28/07/2023
በመተማ ወረዳ ዘውዴ ባድማ ንዑስ ቀበሌ የአካባቢውን ሰላም አስጠብቆ ለማስቀጠል ከኗራዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።
መተማ ሐምሌ:21፣2015 ዓ.ም በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ዘወዴ ባድማ ንዑስ ቀበሌ አካባቢውን ሰላም አስጠብቆ ለሞጠል ብሎም አጋች እና ሌባ በማስወገድ ህብረተሰቡ እንዴት በሰላም መኖር እንደሚችል ከኗሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል።
መድረኩ በአካባቢው የሚንቀሳቁ አጋችና ሌባ ለማስወገድ ህብረተሰቡ ተባባሪ እንዲሆን እና የአካባቢውን ሰላም ለማስፈን ያለመ ውይይት ነው።
ባለፉት አራት አመታት አካባቢያችን ብዙ ፈተናዎችን ያሳለፈ ሲሆን በወቅቱ ብዙ ዋጋ አስከፍሎና ከዚያ በኃላ አካባቢያችን ከህብረተሰባችን ጋር ተባብረን ሰላም ማድረግ ብንችልም አሁን ላይ ቀጠናችን ሰላም እንዳይሆን በሚፈልጉ አካላት እየተፈተነ እንደሚገኝ የመተማ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ሞገስ አስረድተዋል።
ከዚህ በፊት ጠላቶቻችን አማራና ቅማንት የሚል የብሔር ሽፋን በመስጠት ህብረተሰቡን ለችግር እንዳጋለጡት ያነሱት አስተዳዳሪው የነበረው ችግር እንዲደገም የሚፈልጉ አካላት በዕገታ ስም የብሔር ግጭት እንዲፈጠር እየጣሩ ይገኛሉ ብለዋል።
ሌባ እና ሽፍታ ብሔር የለውም ጥቅም ፈላጊ እንጂ ያሉት አስተዳዳሪው ህዝባችን ሊነቃ ይገባል፣ እርስ በእርስ ሊያበላሉን የተነሱትን ሀይሎች ላይ በጋራ ማፅዳት አለብን ብለዋል።
አካባቢያችን እንዴት ሰላም አድርገን አልምተን መጠቀም እንዳለብን የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶችና ወላጆች እንዲመክሩ የጠየቁት አቶ ደሳለኝ እኛ ለሰፊው ህዝብ ሲባል ከጥፋት ለሚመለሱ አካላት በራችን ክፍት ነው ብለዋል።
የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ደህንነት መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ጋሻው አለማየሁ እንደገለፁት ችግሮችን ከምንጩ ማምከን ምንችለው ሁላችንም እኩል ስራ መስራት ስንችል መሆኑን ተረድተን አጋችንና ሌባን ከምንጭ ለማድረቅ መነሳት አለበት ብለዋል።
ህብረተሰባችን ሌባ ጠል ሊሆን ይገባል ያሉት ም/ኃላፊው አንዷ ጣታችን ከተጎዳች እጃችን እንደሚጎዳው ሁሉ ህብረተሰባችን በትንሽ ፅንፈኛ አካላት ወደ ከፋ ችግር እንዳይገባ ከውስጡ ያሉትን
አረሞችን ሊያፀዳ ይገባል ብለዋል።
በቀጠናችን ባለፈው ጊዜ በተፈጠረው ችግር የደረሰበትን መፈናቀልና ጉዳት ልንረሳው አይገባም ያሉት አቶ ጋሻው ለአጋች ምግብና መረጃ የምታቀብሉ እና ሌባን የምታስጠጉ አካላት ከድርጊታችሁ ተቆጥባችሁ ለአካባቢያችን ሰላም የበኩላችሁን ልትወጡ ይገባል ብለዋል።
አካባቢያችን እየተፈተነ ያለው በትንሽ ጥቅመኞች ፍላጎት እንደሆን የተናገሩት የመተማ ወረዳ ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ ሞላ ህብረተሰባችን በመናበብ አስፈላጊውን መረጃ በመያዝ ስርዓት የሚይዘውን አካል ስርዓት ለማስያዝ ተቆራርጠን እየሰራን ነው ብለዋል።
ገበሬው አርሶ መብላትና ሰርቶ ልጆቹን ማሳደግ ይፈልጋል ትንንሽ ሀሳብ ባላቸው አጋቾች አካባቢያችን ሰላሙ ሊደናቀፍ አይገባም ብለዋል።
የጠላት አላማው ህብረተሰቡን እርስ በእርሱ በማጋጨት
ሰላምን በማደፍረስ እና የልማት እንቅስቃሴዎችን ማደናቀፍ ነው ያሉት ኃላፊው አካባቢውን በጋራ መታደግ አለብን ብለዋል።
በመድረኩ የተገኙት ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ስመኘው ጥጋቡ እኛ የምንፈልገው ሰላምና ልማት ነው፣ ሌባው የማን ቤተሰብ እንደሆነ ከማጋለጥ ባሻገር ከፀጥታ አካላት ጋር አስፈላጊውን ስምሪት በመወጣት አካባቢያችን እንጠብቃለን ብለዋል።
ሌላው የቀበሌው ነዋሪ አቶ ሻበል ጥጋቡ ነዋሪ እኛ ከመንግስት ጎን እንጅ ከሌባ ግንኙነት እንፈልግም ይኸን ሽፋን አድርጎ አማራ ቅማንት የሚል አንቀበልም ብለዋል።
በመጨረሻም በመድረኩ የተሳተፉት ነዋሪዎች አጋችና ሌባን ጨምሮ ተባባሪ፣ የመረጃና የስንቅ አቀባይ ናቸው ያሏቸውን አካላት አጋልጠዋል።
✅ መረጃው:የመተማ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ነው።