Gog woreda administrative council የጎግ ወረዳ አሰተዳደር ምክር ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Gambela
  • Gog woreda administrative council የጎግ ወረዳ አሰተዳደር ምክር ቤት

Gog woreda administrative council  የጎግ ወረዳ አሰተዳደር ምክር  ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gog woreda administrative council የጎግ ወረዳ አሰተዳደር ምክር ቤት, Government Official, Gambela.

23/06/2025

የመኸር እርሻ ሥራ - የነገው የአዲስ ቀን የሀገር ጉዳይ ነው
**************

መኸር የተፈጥሮ ዝናብን በመጠቀም በኢትዮጵያ ብዙ ሰብል የሚሰበሰብበት የምርት ወቅት ነው። በዚህ ወቅት በቂ ግብዓት ከቀረበና ድጋፍ ከተደረገ ዓመታዊ የተትረፈረፈ ምርት ስለመገኘቱ ዋስትና ይስጣል።

አዲስ ቀን የዜና መሰናዶ የሀገር ጉዳይም “የዚህ ዓመት የመኸር እርሻ ሥራ ያለበት ሁኔታ ምን ይመስላል?” ሲል ይጠይቃል።

አርሶ አደሩ ለመኸር እርሻው የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ቀርበውለት እንደሆነም በአዲስ ቀን ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ ይሰጥበታል።

በመኸር እርሻ ወቅት በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት ለአርሶ አደሩ ብሎም ለሰብል ልማቱ ያላቸውን ፋይዳ በተመለከተ ማብራሪያ በአዲስ ቀን የሀገር ጉዳይ ይቀርብበታል።

የዚህ ዓመት የመኸር እርሻ ሥራ ምን ያህል ለግብርናው የተመቸ እንደሆነም አዲስ ቀን የሚመለከታቸውን አካላት ስቱዲዮ ጋብዞ ይጠይቃል።

አዲስ ቀን ይህን የሀገር ጉዳይ እና ሌሎች ጥንቅሮችን አካቶ ነገ ጧት ከ1:00 እስከ 3:00 ከአብዮት ይግዛውና ከመቅደላዊት ደረጀ ጋር ይጠብቃችኋል።

አዲስ ቀን!

23/06/2025
በጎግ ወረዳ የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና መስጠት ተጀመረ።********************‎‎ከጎግ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (ሰኔ 3/2017 ዓ.ም)‎‎በጎግ ወ...
10/06/2025

በጎግ ወረዳ የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና መስጠት ተጀመረ።********************

‎ከጎግ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት (ሰኔ 3/2017 ዓ.ም)

‎በጎግ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየተሰጠ መሆኑን የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኡሞድ ኡጉታ አስታወቀ።

‎ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚሰጠው የ8ኛ ክፍለ ማጠናቀቂያ ክልላዊ ፈተና በዘንድሮ 2017 ዓ/ም የት/ት ዘመን ለመማር ከተመዘገቡ ተማሪዎች በመደበኛ ተማሪዎች በመፈተን ላይ እንደሚገኙ በፈተና ላይ የተቀመጠው ፦መደበኛ ተማሪዎች ወ_477 ሴ_508 ድ_985
‎የግል ተፈታኞች ወ_65 ሴ_60 ድ_125 መሆናቸውን ይታወቃል ።
‎በአጠቃላይ በፈተናው ላይ የተቀመጡ 1110 ወ_542 ሴ_568 ተማሪዎች በመፈተን ላይ ይገኛሉ ።ጽ/ቤት ኃላፊው ገልጿል።

‎ በ19ቱ የፈተና መስጫ ጣቢያዎች በሚሰጠው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን የክትትል ሥራ እየተደረገ መሆኑን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ጨምሮ ገልጸዋል።

ሰኔ 2/2017 ዓ/ም ከአኙ/ብሔ/ዞን የመጡ የፑብ/ሠር/ሰ/ሀ/ል/መምሪያ ኃላፊና ባለሙያ በተዘጋጀ የ4ኛ ሩብ ዓመት ቼክ ሊት እና የ9 ወራት ሪፖርት ግብረ መልሰ የተገኙ ማሰተካኪያዎች ለማድረ...
09/06/2025

ሰኔ 2/2017 ዓ/ም ከአኙ/ብሔ/ዞን የመጡ የፑብ/ሠር/ሰ/ሀ/ል/መምሪያ ኃላፊና ባለሙያ በተዘጋጀ የ4ኛ ሩብ ዓመት ቼክ ሊት እና የ9 ወራት ሪፖርት ግብረ መልሰ የተገኙ ማሰተካኪያዎች ለማድረግ ከወረዳ አጠቃላይ የሴ/መ/ቤቶች ሰው ሀብት ልማት ሥራ ሂደት ጋር የወይይት መድረክ ተካሄዷል።

ከጎግ ወረዳ መንግሰት ኮሙኒኬሽን ጉ/ጽ/ቤት

በጋምቤላ ክልል በየጊዜው በሚፈጠሩ ግጭቶች ህብረተሰቡ የሚገባውን ያህል ተጠቃሚ ሳይሆን መቆየቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ከአኙዋ ዞን ነ...
03/09/2024

በጋምቤላ ክልል በየጊዜው በሚፈጠሩ ግጭቶች ህብረተሰቡ የሚገባውን ያህል ተጠቃሚ ሳይሆን መቆየቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።

የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ከአኙዋ ዞን ነዋሪዎች ጋር በፒኝውዶ ከተማ የትውውቅና የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

ከጎግ ወረዳ አሰተዳደር ምክር ቤት (ነሐሴ 28/ 2016 ዓ.ም)

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ እንዳሉት ጋምቤላ በተፈጥሮ ሀብቷ የታደለች ብትሆንም በየጊዜው በሚፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የሀብቷን ያህል ተጠቃሚ አልሆነችም ብለዋል።

በመሆኑም አሁን ላይ በተጀመረው አዲስ የለውጥ ምዕራፍ ያመለጡንን ወርቃማ ዕድሎች በቁጭትና በላቀ ትጋት የህዝቡን የሠላምና የልማት ጥያቄ መመለስ የሚያስችል አመራር ለውጥ መደረጉን ገልፀዋል።

በቀጣይ ለህዝብ የሚሰራ የህዝብ ልጅ የሆነ አመራር እየገነባን በስራው ለህዝብ ባመጣው ውጤት የሚመዘን አገልጋይ አመራር ለመፍጠር እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ጋትሉዋክ ሮን በበኩላቸው በክልሉ ዘላቂ ሰላም በማምጣት የህዝቡን የእርስ በርስ ግንኙነት ለማጠናከር መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ተፈጥሮ የነበረው የፀጥታ ችግር በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ በመወገዱ ህብረተሰቡ የዕለት ተዕለት ተግባራቱን ያለምንም ስጋት እያከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በክልሉ አስተማማኝና ዘላቂ ሠላም ለማረጋገጥ እየተደረገ ላለው ሁሉን አቀፍ ጥረት ህብረተሰቡ የሚጠበቅባቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የጋምቤላ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ለዘመናት ጸንቶ የቆየውን የአንድነት እሴቶቻቸውን እንዳይሸረሽሩ ህብረተሰቡ በጋራ መስራት ይኖርበታል ብለዋል።

የአኙዋ ዞን ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ለዞኑ ብሎም ለክልሉ ዘላቂ ሰላም መስፈን በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

ባለፉት ጊዜያት በክልሉ ተከስቶ በነበረው የሰላም መደፍረስ ምክንያት ለበርካታ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋልጠው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

በአሁኑ ሰዓት የአመራር ለውጥ መደረጉን ተከትሎ ያለው ሰላም መሻሻል እንደሚታይበት ጠቁመው ህብረተሰቡ የዕለት ተዕለት ተግባራቱን ማከናወን መጀመሩን ገልፀዋል።

ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በአኙዋ ዞን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያዩአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በአኙዋ ዞን ...
03/09/2024

ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በአኙዋ ዞን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በአኙዋ ዞን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በፒኝውዶ ከተማ የትውውቅና የውይይት መድረክ አካሄዱ።

ውይይቱ በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማምጣት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ውይይቱን ርዕሰ መስተዳድሯ አለሚቱ ኡሞድ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) እና በብልፅግና ፓርቲ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሽኔ አስቲን መርተውታል።

ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ እንደገለጹት፤ በየጊዜው በሚፈጠሩ ግጭቶች ህብረተሰቡ የሚገባውን ያህል ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል።

ጋምቤላ በተፈጥሮ ሀብቷ የታደለች ብትሆንም በየጊዜው በሚፈጠሩ ችግሮች ተጠቃሚ አልሆነችም ብለዋል።

በመሆኑም ያመለጡንን ወርቃማ ዕድሎች በቁጭትና በላቀ ትጋት የህዝቡን የሠላምና የልማት ጥያቄ መመለስ የሚያስችል ለውጥ ተደርጓል ሲሉ ገልፀዋል።

ባመጣው ውጤት የሚመዘን አገልጋይ አመራር ለመፍጠር እንደሚሰራም ተናግረዋል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የህዝቡን የእርስ በርስ ግንኙነት ለማጠናከር መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

በክልሉ ተፈጥሮ የነበረው የፀጥታ ችግር በመወገዱ ህብረተሰቡ የዕለት ተዕለት ተግባራቱን ያለምንም ስጋት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ በክልሉ ዘላቂ ሠላም ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ህብረተሰቡ መደገፍ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

አመራሮቹ ከዚህ ቀደም ጋምቤላ ከተማን ጨምሮ በኢታንግ ከተማ፣ ኝግኛንግ ከተማና በሜጢ ከተማ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ዘላቂ ሰላም ማምጣት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ማድረጋቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

Address

Gambela

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gog woreda administrative council የጎግ ወረዳ አሰተዳደር ምክር ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share