Gedeb Woreda Government Communication Service

Gedeb Woreda Government Communication Service ይህ የገደብ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው

የጮርሶ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው በፍስሀ ገነት የምርጫ ክልል በጮርሶ ወረዳ ድምጻቸውን እየሰጡ ይገ...
01/06/2026

የጮርሶ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የብልጽግና ፓርቲ ዕጩ ተወዳዳሪ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው በፍስሀ ገነት የምርጫ ክልል በጮርሶ ወረዳ ድምጻቸውን እየሰጡ ይገኛሉ

#‎ገደብ፣ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

‎የጮርሶ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው ጨምሮ የተለያዩ አመራሮች በፍስሀ ገነት ምርጫ ክልል በትውልድ ቦታቸው በመገኘት ድምጻቸውን እየሰጡ ናቸው ።

‎የብልጽግና ፓርቲን ወክለው የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እየተወዳደሩ የሚገኙት እጩ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ጮርሶ ቀበሌ ምረጫ ጣቢያ ጤና ጣቢያ ድምጻቸውን በአካል በመገኘት ሰጥተዋል።

‎7ኛው ጠቅላላ ሀገራ ምረጫ በሰላማዊ መንገድ እየተካሄደ እንደምገኝ የገለጹት አቶ ፍቃዱ ሽፈራው በዕለቱም ማህበረሰቡ በምርጫ ሀገር መንግስት መገንባት በኢትዮጵያ እያደገ ለሚሄደው የዲሞክራሲ ስረዓተ ግንባታ አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን ጠቁመዋል ።

‎በዕለቱም በምረጫ ጣቢያው የተመለከቱት አካታችነትና የሁሉንም ዜጋ መብት ያከበረ የምረጫ ስረዓት ተግባራዊ እየተደረገ በመሆኑ ከመራጮች ጀምሮ ምርጫው ሰላማዊ ሆኖ እንድጠናቀቅ የሁሉም የድርሻውን እንድወጡ አሳስበዋል:

‎በገደብ ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣብያዎች የድምፅ አሰጣጥ ስነስርዓት ሰለማዊ በሆነ መንገድ እንደቀጠለ ይገኛል‎‎ገደብ ፦ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም‎‎በፍስሀገነት ምርጫ ክልል በገደብ ወረዳ ...
01/06/2026

‎በገደብ ወረዳ በተለያዩ የምርጫ ጣብያዎች የድምፅ አሰጣጥ ስነስርዓት ሰለማዊ በሆነ መንገድ እንደቀጠለ ይገኛል

‎ገደብ ፦ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

‎በፍስሀገነት ምርጫ ክልል በገደብ ወረዳ በሚገኙ በተለያዩ የምርጫ ጣብያዎች የወረዳዉ ማህበረሰብ በለልት በመወጣት የድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርዐቱን በሰላማዊ መንገድ እያከናወነ ይገኛል።

‎በዚህም መሠረት የገደብ ወረዳ አስተዳደር አቶ ስሳይ ታደሴ በፍሳገነት ምርጫ ክልል በገደብ ወረዳ ሀርሙፎ ወጣቶች የምርጫ ጣብያ ተገኝተዉ ድምጻቸዉን ሰተዋል።

‎በሀገረመንግስት ግንባታ ዉስጥ የእያንዳንዱ ዘጋ ድምጽ ትልቅ ዋጋ እንዳለዉ የገለጹት የገደብ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ስሳይ ታደሴ ለሀገር እድገት እና ለዉጥ የምንሆን ፖርት በሰላማዊ ዲሞክራስያዊ በሆነ መንገድ መምረጣቸዉን ገልጸዋል።

‎ምርጫዉ ፍጹም ሰላማዊ እና ድሞክራስያዊ በሆነ መንገድ በዉሉም ምርጫ ጣብያዎች በመከናወን ላይም እንደምገኝ አቶ ስሳይ ጠቅሰዋል።

‎ፍሳገነት ምርጫ ጣብያ ክልል የምክር ቤት አጩ ተወዳዳር ወ/ሮ ፍረነሽ አየለ ምርጫዉ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እየተካሄደ መሆኑን በመግለጽ በ7ኛዉ ሀገራቀፍ ምርጫ የሰቶች ተሳትፎ እጅግ የላቀና የዲሞክራስ ግንባታዉን የምያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።

‎በወረዳዉ በምገኙ ምርጫ ጣብያዎች መርጠዉ ስመለሱ ያነጋገርናቸው ዘጎችም እንደገለጹት የምርጫዉን እለት በጉጉት ሰጠባበቁ እንደነበረ በመግለጽ የምፈልጉትን ፖርት በሰላማዊ እና ዲሞክራስያዊ በሆነ መንገድ መምረጣቸዉን ጠቅሰዋል።

‎በይስሐቅ አበበ
‎ፎቶ ፦ በሄኖክ ሽፈራዉ

የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ‎ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ እንድሁም ዕጩ ተወዳዳሪ እንጂነር ተመስገን ጥላሁን በይርጋጨፌ ምረጫ ክልል ሁለት ድምጻቸውን ተሰጥተዋል።‎‎ገደብ፦...
01/06/2026

የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ‎ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ እንድሁም ዕጩ ተወዳዳሪ እንጂነር ተመስገን ጥላሁን በይርጋጨፌ ምረጫ ክልል ሁለት ድምጻቸውን ተሰጥተዋል።

‎ገደብ፦ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

‎የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
‎ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ እንጂነር ተመስገን ጥላሁን በይርጋጨፌ ምረጫ ክልል ሁለት ድምጻቸውን ቦታው በመገኘት ሰጥቷል ።

‎ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የዜግነት መብታቸውን በመጠቀም ያወጡትን ካርድ በየ ምረጫ ጣቢያው በመገኘት ለሚደግፉት ፓርቲ ድምጽ እየሰጡ ይገኛሉ ያሉት ኢንጂነር ተመስገን የብልጽግና ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክርቤት በትውልድ አከባቢያቸው ይርጋጨፌ ምርጫ ክልል 2 ገርቦታ ቁጥር ሁለት ግድቾ ምረጫ ጣቢያ ድምጻቸውን ሰጥቷል ።

‎እኛም ህዝብን ወክለን የሚንወዳደርው መልካም እድል የሚከፈትበትን የመራጭነት ካርድ ወደ ምርጫ ጣቢያ በመሄድ ኢትዮጵያዊነትን የሚናጸናቤት ዕለት ነው ብለዋል።

‎እያንዳንዱ መራጭ በምሰጠው የሰልፍ ስምረት ከጠዋት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሰልፎ በመጠበቅ የምርጫ ስረዓተ ህጉን ባከበረው ያለ አንዳች እንከን የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን እያከናወነ መሆኑን መገንዘባቸውን ተናግረዋል ።

‎ዘጋቢ ይልማ አበበ
‎ፎቶግራፍ ፦ባምላክ ተፈራ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን በወናጎ ምርጫ ክልል ቁጥር ሁለት 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ  እየተሰጠ ነውገደብ ፦ግንቦት 24/2018በወናጎ ምርጫ ክልል 2 በቂሻ ዳቃ የድምፅ አ...
01/06/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን በወናጎ ምርጫ ክልል ቁጥር ሁለት 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ እየተሰጠ ነው

ገደብ ፦ግንቦት 24/2018

በወናጎ ምርጫ ክልል 2 በቂሻ ዳቃ የድምፅ አሰጣጥ ሥርአት እየተካሄደ ነው።

መራጮች በበኩላቸው ምርጫው ፍፁም ሰላማዊና ፍትሃዊ መሆኑን ተናግረዋል ።

የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር)በወናጎ 2 ምርጫ ክልል ጪጩ ቂሻ ዳቃ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ምርጫው ፍፁም ሰላማዊና ፍትሃዊ እንደነበር መራጮቹ ገልጸዋል።

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ለሀገረ መንግስት ግንባታና ለዲሞክራሲ ሥርአት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑም ተገልጿል።

በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባልና የመንግስት የልማት ድርጅት ምክ/ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ ኮሬ በወናጎ ምርጫ ክልል 1 ሚ/ሲሶታ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል...
01/06/2026

በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባልና የመንግስት የልማት ድርጅት ምክ/ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ ኮሬ በወናጎ ምርጫ ክልል 1 ሚ/ሲሶታ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳደርና የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር)በወናጎ ምርጫ ክልል ሁለት  በሀሮወላቡ ጎራን ድባንድቤ ሻይሳ ጣቢያ ተገኝተው ድምፃ...
01/06/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳደርና የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር)በወናጎ ምርጫ ክልል ሁለት በሀሮወላቡ ጎራን ድባንድቤ ሻይሳ ጣቢያ ተገኝተው ድምፃቸውን ሰጥተዋል

ገደብ፦ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን ምክትል ርዕሰ መሥተዳደሩ ገልጸዋል።

ሥልጣን የህዝቡ በመሆኑ ህብረተሰቡ ይበጀኛል የሚለውን ፓርቲ በነቂስ ወጥተው እየመረጡ መሆናቸውን ገልፀዋል ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ።

በሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ላይ ምርጫ አይተኬ ሚና እንዳለው የገለፁት ዶክተሩ ምርጫው ፍፁም ፍትሃዊና ሰላማዊ እንደሆነም ገልጸዋል ።

በሰኒያ መሐመድ
ፎቶ ፦ሜሮን ንጉሤ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ ገደብ፦ ግንቦት 24/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቲቪ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በ...
01/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ

ገደብ፦ ግንቦት 24/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቲቪ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።

‎በገደብ ወረዳ በተለያዩ ምርጫ ጣብያዎች የድምፅ አሰጣጥ ስነስርዓት እየተካሄደ ይገኛል‎‎ገደብ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም‎በጌዴኦ ዞን ‎ጌደብ ወረዳ በተለያዩ ምርጫ ጣብያዎች የድምፅ አሰጣጥ ...
01/06/2026

‎በገደብ ወረዳ በተለያዩ ምርጫ ጣብያዎች የድምፅ አሰጣጥ ስነስርዓት እየተካሄደ ይገኛል

‎ገደብ ግንቦት 20/2018 ዓ.ም

በጌዴኦ ዞን ‎ጌደብ ወረዳ በተለያዩ ምርጫ ጣብያዎች የድምፅ አሰጣጥ ስነስርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

‎የገደብ ወረዳ ነዋርዎች በለልት በመዉጣት የድምጽ መስጠቱ ሰዓት እስክደርስ በመጠባበቅ ላይ የነበሩ ስሆኑ ሰዓቱ ደርሶ በይፋ ድምጽ መስጠት ጀምረዋል።

‎የዛረዉ ቀን ታርካዊ መሆኑን እና ይበጀናል የምንለዉን ፖርት የምንመርጥበት ነዉ ያሉት ድምጻቸውን ለመስጠት ተሰልፈዉ ያገኝናቸዉ ነዋርዎች ምርጫዉ ልዩ ስሜት ያለዉ እና ስላማዊ መሆኑን ጠቅሰዋል ።

‎በይስሐቅ አበበ
‎ፎቶ፦ ሄኖክ ሽፈራዉ

‎በፍስሀ ገነት  የምርጫ ክልል በገደብ ወረዳ የምገኙ የምርጫ ጣብያዎች ለነገዉ ምርጫ አስፈላግዉን ዝግጅት ማጠናቀቃቸዉን ገለጹ ‎ገደብ ‎:-ግንቦት 23/2018 ዓ.ም‎‎በፍስሀ ገነት  የምርጫ...
31/05/2026

‎በፍስሀ ገነት የምርጫ ክልል በገደብ ወረዳ የምገኙ የምርጫ ጣብያዎች ለነገዉ ምርጫ አስፈላግዉን ዝግጅት ማጠናቀቃቸዉን ገለጹ

ገደብ ‎:-ግንቦት 23/2018 ዓ.ም

‎በፍስሀ ገነት የምርጫ ክልል በገደብ ወረዳ የምገኙ የምርጫ ጣብያዎች ለነገዉ ምርጫ አስፈላግዉን ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል ።

‎ነገ በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ማስፈጸሚያ ቁሳቁሶች በየምርጫ ጣቢያዎች በመሰራጨት ዝግጁ እየሆኑ ይገኛሉ።

‎በዚህም በፍስሐ ገነት ምርጫ ክልል በምገኙ የምርጫ ጣብያዎች ለምርጫዉ የምያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ጨምሮ አስፈላግዉን ቅደመ ዝግጅት በማጠናቀቅ የመራጩን ህዝብ መምጣት በጉጉት እየተጠባበቁ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ።

‎በይስሐቅ አበበ
‎ፎቶ ፦ ሄኖክ ሽፈራዉ

ኢትዮጵያ ሁላችንም የምንጠብቃት የሁላችንም ቤት ናት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋርደዉ ተናገሩ #ገደብ ግንቦት 20/2018 ዓለም/ምኮሚሽነሩ ይህን ያሉት በጌዴ...
28/05/2026

ኢትዮጵያ ሁላችንም የምንጠብቃት የሁላችንም ቤት ናት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ፍስሃ ጋርደዉ ተናገሩ

#ገደብ ግንቦት 20/2018 ዓለም/ም

ኮሚሽነሩ ይህን ያሉት በጌዴኦ ዞን አሁናዊ ጸጥታ ሁኔታን ለመገምገምና በቀጣይ በሚሰሩ ተግባራቶች ዙሪያ ከፌዴራልና ከክልሉ ጸጥታ አካላት ጋር በጌዴኦ ዞን ገደብ ከተማ ዉይይት ባደረጉበት ወቅት ነዉ

ከዉስጥም ከዉጪም ያሉ ጠላቶች ሁሌም አላማቸዉ ኢትዮጵያን ማጥቃት እንደሆነ የገለጹት ኮሚሽነር ፍስሃ ለዚህም ዓላማ መመከት የሚችል በቂ የጸጥታ አካላት በመኖሩ ህብረተሰብም ከጸጥታዉ አካል ጎን በመሆን የሰላምን ስራ እንዲሰሩ ኮሚሽነሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጸጥታ ምክር ቤት የመከላከያ ሰራዊት ተወካይ የሆኑት ጄነራል አስፋው ማመጫ በበኩላቸዉ የሰራዊቱን ዉስጣዊ አንድነቱን በማጎልበት የተጠናከረ የጸጥታ ስራን በመስራት የህዝብን መብቶች ማስከበር ተቀዳሚ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል።

የምርጫ ሂደት ምንም አይነት ወከባ እንዳይኖር ዜጎች በራሳቸዉ ፍቃድ ለመረጡት አካል የድምጽ መስጠት ሂደትን በሰላማዊ መንገድ እንዲሰጡ ሁሉም የጸጥታ አካላት የማህበረሰቡ ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ስራን በትኩረት እንደሚሰራ ጄኔራሉ አክለዉ ገልጸዋል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር የጌዴኦ ህዝብ ሰላም ወዳድ ህዝብ በመሆኑ የራሱንና የአካባቢዉን ሰላም ለማስጠበቅ የሚፈጠሩ ችግሮችን በባህላዊ ስርዓት የሚፈታ ለሰላም ቅድምያ ሰጥቶ የሚሰራ ህዝብ እንደሆነ ጠቁመዋል

የማህበረሰባችንን ሰላምና ደህንነት አስጠብቀን 7ኛዉ ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ ከጸጥታዉ አካል ጎን በመሆን የሰላሙን ስራ በቅንጅት ይሰራል ሲሉ ዝናቡ ወልዴ ዶ/ር መናገራቸዉን ተመላክተናል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጸጥታዉ ከፍተኛ አመራሮች በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ በሀገራዊ ጉዳይ እና 7ኛዉ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ እስከ በታች በመዉረድ የሰላምና የደህንነት ሁኔታ በመቃኘት በቀጣይ ስራ ዙሪያ ምክክር አድርገዋል ሲል የጌዴኦ ዞን ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ዘግቧል።

Address

Gedeb

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeb Woreda Government Communication Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share