07/09/2026
ጳጉሜ 2 እየተከበረ ለሚገኘው የማንሰራራት ቀን አስመልክቶ የበየዳ ወረዳ አመራሮ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።
ጳጉሜ 2/2018 ዓ/ም በሃገር አቀፍ ደረጃ የማንሰራራት ቀን ተብሎ የተሰየመው ጳጉሜ 2 በበየዳ ወረዳ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎች ተጎብኝተዋል።
ጉብኝት ከተደረገባቸው የልማት ትሩፋቶች መካከል ለድልይብዛ ከተማ የተገነባው የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው። ከ15 ሺ በላይ ለሚገመት ነዋሪ ከ72 ሚሊየን ብር በላይ የፈጀ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑ የመስክ ምልከታ ተደርጎበታል።
ሌላው የድልይብዛ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርትቤት የተገነቡ የተማሪዎች መመገቢያ ግንባታዎች የተጎበኙ ሲሆን የሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነትና አልማ ወረዳው ላይ ለሚሰሩት ግንባታ አድናቆት ተችሮታል።
በረዳው ዋቲ ቀበሌ አምደወርቅ ተፋሰስ እየተመረተ የሚገኝ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ማር የጉብኝቱ አካል ነበር።