01/06/2026
የጮርሶ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው በፍስሀ ገነት የምርጫ ክልል በጮርሶ ወረዳ ድምጻቸውን እየሰጡ ይገኛሉ
#ገደብ፣ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም
የጮርሶ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው ጨምሮ የተለያዩ አመራሮች በፍስሀ ገነት ምርጫ ክልል በትውልድ ቦታቸው በመገኘት ድምጻቸውን እየሰጡ ናቸው ።
የብልጽግና ፓርቲን ወክለው የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እየተወዳደሩ የሚገኙት እጩ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ጮርሶ ቀበሌ ምረጫ ጣቢያ ጤና ጣቢያ ድምጻቸውን በአካል በመገኘት ሰጥተዋል።
7ኛው ጠቅላላ ሀገራ ምረጫ በሰላማዊ መንገድ እየተካሄደ እንደምገኝ የገለጹት አቶ ፍቃዱ ሽፈራው በዕለቱም ማህበረሰቡ በምርጫ ሀገር መንግስት መገንባት በኢትዮጵያ እያደገ ለሚሄደው የዲሞክራሲ ስረዓተ ግንባታ አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን ጠቁመዋል ።
በዕለቱም በምረጫ ጣቢያው የተመለከቱት አካታችነትና የሁሉንም ዜጋ መብት ያከበረ የምረጫ ስረዓት ተግባራዊ እየተደረገ በመሆኑ ከመራጮች ጀምሮ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንድጠናቀቅ የሁሉም የድርሻውን እንድወጡ አሳስበዋል: