03/09/2026
የአየር መዛባት ተከትሎ አባ ጋዳ ቢፎሚ ዋቆ በገደብ ወረዳ ጎቲት ከተማ የፋጭኤ እና የፀሎት መርሃ ግብር አካሄዱ
#ገደብ ነሃሴ 28/2018 ዓ.ም (ኮሙኒኬሽን)
በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ ባንቆ ጎቲት ከተማ የአየር መዛባት ተከትሎ አባ ጋዳ ቢፎሚ ዋቆ ባሊ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የፋጭኤ እና የፀሎት መርሃ ግብር አካሂዷል።
የጌዴኦ ህዝብ የእራሱን ቋንቋ ፣ ፋጭኤ ማድረግ ስርዓት እና ድርቅ ስከሰት በመፀለይ የራሱን የጋዳ ስርዓት ያለው መሆኑን አባጋዶ ቢፎም ዋቆ ተናግሯል።
የራሱን ስርዓት ይዘው በመሄድ ለምድራችን ሰላም እንዲሰፍን ፡ ረሃብና ቸነፈር ከምድራችን እንዲጠፋ ፡ ምዲርቱ ፍሬ እንዲያፈራ እና የበረከት ዝናብ እንዲዘብ ፡ አባ ጋዳ ቢፎሚ ዋቆ ፋጭኤ እና ፀሎት አድርገዋል።
የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ታደሴ ፡ ፈጣሪ ለምድራችን ምህረትና የበረከት ዝናብ እንዲሰጥልን በሁሉም እምነት ተቋማትና በባህላዊ ሾንጎዎች ፀሎት እንዲደረግ መልዕክታቸውን አስተላልፏል።
የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አቶ ከበደ ገራ በበኩላቸው ፈጣሪ ምድራችንን በምህረቱ እንዲሸፍን እና የበረከት ዝናብ እንዲሰጥልን ሁሉም መፀለይ እንዳለባቸው አሳስቧል።
በመርሃ ግብሩ አባ ጋዳ ቢፎሚ ዋቆ ባሊ ፣ የወረዳው ዋና አስተዳደሪ አቶ ሲሳይ ታደሴ ፣ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ ገራ ፣ ባህላዊ ሽማግሌዎች እና የጎቲት ማህበረሰብ ክፍል በተገኙበት የፋጭኤ ስነስርዓት ተደርጓል።
@የገደብ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት።