Gimbo Woreda Communication Affairs

Gimbo Woreda Communication Affairs Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gimbo Woreda Communication Affairs, Government Organization, adis ababa, Gimbo.
(2)

በጊምቦ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።በ2018 ዓ.ም ወረዳው የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን ስያከናውን በቆየባቸው መንገዶች ጠን...
02/09/2026

በጊምቦ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በ2018 ዓ.ም ወረዳው የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን ስያከናውን በቆየባቸው መንገዶች ጠንካራና ደካማ ጎኖችን መለየት እንዲሁም የአመራሩ ቁመና ጠንካራ እንዲሆን የሚረዳ መድረክ ነው ሲሉ የካፋ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ታከለ ታምሩ ተናግረዋል::

የግምገማውና የምዘናው ዓላማ አመራሩ በተሰማራበት መስክ ቁርጠኛ ሆኖ ሁለንተናዊ ልማቶችን ውጤታማ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚችል ብቁ አመራር መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል::

በተመሳሳይ መልኩ በፓርቲ መሪነት በየወቅቱ የሚወርዱ የኢኒሼቲቭ ስራዎችን እና ሌሎች የልማት ስራዎች ውጤታማ ማድረግ የሚችል ጠንካራ አመራር በመፍጠር የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞ እውን ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ አቶ ታከለ ታምሩ ተናግረዋል::

ግምገማውና ምዘናው በወረዳው እየተሰሩ ያሉ ጠንካራ የልማት ስራዎችን ለማስቀጠል እንዲሁም ጉድለቶችን ለማረም የምረዳ ከመሆኑ ባሻገር በአስተሳሰብና በተግባር አንድነት የተገነባ ጠንካራ አመራር መፍጠር ላይ ተግባር የመፈጸም አቅም፣የስነምግባርና ሌሎች ጉዳዮችን በማጥራት ውጤታማ እንዲሆኑም ይረዳል ብለዋል::

ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

ባሳለፍነው ዓመት የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ''ማሽቃሮ''በዓል አከባበርና የቡና አፈላል ስነ-ስርዓትየጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤትወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-የቴሌግ...
01/09/2026

ባሳለፍነው ዓመት የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ''ማሽቃሮ''በዓል አከባበርና የቡና አፈላል ስነ-ስርዓት

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

የህብረት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ክረምት ወራት በጎ ፍቃድ በማጠናከሪያ ትምህርት ስማሩ የቆዩ 139 ተማሪዎችን አስመረቀ።ከጀመረ ሁለተኛ ዓመቱን የያዘ ይህ የክረምት ወራት...
29/08/2026

የህብረት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ክረምት ወራት በጎ ፍቃድ በማጠናከሪያ ትምህርት ስማሩ የቆዩ 139 ተማሪዎችን አስመረቀ።

ከጀመረ ሁለተኛ ዓመቱን የያዘ ይህ የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ መርሃ ግብር የማጠናከሪያ ትምህርት ዛሬም ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል 139 ተማሪዎችን ማስመረቁ ነው የተገለፀዉ።

የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ ማጠናከሪያ ትምህርት ተማሪዎችን በቀለም ትምህርት ከማብቃት ባለፈ በስነ ምግባርም ስታነፁ ቆይተዋል ያሉት የጊምቦ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ወርቁ ወረዳዉ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ውጤትማ በሆነበት ድል ማግስት ይህ ምረቃ መደረጉ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል ሲሉ ተናግረዋል።

የህብረት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሌሎች ትምህርት ቤቶች አርዓያ ነዉም ሲሉ አክለዋል።

የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ በብዙ ዘርፍ በርካታ ሥራዎችን እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ከዚህም ውስጥ አንዱ የትምህርት ስራ መሆኑን አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል::

ዛሬም በዚሁ ህብረት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሁለተኛ ግዜ እያስመረቀ ይገኛል ያሉት አቶ ሀብታሙ ለዚህም በጎ ሥራ ከጎናቸዉ ላልተለዩት ባልድርሻ አካላቶች ምስጋና አቅርበዋል::

በዕለቱም የእስካሁን የሥራ ሪፖርት በመምህር ሙላቱ ወ/ሚካኤል ቀርቧል።

ትምህርት ለሁሉም ዕድገት መሰረት ነዉ ያሉት የህብረት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር መምህር ሀብታሙ ሃ/ሚካኤል ተማሪዎች በዋና ዋና የትምህርት አይነቶችና በኮሚፒዩተር ትምህርት በስፋት ስማሩ ቆይተዋል ብለዋል::

ተማሪዎች ከትምህርት መርሃ ግብር ጎን ለጎን የአረንጓዴ አሻራ ተከላ፤ግቢ የማስዋብ ስራና መሰል በጎ ተግባራትን ስያከናዉኑ ቆይተዋል ሲሉ አያይዘዉ የገለጹት መምህር ሀብታሙ በክረምት ወራት በጎ ፍቃድ ማጠናከሪያ ትምህርት ላይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ላስተማሩ መምህራንና ለወረዳዉ ትምህርት ጽ/ቤት ምስጋና አቅርበዋል።

የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ ማጠናከሪያ ትምህርቱ ልጆች የክረምት ግዜያቸዉን በተለያዩ ቦታዎች ልውሉ ከነበሩበት ቦታ የመለሳቸዉ ነዉ ያሉት የተማሪ ወላጆች ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ተናግረዋል።

በዕለቱም የተለያዩ አስተማሪ ድራማዎች፤ስነፅሁፎች በተማሪዎች ቀርቦ እንዲሁም በትምህርታቸዉ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት በማበርከት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

በብርሃኔ አባቴ
ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

በጊምቦ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ክረምት ወራት በጎ ፍቃድ ተግባር አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ላይ ውይይት ተካሄደ::በጊምቦ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ክረምት ወራት በጎ ፍቃድ ተግባር አፈጻጸም ያለበት ...
28/08/2026

በጊምቦ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ክረምት ወራት በጎ ፍቃድ ተግባር አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ላይ ውይይት ተካሄደ::

በጊምቦ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ክረምት ወራት በጎ ፍቃድ ተግባር አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ላይ የጊምቦ ወረዳ አቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ ውይይት አካሄደ::

የስራ መስኮችን መለየትና መረጃ በማደራጀት የሪፖርት አካል ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ የጊምቦ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አጥናፉ ጌታቸው ገልጸው ለዝሁ ተግባር ውጤታማነት አቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላቶች ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል::

በወረዳው የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የስራ መስኮችን ውጤታማ ለማድረግ እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ አበርታች ነው ያሉት አቶ አጥናፉ ይህንኑ ተግባር ይበልጥ በማጠናከር ውጤታማነቱን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ ነው የተናገሩት::

305 ደርዘን ደብተርና 117 ፓኮ እስክሪፕቶ እንዲሁም የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት 7 ደርዘን ደብተርና 3ፓኮ እስክሪፕቶ ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች እንዲሆን ማሰባሰብ መቻሉ፣22ሺ 250 ካሬ ሜትር ላይ የጸረ ወባ ዘመቻ ላይ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን ማፋሰስና ማዳፈን መቻሉ፣124 ዩኒት ደም ልገሳ መደረጉ፣በማዘጋጃ ከተሞች የጎርፍ ማፋሰሻ ቦይ 1.4ኪሎ ሜትር መከናወን መቻሉ፣56 ሰዎች በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የሰርተፊከት ባለቤት መሆናቸው፣ከ2ሚሊዮን 300ሺ በላይ ችግኞች በአሬንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ለአቅመ ደካሞች 33 አዲስ ቤት መገንባቱ፣በከተሞች ማስ ስፖርት መስራትና የአካባቢ ጽዳት በሪፖርት ከቀረቡት መካከል ናቸው::

የወረዳው አቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ በሪፖርት የቀረበውን አፈጻጸም ላይ ውይይት በማካሄድ ነው ቀጣይ አቅጣ ማስቀመጥ የተቻለው::

ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

የዘንድሮን ማሽቃሮ ስናከብር በዓሉን ዩኔስኮ ለማስመዝግብ የጀመርነውን እንቅስቃሴ በሚያጎላ መንገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች መስራት አለባቸው:- አቶ  አዳሙ እሸቱየ2019 ዓ/ም የካፈቾ...
28/08/2026

የዘንድሮን ማሽቃሮ ስናከብር በዓሉን ዩኔስኮ ለማስመዝግብ የጀመርነውን እንቅስቃሴ በሚያጎላ መንገድ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች መስራት አለባቸው:- አቶ አዳሙ እሸቱ

የ2019 ዓ/ም የካፈቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ "ማስቃሮ" በዓል አከባበር ሽፋን አሰጣጥን አስመልክቶ ከሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ጋር የጋራ ውይይት ተደርጓል::

"ማሽቃሮ በዓል"አከባበር ሂደት እና በሚደረጉ ዝግጅቶች ላይ ተጨባጭነት ያላቸውና አወንታዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ማድረስ ከሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች እንደሚጠበቅ ተገልጿል::

በዓሉን የዓለም የማይዳሰስ ቅርስ አድርጎ በዩኒስኮ እንዲመዘገብ የሚደረገውን ዝግጅት ለመደገፍ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት እና የዘርፉ ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የማሽቃሮ በዓል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮሚቴ ሰብሳቢና የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳሙ እሸቱ ገልጸዋል ።

የ2019 ዓ/ም ማሽቃሮን በዓል ለየት የሚያደርገው በዩኒስኮ ለማስመዝገብ በየደረጃው ጥናት በተጀመረበት ወቅት የሚከበር መሆኑን የተናገሩት ኃላፊው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ከፍተኛ ተጽዕኖ መፍጠር እንዳለባቸው ተናግረዋል ።

በዓሉ የማንነታችን መገለጫ በመሆኑ ያለንን አቅም ሙሉ በሙሉ ተጠቅመን መስራት ይጠብቀናል ሲሉ አቶ አዳሙ ጠቁመዋል።

"የማስቃሮ በዓል" የሰላም ፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የአዲስ ተስፋ ማብሰሪያ እንደመሆኑ መጠን የሚዲያ ባለሙያዎች አጽንኦት ሰጥቶ መስራት እንደምገባም አሳስበዋል ።
በባህል አልባሳት፣ ባህላዊ ምግቦችና መጠጦች፣ እንዲሁም በባህላዊ ጭፈራዎችና በሌሎች እሴቶች ላይ ማተኮር እንደምያስፈልግ ተገልጿል።

የማሽቃሮ በዓል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮሚቴ አባልና የካፋ ማህበረሰብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ስራ አስፈፃሚ አቶ አስራት ኃይሌ በበኩላቸው በዓሉ በካፋ እና በሀገራችን ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለም ህዝብ እንዲታወቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

አጠቃላይ በዓሉን አስመልክቶ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎችን በመስራት ህዝባዊ በዓል ማድረግ ይገባልም ብለዋል አቶ አስራት።

የማሽቃሮ በዓል አከባበር ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ እተሻሻለ መምጣቱን የማሽቃሮ በዓል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮሚቴ አባልና የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ቦንጋ ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ሳልልህ ተናግረዋል ።

የማሽቃሮን በዓል ለዓለም ለማስተዋወቅ ትልቅ ተልዕኮ የተጣለበት ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት ላይ መሆኑን ገልጸዋል ።

የሚዲያ ስራዎችን በተበታተነ መንገድ ሳይሆን በተደራጀ መልኩ በመስራት ለዓለም አጎልብቶ ማሳይት አስፈላጊ ነው ብለዋል አቶ ስንታየሁ ።

የውይይት ተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችና ሀሳብ አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን በተለይም የሚዲያና ተቋማት ተጨባጭ መረጃዎችን ይዘው የካፋን ባህል ታሪክ እና እሴት የሚያጎሉ ዘገባዎች ሽፋን መስጠት እንደሚያስፈልግ ጠቁሟል::

የመድረኩ ተሳታፊ የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ባለሙያዎች በበኩላቸው፣ የማስቃሮ በዓል ባህላዊ ገጽታውን ጠብቆ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበርና ሰፊ የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኝ የበኩላቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣትም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ባሉሙያዎች በሰጡት አስተያየት በበዓል ዋዜማ እና በዕለቱ ከሎጅስቲክስ አና ተሽከርካሪ ከመመደብ ጀምሮ ተገቢ ትኩረት መሰጠት እንዳለበት አመላክቷል::

ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና ሀሳቦች በመድረክ መሪዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ተጠናቋል ሲል የዘገበው የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

በሌላኛው የMixid martial art(MMA) ጆኒ ሰዶን አሸነፈ...‼️
28/08/2026

በሌላኛው የMixid martial art(MMA) ጆኒ ሰዶን አሸነፈ...‼️

ንቃተህሊና ሮቤልን በማሸነፍ የMixid martial art አሸናፊ ሆነ
27/08/2026

ንቃተህሊና ሮቤልን በማሸነፍ የMixid martial art አሸናፊ ሆነ

በMMA(mixid martial art) ውድድር''የመጨረሻዋ ሰአት ደረሰች ሴዶ Vs ጆኒ''ማን ያሸንፋል? ይገምቱ
27/08/2026

በMMA(mixid martial art) ውድድር''የመጨረሻዋ ሰአት ደረሰች ሴዶ Vs ጆኒ''

ማን ያሸንፋል? ይገምቱ

''ወገሞ አንድነት ማህበር''በ2019 ዓ.ም ለሚከበረው የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ''ማሽቃሮ'' እንዲሆን የ40ሺ ብር ገንዘብ ድጋፍ አበረከተ::''ወገሞ አንድነት ማህበር'' ከዝህ ቀ...
27/08/2026

''ወገሞ አንድነት ማህበር''በ2019 ዓ.ም ለሚከበረው የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል ''ማሽቃሮ'' እንዲሆን የ40ሺ ብር ገንዘብ ድጋፍ አበረከተ::

''ወገሞ አንድነት ማህበር'' ከዝህ ቀደም ለጊምቦ ወረዳ ባህል ማዕከል እንዲሆን የተለያዩ ቅርሶችን ማበርከታቸው የተገለጸ ሲሆን ይህ ማህበር በየዓመቱ በሚከበረው ''ማሽቃሮ''በዓል በጊምቦ ወረዳ ተገኝተው በአብሮነት እያከበሩ መሆናቸውም ተመላክቷል::

በዛሬው እለት የተበረከተው የ40ሺ ብር የገንዘብ ድጋፍ በዘንድሮ ዓመት ለሚከበረው የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል እንድሆን ''የወገሞ አንድነት ማህበር'' ልቀመንበር በሆኑት በአቶ ገረሞ ታከለ ነው ድጋፉ የተደረገው::

በእለቱም የወረዳው ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተገኝ ማሞ፣ጊምበራሻ መለሰ መሸሻ እና ጋወራኖ አብርሃም ዘውዴ ተገኝተው ምስጋና አቅርበዋል::

ምስል:-በአቤል ተስፋዬ

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

በዛሬው እለት ውሽውሽ ከተማ ላይ ከክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አንዱ የሆነው ማስ ስፖርት ተካሄደ::''የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ሌጤናችን የአከባቢ ጽዳት ለውበታችን''በሚል መሪ ቃል በውሽውሽ ከ...
27/08/2026

በዛሬው እለት ውሽውሽ ከተማ ላይ ከክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አንዱ የሆነው ማስ ስፖርት ተካሄደ::

''የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ሌጤናችን የአከባቢ ጽዳት ለውበታችን''በሚል መሪ ቃል በውሽውሽ ከተማ የክርምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተከናውኗል::

ባሳለፍነው ሳምንት በወረዳዉ ዑፋ ከተማ በተመሳሳይ መልኩ የማስ ስፖርት መካሄዱን የገለጹት የጊምቦ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት የስፖርት ተሳትፎና ውድድር ባለሙያ አቶ ካሳሁን አብዲሳ በነገው እለትም በዑፍ ከተማ ለሁለተኛ ጊዜ ይህ ተግባር እንደሚቀጥል ተናግረዋል::

አቶ ካሳሁን አብዲሳ አያይዘው በዝሁ ተግባር ጎን ለጎን የአካባቢ ጽዳት ዘመቻ በማድረግ በክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ የድርሻቸውን እየተወጡ እንዳሉ ነው የገለጹት::

በተለያዩ ከተሞች ተጠናክሮ የሚከናወን ነው ያሉት አቶ ካሳሁን በዝሁ ተግባር የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ወጥቶ እንድሳተፉ መልክት አስተላልፈዋል::

የጊምቦ ወረዳ መን/ኮሚ/ጉዳ/ጽ/ቤት

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/gimbogovtcommunicationaffairs
የቲክቶክ ቻናላችን
https://tiktok.com/
ይቀላቀሉ::

Address

Adis Ababa
Gimbo

Telephone

+251905651100

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gimbo Woreda Communication Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share