ሰሜን ጎንደር ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት North Gondar Zone Prosperity Party

  • Home
  • Ethiopia
  • Gondar
  • ሰሜን ጎንደር ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት North Gondar Zone Prosperity Party

ሰሜን ጎንደር ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት
North Gondar Zone Prosperity Party ኢትዮጵያ የብልፅግና ተምሳሌት ሀገር ለመሆን ቀን ከሌት እየሰራች ትገኛለች

ጳጉሜ 2 እየተከበረ ለሚገኘው የማንሰራራት ቀን አስመልክቶ የበየዳ ወረዳ አመራሮ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።   ጳጉሜ 2/2018 ዓ/ም በሃገር አቀፍ ደረጃ የማንሰራራት ቀን ተብሎ የተሰየመው ጳ...
07/09/2026

ጳጉሜ 2 እየተከበረ ለሚገኘው የማንሰራራት ቀን አስመልክቶ የበየዳ ወረዳ አመራሮ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።

ጳጉሜ 2/2018 ዓ/ም በሃገር አቀፍ ደረጃ የማንሰራራት ቀን ተብሎ የተሰየመው ጳጉሜ 2 በበየዳ ወረዳ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎች ተጎብኝተዋል።

ጉብኝት ከተደረገባቸው የልማት ትሩፋቶች መካከል ለድልይብዛ ከተማ የተገነባው የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው። ከ15 ሺ በላይ ለሚገመት ነዋሪ ከ72 ሚሊየን ብር በላይ የፈጀ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑ የመስክ ምልከታ ተደርጎበታል።

ሌላው የድልይብዛ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርትቤት የተገነቡ የተማሪዎች መመገቢያ ግንባታዎች የተጎበኙ ሲሆን የሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነትና አልማ ወረዳው ላይ ለሚሰሩት ግንባታ አድናቆት ተችሮታል።

በረዳው ዋቲ ቀበሌ አምደወርቅ ተፋሰስ እየተመረተ የሚገኝ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ማር የጉብኝቱ አካል ነበር።

የማንሠራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የመስክ ምልከታ ተካሄደ። ደባርቅ ፡- ዻጉሜ 02/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ የማንሠራራት ቀ...
07/09/2026

የማንሠራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ መሰረተ ልማቶች የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

ደባርቅ ፡- ዻጉሜ 02/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ የማንሠራራት ቀንን አስመልክቶ የተሰሩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በመጎብኘት ተከብሮ ውሏል፡፡

የማንሠራራት ቀን በወረዳው የተሰሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች በትምህርት ዘረፉ እና በሌሎች ተቋማቶች ላይ የሚስተዋሉ ዘረፈ ብዙ ችግሮችን ለመቅረፍ ፋይዳው የጎላ መሆኑን የዳባት ወረዳ መሬት ጽ/ቤት ኃላፊና ተወካይ አስተዳዳሪ አቶ አግንቸ ጌጡ ገልፀዋል፡፡

የማንሰራራት ቀን የተሻለ ነገን ለመፍጠር፣ ያጋጠሙ ችግሮች ለማረም እና በአዲስ አቅም ወደ ፊት ለመጓዝ የሚያነሳሳ ቀን መሆኑን ተወካይ አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡

የአፀደ ህፃናት ትምህርት ቤት ደረጃውን ጠብቆ መገንባቱ ተማሪዎች የተሻለ የትምህርት አቀባበል እንዲኖራቸውና በአቅራቢያቸው እንዲማሩ ለማስቻል ከፍተኛ ድርሻ አለው ብለዋል አቶ አግንቸ፡፡

የማንሠራራት ቀን በባለፉት የለውጥ ዓመታት የተሠሩ ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ ሀገራዊ የልማት ኢኒሼቲቮች፣ እና ሀገራዊ ማንሰራራትን የሚያሳይ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ክፍሌ አቡሃይ ገልፀዋል፡፡

በወረዳው እየተሰሩ ያሉ የመሰረተ ልማት ስራዎችን የመስክ ምልከታ በማድረግ የማንሠራራት ቀን ተከብሮ መዋሉ ተመላክቷል ፡፡

የማንሠራራት ቀን ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ! ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ...
07/09/2026

የማንሠራራት ቀን

ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!

ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ቀጥለዋል። ደባርቅ፡ ጳጉሜን 01/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲን...
06/09/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ቀጥለዋል።

ደባርቅ፡ ጳጉሜን 01/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን መቀበል ቀጥለዋል።

በወረዳው ከአሁን በፊትም በርካታ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለው መግባታቸው ይታወሳል። ዛሬም በወረዳው በምስራቁ ቀጠና ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 32 የሚሆኑ ተጨማሪ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል።

የሰላም አማራጭ የተቀበሉትን ታጣቂዎች የደባርቅ ወረዳ የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የሰላም አማራጭን የተቀበሉት ታጣቂዎች ሲጓዙበት የነበረው መንገድ የተሳሳተ መኾኑን መገንዘባቸውን ገልጸዋል። የነበሩበትን የጥፋት መንገድ በመተው ወደ ኅብረተሰቡ እና ሰላማዊ ሕይወት ለመመለስ መወሰናቸውንም አስታውቀዋል።

በሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር በተለያዩ ወረዳና ከከተማ አስተዳደሮች ጳጉሜ-1 የእመርታ ቀን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሃሳብ በልዩ ልዩ  መርሃ ግብሮችና ዝግጅቶች  ተከብሯል።   ...
06/09/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር በተለያዩ ወረዳና ከከተማ አስተዳደሮች ጳጉሜ-1 የእመርታ ቀን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሃሳብ በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮችና ዝግጅቶች ተከብሯል።

~•~•~•~•
🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ የጳጉሜን 1 የእምርታ ቀንን አስመልክቶ በሚሊገብሳ ቀበሌ  የልማት ጉብኝት ተደረገ።ደባርቅ፡ ጳጉሜን 01/2018 ዓ.ም በደባርቅ ወረዳ የጳጉሜን 1 የእምር...
06/09/2026

በሰሜን ጎንደር ዞን በደባርቅ ወረዳ የጳጉሜን 1 የእምርታ ቀንን አስመልክቶ በሚሊገብሳ ቀበሌ የልማት ጉብኝት ተደረገ።

ደባርቅ፡ ጳጉሜን 01/2018 ዓ.ም በደባርቅ ወረዳ የጳጉሜን 1 የእምርታ ቀን በዓል አስመልክቶ በተለይ የሃገራችን የማክሮ ኢኮኖሚ በውጤታማነት ለማከናወን የሚረዱ የግብርና ተግባራቶች በሚሊገብሳ ቀበሌ የወርቃምባ ተፋሰስ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ወጣቶች በንብ ማነብ ተደራጅተው የስራ እድል የተፈጠረላቸውንና በቀበሌው በክላስተር የለማውን 98 ሄክታር ቢራ ገብስ በወረዳው አመራሮች ጉብኝት ተደርጓል።

የቢራገብስ ልማት የምግብ ሉአላዊነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለጎንደር ብቅል ፋብሪካ ውጤታማነት አበርክቶው ከፍተኛ መሆኑን ጉብኝት ያካሄዱት አመራሮች አክለው ገልፀዋል።

‎  ቀን የእምርታ ቀን‎"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት"፤‎በሰሜን ጎንደር ዞን ‎የጃናሞራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የእምርታ ቀንን  በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን ምርጥ የሰብል ዝርያ ልማቶች ላይ...
06/09/2026

‎ ቀን የእምርታ ቀን
‎"ከተረጅነት ወደ ምርታማነት"፤

በሰሜን ጎንደር ዞን ‎የጃናሞራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የእምርታ ቀንን በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን ምርጥ የሰብል ዝርያ ልማቶች ላይ ጉብኝት አካሄደ።

‎የግርና ቤተሰቡና አርሶ አደሮች በተገኙበት በደረስጌ ቀበሌ በክላስተር እየለማ የሚገኘውን የሰብል ሁኔታ ጉብኝት ተደርጓል።

‎የሽዋ ባቄላ፣ራስ ባለ ስድስት ጠርዝ የቢራ ገብስ አባይና ቦሩ የተሻሻሉ የስንዴ ዝርያ ክላስተር የተጎበኘ ሲሆን የተሻለና ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ አኳያ ተስፋ ሰጭ የሰብል ዝርያ እንደሆኑ በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።

‎የተመረጡት የሰብል ዝርያዎቹ ፈጥነው የሚደርሱ በመሆኑ በአካባቢው ያለውን የአየር ንብረት ሊቋቋሙ የሚችሉ በመሆኑ በሰፊው መስራት እንደደሚገባ ተገልጿል።

የእምርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ተካሄዱ። ደባርቅ :- ጳጉሜን 01/2018 በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽቤት "የእምር...
06/09/2026

የእምርታ ቀንን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ተካሄዱ።

ደባርቅ :- ጳጉሜን 01/2018 በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ አስተዳደር ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽቤት "የእምርታ ቀንን" ምክንያት በማድረግ በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ውድድር በማካሄድ ፍፃሚያቸውን አግኝተዋል ።

በፍፃሜው ጨዋታ ንግግር ያደረጉት የደባርቅ ከተማ አስተዳደር ተወካይ ከንቲባና የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ስጦታው ታጀበ በክረምት ወራት ሲካሄዱ የቆዩት ስፖርታዊ ውድድሮች ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት ባሻገር ጤንነትን በመጠበቅ ጉልህ ሚና መጫወታቸውን ገልፀዋል።

በቀጣይም ስፖርቱን ለማሳደግ በተለያዩ የስፖርት አይነቶች የበጋ ውድድሮችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ ስጦታው ተናግረዋል።

በእለቱ በ13 አመት በታች የእግር ኳስ ጨዋታ ኢቫንጋዲ ከወንደማማቾች በነበረው ጨዋታ ኢቫንጋዲ የዋንጫና የሰባት ሺ ብር ተሸላሚ ሰሆን በ15 አመት በታች እግር ኳስ ውድድር ደግሞ በሰባ ደረጃና ማክቬል ተካሂዶ ሰባ ደረጃ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

ከጧቱ 4:00 ሰአት ጀምሮ በማክቤልና ቦልማ መካከል የተካሄደው የታዳጊዎች የፉት ሳል ውድድር ማክቬል ቦልማን 3ለ1 አሸንፎ የዋንጫ ተሸላሚ የሆነ ሲሆን በአዋቂዎች በቀይመስቀልና ምርጦቹ በተካሄደው የፉት ሳል ውድድር ጨዋታው ሁለት አቻ በመጠናቀቁ ምርጦቹ በመለያ ምት አሸንፈው የዋንጫ ተሸላሚ በመሆን የእለቱ ውድድር ተጠናቋል።

"በጀግንነት እንጠብቃለን፤ በሰብዓዊነት እናገለግላለን!"የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 አመታዊ ግምገማና የ2019 የእቅድ ትዉዉቅ አካሄዷል።ደባርቅ፦ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ...
06/09/2026

"በጀግንነት እንጠብቃለን፤ በሰብዓዊነት እናገለግላለን!"

የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 አመታዊ ግምገማና የ2019 የእቅድ ትዉዉቅ አካሄዷል።

ደባርቅ፦ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የ2018 አመታዊ የአፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 የእቅድ ትዉዉቅ መድረክ በዞኑ መቀመጫ ደባርቅ ከተማ አካሄዷል። በመድረኩም የዞን፣ የወረዳዎችና የከተሞች የፓሊስ አዛዦችና የማኔጅመንት አባላት ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ምህረት መለሰ የዞኑ ፖሊስ በ2018 ዓ.ም በርካታ ተግባራትን አከናውኗል። ጥሩ ዉጤትም አስመዝግቧል። ለዚህ ዉጤትም አባላት ተገብረዋል፤ የህይወት ዋጋ ተከፍሏል፣ በርካታ ፈተናዎችን አልፈን ዛሬ ላይ ላለንበት ደረጃ ደርሰናል።

2018 ዓ.ም ያለፈዉ የፖሊስ ሪፎርምን ተግባራዊ ከማድረግ ጎን ለጎን ህግ የማስከበር ስራዎችን ስናከናውን ቆይተናል ያሉት የፖሊስ አዛዡ ፖሊስ በሃገራችን ብሎም በክልላችን የተከሰተው የጸጥታ ችግር ሳይገድበዉ፦ ወንጀለኞችን አሳድዶ ለህግ በማቅረብ፣ ብሄራዊና ኃይማኖታዊ በዓላትን በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን፣ 7ኛዉን ሃገር አቀፍ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ፣ ብሄራዊና ክልላዊ ፈተናዎችን በብቃት የማስፈጸም፣ እንደባህል የሚቆጠረዉን የጥይት ተኩስ ማስቆም ተችሏል።

በተጨማሪም የወረዳ ቀበሌዎችን ከታጣቂዎች ነጻ የማዉጣት፣ በተወሰኑ ቀበሌዎች የኮሚዩኒቲ ፖሊሲንግ ማስተግበር፣ ለታጣቂ ኃይሎች ሊተላለፉ የነበሩ የምግብና የሎጀስቲክስ ቁሳቁሶች፣ የጦር መሳሪያዎችን ተከታትሎ መያዝና የማስቆም፣ ህገ ወጥ ተግባራትን (የመሬት ወረራ፣ ልቅ ግጦሽ፣ የጨረቃ ቤት) ስራዎችን የማስቆም ተግባራት መከናወናቸውን አብራርተዋል።

አሁን ላይ በተሰሩ ጠንካራ የህግ ማስከበር ተግባራት ፖሊስ ለህይወቱ ሳይሰስት ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት አብዛኞች ቀበሌዎች የአመራሮችና ባለሙያዎች ተንቀሳቅሰው አገልግሎት መስጠት መቻላቸውን ከበየዳ ወረዳ የመጡ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

በጃናሞራ ወረዳ ቀበሌዎች እስካሁን ታጣቂዎች ገብተዉ አያውቅም። ይህም ሊሆን የቻለው ከወረዳው የጸጥታ መዋቅር፣ ከአመራሩ እና ከማህበረሰቡ ጋር በመናበብ በቅንጅት በመሠራቱ ነዉ። ይሄንም አጠናክረን ማስቀጠል ይኖርብናል ሲሉ ከጃናሞራ ወረዳ የመጡ የፖሊስ አመራሮች ገልጸዋል።

የፖሊስ አባላትን መብትና ጥቅማቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል። ፖሊስ ህግ ለማስከበር የሚያግዝ ተሽከርካሪ ያስፈልጋዋል፤ በህብረተሰቡ የሚነዙ ሃሰተኛ መረጃዎች ተቋሙን የሚቀላቀሉ አባላት እንዳይፈጠሩ እንቅፋት ፈጥሯል፤ የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም ከመምሪያ ፖሊስ መኮንኖች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። የ2019 በጀት አመት የእቅድ ኦረንቴሽን ቀርቧል። የቀጣይ አቅጣጫ እና የስራ መመሪያ ተሰጥቷል።

06/09/2026

Address

Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰሜን ጎንደር ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት North Gondar Zone Prosperity Party posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share