦ) እና በፍጆታ የኢንዲስትሪ ምርቶች ተሰማርተው የሚገኙ ደላላዎችን 100% ከገበያ ማስወጣት፣
በህገ ወጥ መንገድ ተከፍተው የሚገኙ ኬላዎችን 100% በማስወገድ ያልተገቡ ክፍያዎችን/ ቀረጦችን በማስቀረት የምርት ዝውውር ቀልጣፋ እንዲሆን እና ሸማቹ ለኑሮ ውድነት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ማድረግ ከዚህ ተግባር አኳያ መምሪያዉ ለሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳድሮች እንዲሁም ለሚመለከታቸዉ አካላት ኬላዉ እንዲነሳ ደብዳቤ ተጽፎ በማዉረድ ሁሉም ኬላዎች እንዲነሱ ተድርጓል፡፡
2ኛ ደረጃ አምራችና ሸማችን የሚያገናኝ ገበያ ማዕከላት ለመገንባት ቦታ የመለየትና የርክክብ ስራ ተፈፅሟል፣ካርታና ፕላን ተሰርቶ የፀደቀ ሲሆን በጀት ተመድቦለት የተቋራጭ ልየታ ተሰርቶ ዉል ተይዞ ስራዉ ተጀምሯል፡፡

ነባር ገበያ ማዕከላት በማሻሻል በመጠገን፣አዲስ ልዩ (እሁድ) ገበያ ማዕከላት ማቋቋም፣ ነባር የእሁድ ገበያ ማዕከልን ወደ ስራ ማስገባት ተችሏል፡፡
የግብይት ትስስሩን በማጠናከርና የፋይናንስ አቅርቦቱን በማሳደግ ገበያውን ማረጋጋት፣
62,199,950 ብር ለገበያ ማረጋጋት የሚዉል ተዘዋዋሪ ብድር ማስመደብ የተለያዩ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በማቅረብ ገበያ የማረጋጋት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
በዚህም የቀረበ ምርት
36,848 ኩ/ል የግብርና ምርት፣ 19,478 ኩ/ል ኢንዱስትሪ ምርት በጠጣር፣666,966 ሊ/ር የኢንዱስትሪ ምርት በፈሳሽ ማቅረብ ገበያዉን የማረጋጋት ስራ ተሰርቷል፡፡
የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽዖ ምርቶች በትስስር ከማገበያየት አኳያ
የአሳ ምርት 19.66 ቶን፣105,853 የቁም እንስሳት በመሸኛ ተልከዋል፣2.292 ቶን የስጋ ምርት፣3,005,360 ሊትር የወተት ምርት፣ 945.24 ቶን የማር ምርት፣152.19 ቶን የተቀነባበረ የእንስሳት መኖ፣107,320 ዶሮ፣801,997 የእንቁላል ምርት ትስስር ተፈፅሟል፡፡
በሌላ በኩል ለዜጎች የስራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ፡-
በነዳጅ ማደያዎች የሥራ ለ20 ሰዎች፣በኤክስፖርት ምርት ዝግጅት ለ21 ሰዎች፣በመሰረተ ልማት ግንባታ ለ55 ሰዎች፣በሽርክና ለ13 ሰዎች፣በአጠቃላይ ለ384 ሰዎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፣ እንዲሁም የሴቶችን፣የወጣቶችን፣የአካል ጉዳተኞችንና የአረጋዊያንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
ያለንግድ ፈቃድ የሚሰሩ ጫት ቤቶችን 100 በመቶ በመዝጋት ህግን ለማስከበር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፣
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቀረበውን የዕቅድና ክንውን ሪፖርት መነሻ በማድረግ ከባለሙያዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። በቀጣይም ያጋጠሙ ችግሮችን በመፍታት የተያዘውን ዕቅድ በስኬት ለማጠናቀቅና ለተገልጋዩ ማህበረሰብ የሚገባውን አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል አቅጣጫ መድረኩ ተጠናቋል።

05/04/2026
የምዕ/ጎጃም ዞን ንግድ እና ገበያ ልማት መምሪያ በምግብ ዘይት ምርት  ላይ የሚታየውን የዋጋ ጭማሬ ለማስተካከል  የዳሞት ሁለገብ የገበሬዎች ህ/ስራ ማህበር ዩኒየንን ኤጀንት  እንዲሆን በማድ...
04/04/2026

የምዕ/ጎጃም ዞን ንግድ እና ገበያ ልማት መምሪያ
በምግብ ዘይት ምርት ላይ የሚታየውን የዋጋ ጭማሬ ለማስተካከል የዳሞት ሁለገብ የገበሬዎች ህ/ስራ ማህበር ዩኒየንን ኤጀንት እንዲሆን በማድረግ ከፊቨላ የዘይት ምርት በማቅረብ በከተሞች እና በወረዳዎች ገበያ የማረጋጋት ስራ እየሰራ መሆኑን መምሪያው ገልጿል ።
በቀጣይም መምሪያችን በትኩረት ምርት በማቅረብ የገበያ ማረጋጋት ስራ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ገልፂል።

02/04/2026

ይህ የአብክመ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ እና የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የፌስቡክ ገጽ ነዉ፣
Follow, Like & Share አድርጉ አዳዲስ መረጃዎችን ታገኛላችሁ https://web.facebook.com/profile.php?id=100079907714520&__cft__[0]=AZZitgyzmDEkkuQfwrakXUuVC0NjSYQizY8TYkd0QcBmFrokaF5Bh2920SJzwmxzhvNvc3qXOHoM31WWqzUxBwxf5uSD3-ZE5kUhCJqQsl2IemAW8BhzuvY373IeELLqTmhqv1slXBG2XdQ521eLrVq4StH7DAvcu33zCqMFovb54QL3pmTaZm76oCqD0-1zyBg&__tn__=-UK-R
https://www.facebook.com/share/1Dy5MDsfwh/

በህግና ስርአት የሚመራ የዘመነ ንግድና ግብይት ተፈጥሮ ማየት

በጅጋ ከተማ አስተዳድር ከ60 ኩንታል በላይ የምግብ ጨው በህገወጥ መንገድ በማከማቸት በተጋነነ ዋጋ ሲሸጥ የተገኘ ግለሰብ የ2 ዓመት እስራት እና የገንዘብ ቅጣት ተወሰነበት።ግለሰቡ ምንም አይ...
01/04/2026

በጅጋ ከተማ አስተዳድር ከ60 ኩንታል በላይ የምግብ ጨው በህገወጥ መንገድ በማከማቸት በተጋነነ ዋጋ ሲሸጥ የተገኘ ግለሰብ የ2 ዓመት እስራት እና የገንዘብ ቅጣት ተወሰነበት።

ግለሰቡ ምንም አይነት የንግድ ፈቃድ ሳይኖረው 60 ነጥብ 5 ኩንታል የምግብ ጨው በማከማቸት የገበያ እጥረት በመፍጠር በህዝብ ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ሲያደርግ እንደነበር ተገልጿል።

የጅጋ ከተማ ፖሊስ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሰረት ግለሰቡ ያከማቸውን ጨው በአይሱዙ ተሽከርካሪ ጭኖ ሊሸሽ ሲል መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በከተማው 01 ቀበሌ ደንበጫ በር አካባቢ በቁጥጥር ስር አውሎታል።

ፖሊስ የሰበሰበውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማጠናቀቅ ጉዳዩን ለአቃቤ ህግ አስተላልፎ በተፋጠነ የክስ ሂደት እንዲታይ ተደርጓል።

ጉዳዩን የመረመረው የጅጋ ንዑስ ፍርድ ቤት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹ የቀረበበትን ማስረጃ መቃወም ባለመቻሉ ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ የሁለት ዓመት እስራትና የ10 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ በኤግዚቢት የተያዘው 60 ነጥብ 5 ኩንታል የምግብ ጨው ሙሉ በሙሉ ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ትዕዛዝ ሰጥቷል።

የጅጋ ከተማ ፖሊስ በህብረተሰቡ የተሰጠውን ጥቆማ እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ምስጋና አቅርቦ፣ ከህገ-ወጥ ንግድ ተግባራት ጋር በተያያዘ የሚደርሱ ጥቆማዎች እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል።

01/04/2026

መንግሥት በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትና ዓለም አቀፍ ቀውስ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቋቋም የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 ፦ መንግሥት በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነትና ዓለም አቀፍ ቀውስ ምክንያት በነዳጅ አቅርቦት ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቋቋም የሚያስችሉ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በመካካለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና አለመረጋጋት በሀገራችን የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተጽዕኖ እንዲሁም መንግሥት የሚከተላቸውን አቅጣጫዎች በተመለከተ ለኢዜአ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን የሚከታተል፣ እርምጃ የሚወስድና የነዳጅ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ዘርፍች የሚለይ ልዩ ክፍል መቋቋሙንም ይፋ አድርገዋል።

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና አለመረጋጋት በሀገራችን የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ተናግረዋል።

በጦርነቱ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከጦርነቱ በፊት የአንድ በርሜል ነጭ ናፍጣ ዋጋ 80 ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን 230 ዶላር መድረሱን ቤንዚንም ከ70 ወደ 150 ዶላር ማሻቀቡን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ጋር የነበራት የረጅም ጊዜ የነዳጅ ግብይት ውል በጦርነቱ ምክንያት መስተጓጎሉንና አቅራቢ ሀገራቱ ምርቱን ማቅረብ እንደማይችሉ ማሳወቃቸውን አስታውሰዋል።

በዚህም ምክንያት በግዥ ሂደት ላይ የነበረ ከ180 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ነዳጅ አለመቅረቡን ጠቅሰዋል።

በጦርነቱና አለመረጋጋቱ ምክንያትም በነጭ ናፍጣ ላይ የነበረው የቀን አቅርቦት ከ9 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሊትር ወደ 4 ነጥብብ 5 ሚሊዮን ሊትር ዝቅ ማለቱን ጠቁመዋል።

የተለያዩ ሀገራት ያጋጠማቸውን የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ተከትሎ የተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እቀባዎችን እያደረጉ መሆኑን ገልጸው፥ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚከተለው መርህ ግን ከህዝቡ ጋር በመተባበር ችግሩን በጋራ ለመሻገር መሆኑን ጠቅሰዋል።

መንግሥት የተፈጠረውን የአቅርቦት እጥረት ለመቅረፍና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እንዳይገቱ ነዳጅን ከተጓዳኝ ገበያ ስለሚገዛና የዓለም የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ ምክንያት በሦስት እጥፍ ዋጋ እየገዛ ለማቅረብ መገደዱን ሚኒስትሩ አስረድተዋል።

ምንም እንኳን የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቢጨምርም፣ መንግሥት የዜጎችን ኑሮ ለመታደግ በአሁኑ ወቅት በነጭ ናፍጣ ላይ በአንድ ሊትር 95 ብር፣ በቤንዚን ላይ ደግሞ 42 ብር ድጎማ እያደረገ ይገኛል ነው ያሉት።

እስካሁን 262 ቢሊዮን ብር ገደማ ድጎማ ማድረጉን በማንሳት የተደረገ ሲሆን፣ በየወሩም ከ15 እስከ 20 ቢሊዮን ብር ለድጎማ እየተመደበ መሆኑ ጠቅሰዋል።

ያጋጠመው የነዳጅ አቅርቦት እጥረት በሀገርና በዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ጫና እንዳያሳድርና በፍትሐዊነት ለመምራት መንግሥት ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የቅድሚያ አሰጣጥ ውሳኔ ማሳለፉን ሚኒስትሩ ይፋ አድርገዋል።

በዚህም መሠረት

1. ነዳጅ የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች በማደያ የቅድሚያ ቅድሚያ እንዲሰጣቸው

2. ከፍተኛ አምራችና የኤክስፖርት ድርጅቶች በቀጥታ ፣

3. ልዩ ትኩረት የሚሹ የመንግሥትና የግል ፕሮጀክቶች በቀጥታ፣

4. የገቢና ወጪ ንግድን ጨምሮ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች

5. ግብርናን የሚያዘምኑ ትራክተሮች፣

6. የከተማና ሀገር አቀፍ የብዙሃን ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች

7. እንዲሁም በናፍጣ የሚሰሩ የሕዝብ ማ

Address

Finote Selam
Finote Selam

Telephone

+251587751952

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share