Gambella Police Commission

Gambella Police Commission በጀግንነት መጠበቅ፣ በሰብዓዊነት ማገልገል!

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በንቃት ተሳተፈ​በጋምቤላ ክልል በጋምቤላ ወረዳ ቃርሚ ቀበሌ ዛሬ በተካሄደው ክልል አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተ...
03/08/2026

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በንቃት ተሳተፈ

​በጋምቤላ ክልል በጋምቤላ ወረዳ ቃርሚ ቀበሌ ዛሬ በተካሄደው ክልል አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራር እና አባላት በንቃት በመሳተፍ የድርሻቸውን ተወጥተዋል።

​የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ እና ምክትል ኮሚሽነር ክቡር አቶ ቾት ኒት ፓል የተመሩት የፖሊስ አባላት በሥፍራው በመገኘት ችግኞችን ተክለዋል።

​በዚህ ወቅትም ምክትል ኮሚሽነሩ ለአመራሩና ለአባላቱ ባስተላለፉት መልእክት፤ መርሐ ግብሩ የደን ሽፋንን ከማሳደግ እና የአየር ንብረት ለውጥን ከመቋቋም ባሻገር የአፈር ለምነትን በመጠበቅ የአካባቢ ጥበቃን ለማጠናከር እና ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ አረንጓዴ አካባቢን ለማስተላለፍ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል።

​በመርሐ ግብሩ ላይ የተሳተፉ የፖሊስ አመራር እና አባላት በበኩላቸው፣ የችግኝ ተከላ ሥራው ችግኞችን በመትከል ብቻ የሚጠናቀቅ ሳይሆን በቀጣይነት በመንከባከብ እና በማጽናት ሂደት ውስጥም የድርሻቸውን ንቁ ተሳትፎ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የ12 ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ጀመረየጋምቤላ ክልል ምክር ቤት የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች በ2018 በጀት ዓመት ...
01/08/2026

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የ12 ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ጀመረ

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት 12 ወራት ያከናወኑትን የስራ አፈጻጸም የሚገመግም መድረክ ዛሬ ተጀምሯል።

ለሁለት ቀናት የሚቆየው ይህ ግምገማ፣ በበጀት ዓመቱ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች የተከናወኑ ስራዎችን በዝርዝር በመመልከት የተገኙ ስኬቶችን፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን እና የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን ለመለየት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይም በክልሉ የሰላምና የፀጥታ ሁኔታን በማጠናከር ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችና የታዩ ክፍተቶችን በጥልቀት የሚገመገሙ ሲሆን፣ ቋሚ ኮሚቴውም በቀጣይ ጊዜ ትኩረት የሚሰጣቸውን የስራ አቅጣጫዎች እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል።

እንዲሁም ግምገማው የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ የታዩ ድክመቶች በአግባቡ እንዲታረሙ እና ለቀጣዩ የስራ ዘመን ግልጽ የልማት አቅጣጫዎች እንዲቀመጡ ወሳኝ መድረክ መሆኑ ተጠቁሟል።

በግምገማው ላይ የክልሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ኃላፊዎች፣ የቋሚ ኮሚቴ አባላትና ሰብሳቢዎች፣ እንዲሁም የስራ ሂደት፣ የመረጃና የዕቅድ ባለሙያዎች ተገኝተው በየዘርፉ የቀረቡ አፈጻጸሞችን በመገምገም ላይ ይገኛሉ።

የሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር አሠራር ግልፅ፣ ተገማችና ውጤታማ እንዲሆን ተጨማሪ የአሠራር ማሻሻያዎች እንደሚያስፈልጉ ጥናት አመለከተአዲስ አበባ --  የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ...
01/08/2026

የሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር አሠራር ግልፅ፣ ተገማችና ውጤታማ እንዲሆን ተጨማሪ የአሠራር ማሻሻያዎች እንደሚያስፈልጉ ጥናት አመለከተ

አዲስ አበባ -- የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ያካሄደው 2ኛ ዙር የሙስና ወንጀል ህግ የማስከበር የአሰራር ሥርዓት ግልጽነት ጥናት የሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር አሠራር ግልፅ፣ ተገማችና ውጤታማ እንዲሆን ተጨማሪ የአሠራር ማሻሻያዎች እንደሚያስፈልጉ አመላክቷል።

በፌዴራል ደረጃ የተካሄደ የሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር አሠራር ሥርዓት ግልፅነት ዳሰሳ ጥናት፣ ከሙስና ወንጀል ጥቆማ ቅበላ፣ ምርመራ፣ ክስና ክርክር፣ የፍርድ ሂደት እንዲሁም ከንብረት ማስመለስ ሂደቶች አንፃር ግልፅነትን ለማጠናከር የተደረጉ አበረታች መሻሻሎች መኖራቸውን አመልክቷል።

ሆኖም፣ የሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር አሠራር የበለጠ ግልፅ፣ ተጠያቂነት ያለው፣ ተገማችና ውጤታማ እንዲሆን ቀጣይነት ያለው የአሠራር ማሻሻያ ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግ ጥናቱ አሳይቷል።

ጥናቱ እንደሚያመለክተው፣ በሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር ሂደት ውስጥ የሚሳተፉ ተቋማት በጋራ የመሥራት አቅማቸው መሻሻሉ የተመዘገበ ቢሆንም፣ በመረጃ ልውውጥና በውሳኔ አፈጻጸም ላይ የሚስተዋሉ መዘግየቶች የምርመራ፣ የክስ አቀራረብና የፍርድ ሂደቶችን በአሉታዊ ሁኔታ እየጎዱ መሆናቸውን ጠቁሟል።

በዜጎች የሙስና ወንጀል ጥቆማ አቀራረብ ረገድ፣ በኢትዮጵያ የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የተዘረጋው National Corruption Reporting System (NCRS) እና በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የተዘረጋው Ethiopian Federal Police Citizens Engagement Application (EFPApp) ዜጎች ጥቆማቸውን በቀላሉ እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠራቸውም በላይ፣ የሙስና መረጃ ብክነትን በመቀነስ አስፈላጊ አስተዋጽኦ እያደረጉ መሆኑን ጥናቱ አረጋግጧል።

ሆኖም፣ በአንዳንድ ተቋማት አሁንም በወረቀት ላይ የተመሠረተ ወይም በዲጂታል ሥርዓት ያልተደገፈ የጥቆማ አቀባበል መኖሩ የመረጃ ብክነትን በመጨመር የጥቆማ ሥርዓቱን ውጤታማነት እንደሚቀንስ ተገልጿል።

በምርመራ ሂደት፣ የማስረጃ አሰባሰብ ውስንነት፣ የዲጂታልና የፎረንሲክ ምርመራ አቅም ውስንነት እንዲሁም የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት የሙስና ወንጀል ምርመራዎችን ውጤታማነት እየጎዱ መሆናቸውን ጥናቱ አመልክቷል።

በዚህ ምክንያትም ከአቃቤ ህግ ወደ ፖሊስ ለተጨማሪ ምርመራ የሚመለሱ የሙስና ወንጀል መዝገቦች አሁንም መኖራቸውን ጥናቱ አሳይቷል። በተጨማሪም፣ የጠቋሚዎችና የምስክሮች ጥበቃ ሥርዓት ከሚጠበቀው ደረጃ በታች መሆኑ ተገልጿል።

በተለይም የህግ ከለላና የጥበቃ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ አለማግኘታቸው፣ በተቋማት መካከል ያለው የቅንጅት ውስንነት እና ግልጽና ውጤታማ የክትትል ሥርዓት አለመጠናከሩ ከዋና ተግዳሮቶች መካከል መሆናቸውን ጥናቱ ጠቁሟል።

በክስና በፍርድ ሂደትም የማስረጃ ዝግጅት፣ የክስ አመራር ጥራት እና የሰነዶች አያያዝ ላይ የሚስተዋሉ ጉድለቶች የሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር ሂደቱን እንዲዘገይ እና የፍርድ ውሳኔዎችን ጥራት እንዲቀንሱ እያደረጉ መሆናቸው ተመልክቷል።

በአጠቃላይ፣ ጥናቱ በሙስና ወንጀል ህግ ማስከበር አሠራር ውስጥ የዲጂታል መረጃ አስተዳደር መሻሻሉን፣ የዜጎች የሙስና ማጋለጥ ተሳትፎ መጨመሩን እና በህግ ማስከበር ሰንሰለት ውስጥ የሚሳተፉ ተቋማት መካከል ያለው ቅንጅት መሻሻሉን እንደ አበረታች ውጤቶች ቢያሳይም፣ የተቋማት ቅንጅትን የበለጠ ማጠናከር፣ የምርመራ አቅምን ማሳደግ፣ የጠቋሚዎችና የምስክሮች ጥበቃ አገልግሎትን ማሻሻል፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማስፋት እና በሙስና ወንጀል የተመዘበረ ንብረትን በውጤታማ ሁኔታ የማስመለስ አቅምን ማጠናከር ለቀጣይ የማሻሻያ ሥራዎች ቅድሚያ ሊሰጣቸው እንደሚገባ ያመለክታል።

ምንጭ፦ ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም

የጋምቤላ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በተገኙ ግለሰቦች ላይ የጽኑ እስራት ቅጣት አስተላለፈ​ጋምቤላ - ​የጋምቤላ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፈጣን ወንጀል ምድብ ...
31/07/2026

የጋምቤላ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በተገኙ ግለሰቦች ላይ የጽኑ እስራት ቅጣት አስተላለፈ

​ጋምቤላ - ​የጋምቤላ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፈጣን ወንጀል ምድብ ችሎት፣ ህገወጥ የጥቅማጥቅም ፍላጎትን መሰረት አድርገው በፈጸሙት የስርቆት ወንጀል ጥፋተኛ የተገኙ ግለሰቦች ላይ የጽኑ እስራት ቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ።

​በወንጀል ድርጊቱ ተሳትፈዋል ተብለው ጥፋተኛ ተብለው የተወሰነባቸው ግለሰቦች፡- ​፩ኛ. አቶ ጉታ ተስፋዬ ገመዳ (ዕድሜ 30፣ የ05 ቀበሌ ነዋሪ) ​፪ኛ. ወጣት ገመቹ አበበ ደበላ (ዕድሜ 23፣ የ05 ቀበሌ ነዋሪ) ​ተከሳሾቹ ሆን ብለው የማይገባቸውን ብልጽግና ለማግኘት በማሰብ በጋምቤላ ከተማ 05 ቀበሌ ልዩ ስሙ "ዞን 10" በሚባለው አካባቢ የሚገኘውን የግል ተበዳይ አቶ አብዱራኪም ዘይኑ መሐመድን መኖሪያ ቤት ሰብረው በመግባት ወንጀሉን ፈጸመዋል።

​ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 9፡00 ሰዓት አካባቢ በፈጸሙት የዚህ የስርቆት ድርጊት የተወሰዱ ንብረቶች ዝርዝር፡- ​አንድ አልትራ ኤስ 23 (Ultra S 23) ሳምሰንግ ሞባይል (ግምቱ 150,000 ብር)፣ ​አንድ ኤ 17 (A 17) ሳምሰንግ ሞባይል (ግምቱ 40,000 ብር)፣ ​ሶስት ጥንድ ጫማዎች (ግምታቸው 20,000 ብር)
​በአጠቃላይ 210,000 (ሁለት መቶ አስር ሺህ) ብር የሚያወጡ ንብረቶችን ሰርቀው ለማምለጥ ሲሞክሩ በጸጥታ አካላት እጅ ከፈንጅ መያዛቸው በክስ መዝገቡ ሰፍሯል።

​ተከሳሾቹ በ1997 ዓ.ም ተሻሽሎ የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32፣ 37 እና 669(3) "ለ" ስር የተመለከቱትን ህጋዊ ድንጋጌዎች በመተላለፍ የቀረበባቸውን ክስ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን የሰው እና የሰነድ (ኤግዚብት) ማስረጃዎች መርምሮ ጥፋተኛ ብሏቸዋል።

​በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾችን አርሞ ለአገር አርአያ በማድረግ እና ህብረተሰቡን ከወንጀል በመከላከል ረገድ አስተማሪ ይሆናል ያላቸውን ውሳኔ በመወሰን፣ ** ለእያንዳንዳቸው 6 (ስድስት) ዓመት ከአራት (4) ወራት በጽኑ እስራት** እንዲቀጡ ወስኗል።

​ማንም አካል ወንጀል ፈጽሞ ከህግ ቁጥጥር ማምለጥ እንደማይችል የገለጸው የፍትህ አካሉ፣ ህብረተሰቡም ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ህገወጥ ድርጊቶች ከመፈጸም አበክሮ ሊቆጠብ ይገባል ብሏል። በሌላ በኩል ጉዳቱ የደረሰባቸው ባለቤቶች የተሰረቁባቸው ንብረቶች ሙሉ በሙሉ ተመላሽ መደረጋቸውን ከፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖልና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በቁጥጥር ሥር አዋለአዲስ አበባ -- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከ...
30/07/2026

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖልና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በቁጥጥር ሥር አዋለ

አዲስ አበባ -- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል እና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር በበርካታ የሀገራችን ወጣቶች ላይ ከባድ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም የቆየውን አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በማላዊ ሀገር በቁጥጥር ሥር እንዲውል በማድረግ በሕግ ተጠያቂ እንዲሆን ወደ ሀገራችን እንዲመጣ አድርጓል።

አድነው ባሻው ውዳሞ በቁጥጥር ሥር ሊውል የቻለው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተለይም ከሀድያ እና ከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን ሕይወት እንደሚያሻሽል በመሐላና በአጉል ተስፋ በማታለል በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያዘዋውር መቆየቱን ፖሊስ በሰውና በሰነድ ማስረጃ አረጋግጧል።

ተጠርጣሪው ከእያንዳንዱ ተጓዥ ከ600 ሺህ እስከ 800 ሺህ ብር የሚጠይቅ ሲሆን፤ በቅድመ ክፍያ ኢትዮጵያ ውስጥ 100 ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ ሲቀበል መቆየቱንም የምርመራ መዝገቡ አመላክቷል።

ተጓዦችን በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ በማሻገርም በጋንቦ ጫካ ውስጥ በድብቅ በማስቀመጥ በየ 24 ሰዓት ትንሽ ሩዝ ከቁራጭ ዳቦ ጋር ብቻ በመስጠት፣ በከፍተኛ ረሃብና የውሃ ጥም እንዲሰቃዩ ከማድረጉም በላይ በሞተርና በእግር ሴሎ በረሃን ጭምር እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል ሲል ፖሊስ ገልጿል።

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተጎዦችን በሕገ-ወጥ መንገድ ናይሮቢ ከተማ ካደረሳቸውም በኋላ በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር፣ ተጨማሪ ገንዘብ ከቤተሰቦቻቸው እንዲያስልኩ በማስገደድ ከፍተኛ ግፍ መፈጸሙን ፖሊስ በሰውና በሰነድ ማረጃ ደርሼበታለሁ ብሏል።

ከቤተሰብ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን ተጓዦችን በዱላ በመደብደብና "እዚሁ ትሞታላችሁ" እያለ በማስፈራራት እንዲሁም በኤሌክትሪክ ንዝረት በማሰቃየት ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት በመፈጸም ተጨማሪ አንድ መቶ ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግብረ አበሮቹ በኩል በባንክ እንዲከፈለው አድርጓል ብሏል ፖሊስ።

ከዚህም ባለፈ ተጓዦቹን ከናይሮቢ ወደ ሞምባሳ፣ ከዚያም ወደ ታንዛኒያ በዕቃ መጫኛ ኮንቴነሮች፣ በተሳቢና ከኋላ ክፍት በሆኑና በሸራ በተሸፈኑ መኪኖች ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ተጓዦች በመጫን ታንዛኒያ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ጥሎ በመጥፋት ለአሰቃቂ አደጋ ዳርጓቸዋል ሲል ፖሊስ ገልጿል።

አብዛኞቹ ወጣቶች ደቡብ አፍሪካ ሳይደርሱ በተለያዩ ሀገራት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር በመግባታቸው እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡና እስራቱን ሲጨርሱም እስከ 170 ሺህ ብር ከፍለው ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን የፖሊስ ምርመራ መዝገብ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ባደረገው ከፍተኛ ክትትል በበርካታ የሀገራችን ወጣቶች ላይ ኢሰብዓዊ ድርጊት ሲፈጽምና የኢኮኖሚ ጉዳት ሲያደርስ የቆየውን አድነው ባሻው ውዳሞን የማላዊ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ለኢትዮጵያ አሳልፎ መስጠቱን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሌሎች ሀገራት የፖሊስ ተቋማት ጋር በመተባበር በተመሳሳይ ወንጀል ላይ የተሰማሩትን አድኖ ለሕግ የማቅረብ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል እየገለፀ ኅብረተሰቡ በEFPApp፣ በ991 እና በSPS መረጃ በመስጠት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።

በአኮቦ ወረዳና በደቡብ ሱዳን አኮቦ ካውንቲ መካከል የሰላም ጉባኤ ተካሄደ​አኮቦ — በኑዌር ብሔረሰብ ዞን አኮቦ ወረዳ እና በደቡብ ሱዳን ጁንግሌ ግዛት አኮቦ ካውንቲ እንዲሁም በአፈር ናይል ...
30/07/2026

በአኮቦ ወረዳና በደቡብ ሱዳን አኮቦ ካውንቲ መካከል የሰላም ጉባኤ ተካሄደ

​አኮቦ — በኑዌር ብሔረሰብ ዞን አኮቦ ወረዳ እና በደቡብ ሱዳን ጁንግሌ ግዛት አኮቦ ካውንቲ እንዲሁም በአፈር ናይል ዋምዲንግ መዋቅር መካከል በድንበር ጉዳዮች፣ በሰላምና በደህንነት ዙሪያ ያተኮረ ከፍተኛ የሰላም ጉባኤ ተካሄደ።

​በአኮቦ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት መረጃ መሠረት፣ በጉባኤው ላይ የአኮቦ ወረዳ አመራሮች፣ የ17ቱ ቀበሌዎች ሊቀመንበሮች፣ የደቡብ ሱዳን አኮቦ ካውንቲ እና የዋምዲንግ አመራሮች ተገኝተዋል።

​እንዲሁም የአካባቢ አስተዳደር ባለሥልጣናት፣ የደህንነት አካላት፣ ባህላዊ መሪዎች እና የማህበረሰብ ተወካዮች በመድረኩ ላይ በመሳተፍ በድንበር አካባቢ በሚከሰቱ ችግሮች ላይ ግልጽ ውይይት አድርገዋል። መድረኩ በድንበር አካባቢ የሚኖሩ ማህበረሰቦች በሰላም እንዲኖሩ፣ አለመግባባቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ እና የአካባቢው ትብብር እንዲጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

​በሁለቱ አገራት ድንበር አዋሳኝ የሚኖሩ ህዝቦች መካከል ያለውን ታሪካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ተመላክቷል።

ግጭቶችን አስቀድሞ ለመከላከል፣ ቀልጣፋ የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ እና የችግር መፍቻ የጋራ ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል።

​በድንበር አካባቢ የሚፈጠሩ ማናቸውም አለመግባባቶች በንግግር፣ በመግባባት እና በትብብር ብቻ እንዲፈቱ ጥሪ ቀርቧል።

​የጋራ ትብብር: የሰላምና የደህንነት ትብብርን ማጠናከር ለሁለቱም ወገኖች የጋራ ጥቅም ስላለው በንግድና በማህበራዊ ግንኙነቶች ላይ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተሳታፊዎች አጽንኦት ሰጥተዋል።

​የጉባኤውን መጠናቀቅ አስመልክቶ የአኮቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳይመን ሆስ እንዳስታወቁት፤ ተሳታፊዎች ሰላማዊ አብሮ መኖርን፣ የጋራ መግባባትን እና የድንበር ጉዳዮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ሂደትን ለማጠናከር ከፍተኛ ቁርጠኝነት አሳይተዋል።

​ጉባኤው ሁሉም ወገኖች ግጭትን በመከላከል፣ በመተማመን መንፈስና በቀጣይነት በሚደረጉ ውይይቶች በድንበር አካባቢ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲረጋገጥ ባስተላለፉት የጋራ ጥሪ ተጠናቋል።

የጆር ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ማኔጅመንት አባላት ለአካባቢ ጽዳትና ለአቅመ ድካማ ወገኖች ድጋፍ የሚሆን ውሳኔ አሳለፉኡንጎጊ -- ​የጆር ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ማኔጅመንት አካላት በሁለት ...
30/07/2026

የጆር ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ማኔጅመንት አባላት ለአካባቢ ጽዳትና ለአቅመ ድካማ ወገኖች ድጋፍ የሚሆን ውሳኔ አሳለፉ

ኡንጎጊ -- ​የጆር ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ማኔጅመንት አካላት በሁለት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ በመወያየት አርአያነት ያላቸው ውሳኔዎችን ማስተላለፋቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

​ጽህፈት ቤቱ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መረጃ መሠረት፣ የማኔጅመንት አባላቱ በዋነኛነት የኡንጎጊ ከተማን የግራና ቀኝ መንገድ ቦዮች ከፍታ በማስተካከል ሁለተኛ ዙር የጽዳት ዘመቻ ለማካሄድ እና ለአምስት አቅመ ድካማ ወገኖች የምግብ እና የአልባሳት ድጋፍ ለማድረግ መክረዋል።

​በዚህም መሰረት ለአቅመ ድካማ ወገኖች ለሶስት ተከታታይ ወራት (ከሐምሌ 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 2019 ዓ.ም ድረስ) የሚደረገውን ድጋፍ እውን ለማድረግ በአራት የደመወዝ ስኬል የተከፋፈለ የገንዘብ ማዋጮ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል፦

​ደረጃ 1 (ከ 6,000 እስከ 9,000 ብር ደመወዝ): 200 ብር
​ደረጃ 2 (ከ 10,000 እስከ 14,000 ብር ደመወዝ): 300 ብር
​ደረጃ 3 (ከ 15,000 እስከ 17,000 ብር ደመወዝ): 400 ብር
​ደረጃ 4 (ከ 18,000 ብር በላይ ደመወዝ): 500 ብር

​ይህ የመዋጮ መጠን እና የጽዳት መርሃ ግብር ለጽህፈት ቤቱ አጠቃላይ አባላት በቀን ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ አባላቱ በሙሉ ድምፅ ውሳኔውን አጽድቀውታል።

​የጆር ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ኡጆሆ ሜዶ እንደገለጹት፣ ማኔጅመንቱ እና አባላቱ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ እና አካባቢያቸውን ንጹህ የሚያደርጉ መሰል የክረምት የበጎ አድራጎት ስራዎችን አጠናክረው እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

ከጋምቤላ ከተማ አስተዳደር የተሰጠ መግለጫ የክልሉ ኮማንድ ፖስት በቀን 21/11/2018 ዓ/ም ባካሄደው ስብሰባ በጋምቤላ ከተማን ያለውን ወቅታዊ የሰላም ሁኔታ በመገምገም ውሳኔዎችን አሳልፏል...
29/07/2026

ከጋምቤላ ከተማ አስተዳደር የተሰጠ መግለጫ

የክልሉ ኮማንድ ፖስት በቀን 21/11/2018 ዓ/ም ባካሄደው ስብሰባ በጋምቤላ ከተማን ያለውን ወቅታዊ የሰላም ሁኔታ በመገምገም ውሳኔዎችን አሳልፏል ።

ይህንኑ መሠረት በማድረግ ከተማ አስተዳደሩ እንደሚከተለው መግለጫ አውጥቷል ።

በጋምቤላ ከተማ በተከሰተው የጸጥታ መደፍረስ የሰው ሞትና መፈናቀል ፣ የንብረት መውደምን ጨምሮ በከተማው አለመረጋጋት ተከስቷል ።

ይህንኑ መሠረት በማድረግ የክልሉ ኮማንድ ፖስት የጸጥታ ሁኔታውን ለመቆጣጠር የሰዓት እላፊ ገደብና ክልከላዎችን ጥሎ መቆየቱ ይታወቃል ።

የከተማ አስተዳደሩ የጸጥታ አካላት፣ የከተማው ነዋሪዎች ፣ ወጣቶችና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በሰሩት ቅንጅታዊ ስራ አንጻራዊ ሰላም ሊገኝ ችሏል ።

ይህንን መሠረት በማድረግ የተሽከርካሪዎች የሰዓት ማሻሻያ ተደርጓል ።

1. ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ( ባጃጆች ) እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት ብቻ የነበረው እስከ 3 ሰዓት ድረስ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ።

2. መኪኖች እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ድረስ ብቻ የነበረው አስከ 4 ሰዓት ድረስ አገልግሎት እንዲችሉ።

3.ሞተሮች ባሉበት እንዲቀጥሉ ውሳኔ ተላልፏል ።

በቀጣይ ሞተር ሳይክሎችን በተመለከተ የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን ከተሟሉ ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ኮማንድ ፖስቱ አቅጣጫ የሚሰጥበት መሆኑ ተገልጿል ።

ከዚህ ውጭ የተላለፈ ውሳኔ አለመኖሩን ታውቆ ህብረተሰቡ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴውን በአግባቡ እንዲያከናውን ሆቴሎች ፣ መዝናኛ ቦታዎች ሰላማዊ ሆነው እስከሰሩ ድረስ አካባቢውን በማይረብሽ መልኩ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው ተገልጿል ።

በከተማዋ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የከተማው ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል ።

ተፈናቃዮችን በተመለከተ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ከተማ አስተዳደሩ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል ።

የሜጢ ከተማ አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት በነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚያደርገውን የቁጥጥር ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ​ሜጢ (ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም) - ​የሜጢ ከተማ አስተዳደር ንግድ ጽ...
28/07/2026

የሜጢ ከተማ አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት በነዳጅ ማደያዎች ላይ የሚያደርገውን የቁጥጥር ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ

​ሜጢ (ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም) - ​የሜጢ ከተማ አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት በከተማዋ በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ላይ የጀመረውን የቁጥጥር ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

​የሜጢ ከተማ አስተዳደር ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የንግድ ጽ/ቤት ተወካይ አቶ ክፍሌ አጋር እንደገለጹት፣ በከተማዋ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ማደያዎች የነዳጅ ስርጭት ፍትሃዊ፣ ግልጽ እና ሕጉን በተከተለ መልኩ ለታለመለት ዓላማ (ለተሽከርካሪዎች ብቻ) እንዲደርስ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ ይገኛል።

​ባለፉት ቀናት በተከናወነው የተቀናጀ የቁጥጥር ሥራ ሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድን ለመከላከል እና ሕዝባዊ ሀብቱ ለታለመለት አገልግሎት ብቻ እንዲውል ሰፊ ጥረቶች ተደርገዋል። በዚህም መሠረት ሕጋዊ ሥርዓቱን ጠብቀው በሚንቀሳቀሱት «ዛጎል» እና «MA» ማደያዎች የናፍጣ ስርጭት በየጊዜው እየተቆጣጠሩና እየተለካ፣ ተሽከርካሪዎች በመንግሥት በተቀመጠው መመሪያ መሠረት ቤንዚንና ናፍጣ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

​ተወካዩ አክለውም ከተቋቋመው ግብረ-ኃይል እና ከቴክኒክ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ሕገ-ወጥ ዓላማ ያላቸውን አካላት ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

​በሌላ በኩል፣ የትራንስፖርት አገልግሎት በተቀመጠው ሕጋዊ ታሪፍ መሠረት ብቻ እንዲሰጥ የማድረግ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶበት እንደሚሠራ ተመላክቷል። አሽከርካሪዎች እና የነዳጅ ማደያ ባለቤቶችም ሕጉንና ደንቡን በማክበር ለተቀላጠፈ አገልግሎት አሰጣጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ ቀርቧል።

​የከተማ አስተዳደሩ የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የነዳጅ እጥረት ሳያጋጥም አቅርቦቱ የተረጋጋ እንዲሆን የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።
​በመሆኑም ማንኛውም ባለተሽከርካሪ ናፍጣ ወይም ቤንዚን ሲቀዳ በቴሌብር እና በታሪፉ መሆን እንዳለበት ተገልጿል። ሕገ-ወጥ ተግባራት ሲፈጸሙ የተመለከተ አካል ካለ ለሚመለከተው አካል ጥቆማ በመስጠት ኃላፊነቱን እንዲወጣም መልዕክት ተላልፏል በማለት የጎደሬ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል።

የምስራቅ አፍሪካ የፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት (EAPCCO) አባል ሀገራት የተሳተፉበት ቀጠናዊ የህፃናት ጥበቃ አውደ ጥናት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው‎አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21 ቀን 20...
28/07/2026

የምስራቅ አፍሪካ የፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት (EAPCCO) አባል ሀገራት የተሳተፉበት ቀጠናዊ የህፃናት ጥበቃ አውደ ጥናት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅት አባል ሀገራት (EAPCCO)፣ የኢንተርፖል የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ቢሮ እና አጋር ድርጅቶች ባለሙያዎች የተሳተፉበት ቀጠናዊ የህፃናት ጥበቃ አውደ ጥናት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የአስተዳደርና ልማት ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ነብዩ ዳኜ በአውደ ጥናቱ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የህፃናትን ደህንነት መጠበቅ የሁሉም ማህበረሰብ ኃላፊነት መሆኑን አንስተው በቀጠናችን ያሉ ህፃናት ከድህነት፣ ከግጭት፣ ከመፈናቀል፣ ከቤተሰብ መበታተን እና በተራቀቁ የተደራጁ ወንጀሎች ከፍተኛ አደጋዎች ተጋርጠውባቸዋል ብለዋል።


‎ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል አሁን ላይ እነዚህ ተግዳሮቶች ከሀገርና ድንበር የዘለሉ አሳሳቢ ችግሮች እየሆኑ መምጣታቸውንና በተለይም ወንጀለኞች ቴክኖሎጂዎችንና በሕግ እና ተቋማዊ ሥርዓቶች ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመጠቀም አሁንም የወንጀል ድርጊቱን እየፈፀሙ በመሆኑ ድርጊቱን ለመከላከል የቀጠናው የፀጥታ አካላት ምላሽ የተናጠል ሳይሆን የተቀናጀ፣ መረጃን መሰረት ያደረገ እና የጋራ ትብብርን ያጠናከረ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

‎በናይሮቢ የምስራቅ አፍሪካ ኢንተርፖል ቢሮ ስፔሻላይዝድ ኦፊሰር የሆኑት ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ በበኩላቸው በቀጠናው ሀገራት የሚገኙ ህፃናት ከወንጀል ስጋቶች የተነሳ ከፍተኛ ተጋላጭነት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል ::

በተለይም የወንጀል አይነቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተቀያየሩ፤ ይበልጥ እየተወሳሰቡ እና ድንበር ተሻጋሪ እየሆኑ መምጣታቸውን አንስተው የዛሬው አውደ ጥናት የህፃናት ጥበቃ ረቂቅ ማዕቀፍን ለመገምገም፣ ልምዶችን ለመካፈል እና በስ
ሥራ ላይ የሚያጋጥሙ የዕለት ተዕለት ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ልዩ ዕድል ከመስጠቱም ባሻገር ፖሊሲዎችን ለመቅረጽ እጅግ ጠቃሚ እንደሚሆን ጠቁመዋል።

‎በመጨረሻም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አውደ ጥናቱ በመዲናችን እንዲዘጋጅ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ አመስግነው ይህም ለጉዳዩ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ የአፍሪካን የአብሮነት መንፈስ እና በህፃናት ጥበቃ ላይ ያለውን መሪነት ዳግም የሚያሳይ መሆኑን ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ተናግረዋል።

Address

Gambella Police Commission
Gambela
P.O.BOX24

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gambella Police Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share