30/04/2026
የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት ከUNDP ፕሮጀክት ድጋፍ የተገኘ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ አጸደቀ ።
ሚያዚያ22/2018ዓ.ም(ሐይቅ ኮሙዩኒኬሽን)
የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ በህወሀት ወረራ ጉዳት የደረሰባቸውን የማህበረሰብ ክፍሎችን መልሶ ለማቋቋም የሚያስችል ከUNDP ፕሮጀክት ድጋፍ የተገኘ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ ብር አጽድቋል።
ፕሮጀክቱ በከተማው በህውሀት ወረራ ወቅት የተለያየ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነልቦናዊ ጉዳት ለደረሰባቸው የማህበረሰብ ክፍሎች መልሶ ለማቋቋም ያለመ ሲሆን የተመደበው ገንዘብ ለግንባታ 41 ሚሊዮን713 ሺህ 4 64 ብር፣ለቀጥታ ድጋፍ 5 ሚሊዮን304 ሺህ ፣
ለግዥ 7 ሚሊዮን800 ሺህ ብርና
ለአቅም ግንባታ 9 ሚሊዮን 791 ሺህ 964 ብር
በጠቅላላ ድምር 64 ሚሊዮን606 ሺህ 428 ብር ጥቅም ላይ ለማዋል የታቀደ መሆኑን የሐይቅ ከተማ ገንዘብ ጽህፈት ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ ጌትነት ደረሰ ገልጸዋል።
አቶ ጌትነት አያይዘውም ከፕሮጀክቱ የተገኘውን ሀብት ለሚፈለገው አላማ በማዋል የማህበረሰባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በታቀደለት የጊዜ ገደብና በሚፈለገው ጥራት ለመስራት የሚመለከታቸው አካላት የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል ።
የሐይቅ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር መሃመድ በበኩላቸው ከፕሮጀክቱ የተገኘውን ሀብት ለሚፈለገው አላማ በማዋል የማህበረሰባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ሌላ ተጨማሪ ሀብት ለማግኘት የሚመለከተው አካል በፍትሀዊነት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል።
የሐይቅ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘገባ ነው