Gimbo Woreda Communication Affairs

Gimbo Woreda Communication Affairs Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gimbo Woreda Communication Affairs, Government Organization, adis ababa, Gimbo.
(2)

የ7ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ላይ በጊምቦ ወረዳ ከ60 ሺህ በላይ ህዝብ በምርጫ ሂደቱ ይሳተፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለፀ።በጊምቦ ጋዋታ እና በአድያ ካካ ምርጫ ክልል በ63 የምርጫ ጣቢያ...
31/05/2026

የ7ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ላይ በጊምቦ ወረዳ ከ60 ሺህ በላይ ህዝብ በምርጫ ሂደቱ ይሳተፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለፀ።

በጊምቦ ጋዋታ እና በአድያ ካካ ምርጫ ክልል በ63 የምርጫ ጣቢያዎች ከ60 ሺህ በላይ ህዝብ በምርጫ ሂደቱ ይሳተፋል ተብሎ ይጠበቃል።

በአሁኑ ሰዓትም ምርጫ ጣቢያዎች ለመራጮች ዝግጁ ሆኗል።

በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

በጊምቦ ወረዳ የሾምባ ኩሪ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች መማሪያ ክፍል ማስፋፊያ ግንባታ ተመረቀ::የለውጡ መንግስት ለህዝብ ተጠቃሚነት በርካታ የልማት ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል ያሉት የ...
27/05/2026

በጊምቦ ወረዳ የሾምባ ኩሪ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች መማሪያ ክፍል ማስፋፊያ ግንባታ ተመረቀ::

የለውጡ መንግስት ለህዝብ ተጠቃሚነት በርካታ የልማት ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል ያሉት የካፋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻዉ ከበደ ሾምባ ኩሪ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የበርካታ ምሁራን መፍለቂያናት ሲሉ ገልጸዋል::

የተሻለና ተወዳዳሪ ተማሪ ከማፍራት አንጻር የመምህራን ሚና ከፍተኛ በመሆኑ የተሻለ ተማሪ ለማፍራት የድርሻቸዉን ልወጡ ይገባልም ብለዋል።

የሾምባ ኩሪ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዕድሜ ጠገብ ቢሆንም ለብዙ ዓመታት ምቹና ማራኪ ባልሆነ መልኩ በመቆየቱ ባጠረ ጊዜ ውስጥ የወረዳው መንግስትና ሕዝብ ገንብቶ በመጨረስ በዛሬዉ ዕለት ማስመረቅ ችሏል ሲሉ የጊምቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ትብብሩ አሰፋ ገልጸዋል።

አቶ ትብብሩ አያይዘዉም የለዉጡ መንግስት ለማህበራዊ ብልፅግና ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን በዋናነት ደግሞ ለትምሀርት ጥራት በሰጠዉ ልዩ ትኩረት በትምህርት ዘርፉ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛልም ብለዋል።

በወረዳ ደረጃም በርካታ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዉ ለመማር ማስተማር ሥራ ክፍት መሆናቸዉን ያስታወሱት አቶ ትብብሩ በዛሬው እለት ለተመረቀው ትምህርት ቤት የአካባቢውን ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

የትምህርት ቤቱ መገንባት ለተማሪዎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለዉ ያሉት የጊምቦ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ወርቁ በዝህ ትምህርት ቤት ግንባታ ሂደት ውስጥ ህዝቡ ከመንግስት ጎን መሆኑን አሳይቷል ሲሉም ገልጸዋል::

አቶ ሀብታሙ አያይዘዉም አሁን እየታየ ያለዉን የትምህርት ስብራት ለማከም የመምህራን ድርሻ የጎላ በመሆኑ መምህራን ተማሪዎቻቸዉን የማብቃት ሥራ ላይ ልጠናከሩ ይገባልም ብለዋል።

ለትምህርት ቤቱ ግንባታ በተለያየ መልኩ አሻራቸዉን ላሳረፉ ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸዉን አቅርበዋል::

6 የመማሪያ ክፍሎች እንደተገነቡና በአጠቃላይ ለተምህርት ቤቱ ግንባታ ከ8 ሚሊዮን 921ሺ ብር በላይ ወጪ እንደተገነባ የትምህርት በቱ ርዕሰ መምህርት ንግስት አየለ በሪፖርታቸዉ አቅርበዋል።

የሾምባ ክጭብ ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ መላኩ አባግሳ እንዳሉት የትምህርት ቤቱ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ እንድጠናቀቅ ላደረጉ ለአካባቢዉ ማህበረሰብ ምስጋና አቅርበዉ የተሰራዉን ትምህርት ቤት በኃላፊነት ጠብቆ እንደምገለገሉም ተናግረዋል።

ትምህርት ቤቱ እውቀት የሚቀሰምበት ብቻ ሳይሆን የአካባቢዉ ማህበረሰብ የሚገናኝበትና ልማት የሚፋጠንበት የስልጣኔ ማዕከል ነዉ ያሉት የአካባቢዉ ነዋሪዎች ትምህርት ቤቱ ተሰርቶ በመጠናቀቁ ደስተኛ በመሆናቸው ተናግረዋል።

በዕለቱም የክልል፣የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች፣የሀገር ሽማግሌዎች የሃይማኖት አባቶች፣ወጣቶች፣የትምህርት ቤቱ መምህራንና ተማሪዎች ተገኝተዉበታል።

በብርሃነ አባተ
ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

ለ1447ኛ ጊዜ የሚከበረዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች የኢድ አ አድሃ በዓል በጊምቦ ወረዳ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።የኢድ አል አድሃ በዓል በሙስሊም እምነት...
27/05/2026

ለ1447ኛ ጊዜ የሚከበረዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች የኢድ አ አድሃ በዓል በጊምቦ ወረዳ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

የኢድ አል አድሃ በዓል በሙስሊም እምነት ተከታዮች ዘንድ ልዩ ቦታ ተሰጥቶት የሚከበር ታላቅ በዓል ሲሆን ይህም በዓል በታላቅ ክብርና ደስታ የሚከበር በዓል ነዉ።

ኢድ አል አድሃ በዓል የመታመን፣በፈተና የመፅናትና የመታዘዝን የላቀ ዋጋ የሚያሳይ በዓል በመሆኑ የመረዳዳትና የአብሮነታችንን ባህል በማጠንከርና ለተቸገሩ ወገኖቻችን ያለንን በማካፈል የሚከበር ታላቅ በዓል መሆኑ ተጠቁመዋል::

በጊምቦ ወረዳ የእስልምና እምነት ተከታዮችም በዓሉ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴቶች የሚጎሉበት በዓል በመሆኑ ያለንን ለአቅመ ደካማ ወገኖች በማካፈልና መዓድ በማጋራት ልናከብር ይገባል ሲሉ የእምነቱ አባቶችና ተከታዮች ተናግረው በዓሉ የሰላም፤የፍቅር፤የመተሳሰብና የአብሮነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸዉን ገልፀዋል።

በብርሃነ አባተ
ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛው የዒድ አል አድሃ ( አረፋ) በዓል እንኳን አደረሳችሁ:-አቶ አጥናፉ ጌታቸውለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447 ኛውን የዒድ አል አድ...
27/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛው የዒድ አል አድሃ ( አረፋ) በዓል እንኳን አደረሳችሁ:-አቶ አጥናፉ ጌታቸው

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447 ኛውን የዒድ አል አድሃ ( አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት የጊምቦ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፉ አቶ አጥናፉ ጌታቸው አስተላለፉ።

ሀገራችን የተለያዩ ብሔሮችንና ሃይማኖቶችን በአንድነት አቅፉ የምትኖር ድንቅ ሀገርናት ያሉት አቶ አጥናፉ ከዝህም ዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ መልካምነት፣ አብሮነት እና መተጋገዝ ጎልተው የሚታይበት በዓል አንዱ ነው ሲሉ ተናግረዋል::

ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር ሃይማኖታዊ አስተምሮ በመከተል በወረዳችን ጎልቶ የወጣውን የእርስ በእርስ በአብሮነትና፣ በአንድነት፣በመረዳዳትና የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በሚያጎለብትና በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባልም ብለዋል።

የእምነቱ ተከታዮች ይህን በዓል ሲያከብሩ ከፊታችን ሀገራዊ ምርጫን ለማድረግ በተቃረብንበት ወቅት በመሆኑ ፍጹም ሰላማዊና ሕዝቡ በነጻነት ወጥቶ ድምጹን የምሰጥበት እንዲሆን የበኩላቸውን እንድወጡ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል::

በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣የደስታና የብልጽግና እንዲሆን ሲሉ አቶ አጥናፉ ጌታቸው መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

‎የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

እንኳን ለ1447ኛው የአረፋ (ዒድ አል-አድሐ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ:-አቶ ትብብሩ አሰፋየጊምቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ትብብሩ አሰፋ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛ...
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የአረፋ (ዒድ አል-አድሐ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ:-አቶ ትብብሩ አሰፋ

የጊምቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ትብብሩ አሰፋ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የአረፋ (ዒድ አል-አድሐ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሲሉ መልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚከበሩ ታላላቅ በዓላት መካከል የአረፋ (ዒድ አል-አድሐ) በዓል አንዱ ነው ያሉት አቶ ትብብሩ አሰፋ ይህ በዓል የመስዋዕትነትና የእምነት ማሳያ መንፈሳዊ በዓል ነው ብለዋል።

በሀገራችንም ይሁን በወረዳችን ልክ እንደወትሮ በዓሉ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳት፣ የሰላምና የአብሮነት እሴቶችን ይበልጥ የሚያጠናክር በዓል ነው ሲሉም ገልጸዋል::

በወረዳችን እየተከነወነ የሚገው የልማትና የአንድነት ጉዞ በጋራ ማስቀጠል ላይ ሕዝበ ሙስሊሙ በመመካከር በዓሉን እንድያከብሩ ብለዋል::

ይህ በዓል በሀገራችን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊደረግ ጥቂት ቀናት ብቻ በቀረበት መሆኑ ልዩ ትርጉም አለው ያሉት አቶ ትብብሩ ይህንን የሰላም እሴታችንን በመጠበቅ፣ቀጣዩን የምርጫ ወቅት ፍፁም ሰላማዊ፣ስልጡንና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ልንፈፅመው ይገባል ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በሀገራችንና በወረዳችን ባህል ልክ እንደ ቀድሞ ለአቅመ ደካሞች፣ ለተቸገሩና ለድጋፍ ፈላጊ ወገኖቻችን መዓድ የማጋራት፣የመረዳዳትና የመተሳሰብ ስራ በማጠናከር የበዓሉን ደስታ በጋራ እንድንካፈል አሳስባለሁ ብለዋል።

በዓሉ የሰላም፣የደስታ፣የፍቅርና የአንድነት እንድሆን መልካም ምኞተ ነው ሲሉ አቶ ትብብሩ አሰፋ ገልጸዋል::

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

የጊምቦ ወረዳ ልዑክ ቦንጋ ከተማ ለብልጽግና ፓርቲ ሕዝባዊ ሰልፍ ቦንጋ ከተማ ገብተዋል::በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የአስተዳደርና ፖለቲካ መቀመጫ እንዲሁም የካፋ ዞን ርዕሰ ከተማ...
26/05/2026

የጊምቦ ወረዳ ልዑክ ቦንጋ ከተማ ለብልጽግና ፓርቲ ሕዝባዊ ሰልፍ ቦንጋ ከተማ ገብተዋል::

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የአስተዳደርና ፖለቲካ መቀመጫ እንዲሁም የካፋ ዞን ርዕሰ ከተማ ቦንጋ አደባባይ ላይ የብልጽግና ፓርቲ ድጋፍና የምርጫ ቅስቀሳ ሰልፍ ላይ የጊምቦ ልዑክ እየተሳተፈ ይገኛል::

በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

ሀገረ መንግሥት መመስረት ላይ የሴቶች ሚና የጎላ ነው፦ወ/ሮ ትዕግስት በላይ።7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ አስመልክቶ በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ሾቻ ቀበሌ የቡና ጠጡ እና የብልጽግና ፓርቲ የእጩ...
25/05/2026

ሀገረ መንግሥት መመስረት ላይ የሴቶች ሚና የጎላ ነው፦ወ/ሮ ትዕግስት በላይ።

7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ አስመልክቶ በካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ሾቻ ቀበሌ የቡና ጠጡ እና የብልጽግና ፓርቲ የእጩ ትውውቅ መድረክ ተካሄደ።

የሴቶችን እኩልነት በአደባባይ ያረጋገጠ ፓርቲ ቢኖር ብልፅግና ፓርቲ ነው ያሉት በአዲያ ካካ ምርጫ ክልል ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ለክልል ምክር ቤት እጩ የሆኑትና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የገቢዮች ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት በላይ ለዝህም በ7ተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ላይ ይህን ፓርቲ መርጦ ማስመረጥ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል::

ሁሉም ሴቶች ለቀጣይ 5 አመታት ብልጽግና ፓርቲ መንግሥት ሆኖ ሀገርን እንዲመራ ልናደርግ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በእለቱም ሌላኛው በፕሮግራም ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጊምቦ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ትብብሩ አሰፋ እንዳሉት የጊምቦ ወረዳ በለውጡ መንግስት የህዝቡን የተለያዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በርካታ የልማት ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውቀዋል።

አቶ ትብብሩ አያይዘው ለአብነትም በሾቻ ቀበሌ 2ኛ ትውልድ አጠቃላይ አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ (Comprehensive HP) እንዲሁም የመንገድ ልማት ስራዎች ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

የብልጽግና ጉዞን በዘላቅነት ለማስቀጠል የብልጽግና ፓርቲ መወዳደሪያ ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶን ይምረጡ ያስመርጡ ሲሉ የጊምቦ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አበዛሽ መለሰ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ሌላኛው በአዲያ ካካ ምርጫ ክልል ብልፅግና ፓርቲን በመወከል እጩ የሆኑት ወ/ሮ አልማዝ ታደሰ በበኩላቸው እንዳሉት የተጀመሩ ሁሉ አቀፍ የብልጽግና ጉዞ ለማስቀጠልም ይሁን በቀጣይ ሌሎች ልማቶችንም ለማስጀመር ብልጽግና ፓርቲን መምረጥ ማስመረጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

በሾቻ ቀበሌ የቡና ጠጡ ፕሮግራም ያዘጋጁ ሴቶች በስንዴ ነዶ የተወከለውን የብልፅግና ፓርቲን ግንቦት 24 በሚደረገው ምርጫ ላይ ለመምረጥ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በመጨረሻም ከቡና ጠጡ ፕሮግራም ቦኃላ የግንባታ ሂደቱ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት የቀረው በሾቻ ቀበሌ 2ኛ ትውልድ አጠቃላይ አገልግሎት መስጫ ጤና ኬላ (Comprehensive HP) ጎብኝተዋል።

በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

በሀገረ መንግስት ግንባታና በሀገራችን ብልጽግና ጉዞ ውስጥ የሴቶች አበርክቶ የጎላ ነው:-ወ/ሮ ሄለን ድበበበዛሬው እለት በጊምቦ ወረዳ ዑፋ ከተማ በአደባባይ የሴቶች ቡና ጠጡ ፕሮግራምና የብል...
24/05/2026

በሀገረ መንግስት ግንባታና በሀገራችን ብልጽግና ጉዞ ውስጥ የሴቶች አበርክቶ የጎላ ነው:-ወ/ሮ ሄለን ድበበ

በዛሬው እለት በጊምቦ ወረዳ ዑፋ ከተማ በአደባባይ የሴቶች ቡና ጠጡ ፕሮግራምና የብልጽግና ፓርቲ መወዳደሪያ ምርጫ ምልክት ማስተዋወቅ በደመቀ መልኩ ተካሂዶ ውሏል።

በሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደት ውስጥ የሴቶች አበርክቶ የጎላ ነው ሲሉ የገለፁት የኢፌዲሪ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስቲር ዴኤታና የጊምቦ ገዋታ ምርጫ ክልል የሕዝብ ተወካዮች እጩ ወ/ሮ ሄለን ደበበ በብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ተደማጭነት ብሎም ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ጎልቶ የታየበት ነው ብለዋል።

ወ/ሮ ሄለን አያይዘዉም ሴት እህቶቻችንን በዘመናዊ ትምህርት በማብቃት የሀገር ተረካቢ የማድረግ ሂደት ውስጥ ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉን ልወጣ ይገባልም ብለዋል።

ፓርቲው ሴቶች ያላቸዉን ተሳትፎ እንዲያጠናክሩ ከወትሮ በተሻለ እየሰራ ይገኛል በማለት ብልፅግና ፓርቲን ይምረጡ ያስመርጡ ሲሉ ወ/ሮ ሄሌን ደበበ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

ብልፅግና ፓርቲ ከመቸዉም ግዜ በበለጠ ለሴቶች ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል ሲሉ የጊምቦ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪት አበዛሽ መለሰ ገልፀዋል::

የሀገራችን ሰላም፣ልማትና ዲሞክራሲ ያለ ሴቶች ንቁ ተሳትፎ የማይሳካ ነዉ ያሉት ወ/ሪት አበዛሽ የዛሬዉ ፕሮግራም ከሌላዉ ግዜ በተለየ መልኩ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ እጅግ ደምቆ የታየበት ነው በማለት አብራርተዋል።

በእለቱም በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ብልጽግና ፓርቲን በመወከል ከሚወዳደሩ ሴት እጩዎች የኢፌዲሪ ከተማ ልማትና ኪንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ሄለን ድበበ፣የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይዎት አሰግድ፣የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት በላይን ጨምሮ ሌሎች ሴት አመራሮችና መንግስት ሠራተኞች እንዲሁም በአካባቢው የሚገኙ ሴቶች ተሳትፈውበታል::

በብርሃነ አባተ
ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ከማሸጋገር አንጻር የብልጽግና ፓርቲ ድርሻው የጎላ መሆኑ ተጠቆመ።የ7ተኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ ከውሽውሽ ሻይ ልማት ከተውጣጡ የማህበራዊ መ...
23/05/2026

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ከማሸጋገር አንጻር የብልጽግና ፓርቲ ድርሻው የጎላ መሆኑ ተጠቆመ።

የ7ተኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን አስመልክቶ ከውሽውሽ ሻይ ልማት ከተውጣጡ የማህበራዊ መሠረቶች ጋር የጋራ ውይይት በውሽውሽ ሻይ ልማት ድርጅት ተካሂዷል።

ብልፅግና ፓርቲ ሀገርን እያሻገር ያለ ፓርቲ ነው ያሉት በጊምቦ ገዋታ ምርጫ ክልል ለክልል ም/ቤት ፓርቲውን በመወከል እጩ ሆነው የቀረቡት የደ/ም/ኢ/ሕ/ክልል የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ ለዚህም ይህን ፓርቲ በቀጣይ በመምረጥ የሀገሪቱን ዕድገት እውን ልናደርግ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

ብልፅግና የህዝቡን ችግር የሚያዳምጥ ሰው ተኮር የሆነ ፓርቲ ነው ሲሉ የአዲያ ካካ ምርጫ ክልል ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ብልፅግና ፓርቲን በመወከል እጩ ሆኖው የቀረቡት አቶ ታከለ ታምሩ ተናግረዋል።

አቶ ታከለ አክለውም መጪው 7ተኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ፍጹም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለመራጭነት የሚያበቃውን ካርድ የወሰዱ የሁሉንም እርብርብ የሚፈልግ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በጊምቦ ገዋታ ምርጫ ክልል ለክልል ም/ቤት ፓርቲውን በመወከል እጩ ሆነው የቀረቡት የጊምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትብብሩ አስፋ በበኩላቸው የውሽውሽ ሻይ ልማት በውስጡ ያቀፋቸው ሰራተኞች ከተለያዩ አካባቢዎች ስብስብ በመሆኑ የኢትዮጵያዊነት ተምሳሌት ነው ብለዋል።

ምርጫው ያለምንም ችግር እንዲጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሰሩና በዕለቱም በነቂስ በመውጣት ለመምረጥና ለማስመረጥ በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሆነ በውይይቱ ወቅት የተገኙ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

የድርጅቱ ሰራተኞች በግንቦት 24 ያለምንም መንጠባጠብ ህዝቡ በነቂስ ወጥተው እንደሚመርጡ የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ንጉሴ ባደረጉት ንግግር ጠቁመዋል።

በሀገራችን እድገትና አንድነት ብልፅግና ፓርቲ እያሳረፈ ያለው አሻራ ጠንካራ ነው ሲሉ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ የሆኑት አቶ አጥናፉ ጌታቸው አብራርተዋል።

በውይይቱም የጊምቦ ገዋታና አዲዮ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ም/ቤት ብልፅግና ፓርቲን የምወክሉ እጩዎች ተገኝተው ከወከላቸው ህዝብ ጋር ትውውቅና ውይይት አድርገዋል።

በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

ብልፅግና ፓርቲ ልማት ወዳዱን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎኑ በማሰለፍ ሰፋፊ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል:-ወ/ሮ ሄለን ደበበበ7ተኛዉ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ላይ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወ...
22/05/2026

ብልፅግና ፓርቲ ልማት ወዳዱን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎኑ በማሰለፍ ሰፋፊ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል:-ወ/ሮ ሄለን ደበበ

በ7ተኛዉ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ላይ ብልጽግና ፓርቲን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት የሚወዳደሩ እጩዎች ከዑፋ ሕዝብ ጋር የትውውቅና የውይይት መርሃ ግብር አካሄዱ::

ብልፅግና ፓርቲ ልማት ወዳዱን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎኑ በማሰለፍ ሰፋፊ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ያሉት የኢፌዲሪ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሄለን ደበበ የካፋ ህዝብ በቀደመ ታሪኩም ዲሞክራሲን ስያራምድ የነበረ ያለምንም መከፋፈል ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር የቆየ ድንቅ ህዝብ ነው ሲሉም ተናግረዋል::

ብልፅግና ፓርቲ እንደ ሀገር በርካታና ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በመስራት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚን በማሳደግ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸዉ ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ እየተሰራ ነው ብለዋል::

ወ/ሮ ሄለን አያይዘው ኢትዮጵያ በኢኮኖሚም ሆነ በፖለቲካዉ ዘርፍ በአለም ደረጃ ተደማጭነትን እያተረፈች ትገኛለች በማለት ጠቁመዋል።

በሌላ መልኩ ጊምቦ ወረዳ ላይ እየታዩ ላሉ ፈጣን ለዉጦች የወረዳዉን ንቁ አመራሮችና እንዲሁም የጊምቦ ወረዳ ህዝብም ለልማት ያለው ቁርጠኝነት ጠንካራ ስለመሆኑ ምስጋና አቅርበዋል::

ብልፅግናን መምረጥ ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ማሰረከብ ነው ያሉት ወ/ሮ ሄለን ደበቀ ብልፅግናን ይምረጡ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዙ ዉጣ ውረዶችን እያስተናገደች እዚህ የደረሰች ሀገርናት ሲሉ የጊምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትብብሩ አሰፋ ገልጸው ቀደም ሲል በሀገራችን የነበረዉ የዲሞክራስ ያልዳበረ መሆኑን አስታዉሶ ከለዉጡ ወዲህ ሀገራችን ፍፁም ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ነጠላ ትርክቶችን በመኮነን እና የጋራ ትርክትን በማጽናት ሁለንተናዊ ብልፅግናን እያረጋገጠ የሚገኝበት ግዜ ላይ ነን ብለዋል።

አቶ ትብብሩ አያይዘዉም ብልፅግና ፓርቲ ሀገሪቱ ላይ የሚገኘዉን የውሃ ሃብቶችን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር የስንዴ ልማቱን በስፋት በማምረት ኢትዮጵያ ስንዴን ወደ ውጪ ሀገራት በመላክና በአፍሪካ ግንባር ቀደም ከምባሉት ተርታ መሰለፍ ችላለች ሲሉም ጠቁመዋል::

ጊምቦ ወረዳ በተለያዩ መሰረተ ልማቶች እጅግ የተፋጠነ ለውጥ በማምጣት ግምባር ቀደም ወረዳ በመሆኑ የጉብኝት ማዕከል ሆኖ ከመቆየቱም ባሻገር ለሌሎች አካባቢዎች ምሳሌ መሆን የሚችል ወረዳ ነውም ተብሎዋል።

የዑፋ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስክያጅ አቶ ፍቅሩ ገላየ በነቂስ በመዉጣት ፕሮግራሙን ለተሳተፈዉና ላስተባበረው ማህበረሰብ ምስጋናቸዉን አቅርበዋል::

በዕለቱም የጊምቦ ገዋታ ምርጫ ክልል የክልል ም/ቤት ዕጩዎች፣የክልል አመራሮች፣የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች የሃይማኖት አባቶች፣የሃገር ሽማግሌዎች ወጣቶች፣ባለሃብቶችና ሌሎች የአካባቢዎች ነዋሪዎች ተሳትፈውበታል።

በብርሃነ አባተ
ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

Address

Adis Ababa
Gimbo

Telephone

+251905651100

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gimbo Woreda Communication Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share