Haik ketema council office

Haik ketema council office ምክር ቤቶች የህዝብ ሉአላዊነት መገለጫ መድረኮች ናቸው

የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት  ከUNDP ፕሮጀክት  ድጋፍ የተገኘ ከ64 ሚሊዮን ብር   በላይ አጸደቀ ።ሚያዚያ22/2018ዓ.ም(ሐይቅ ኮሙዩኒኬሽን)የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ መደበኛ ጉባኤው ላ...
30/04/2026

የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት ከUNDP ፕሮጀክት ድጋፍ የተገኘ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ አጸደቀ ።

ሚያዚያ22/2018ዓ.ም(ሐይቅ ኮሙዩኒኬሽን)

የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ በህወሀት ወረራ ጉዳት የደረሰባቸውን የማህበረሰብ ክፍሎችን መልሶ ለማቋቋም የሚያስችል ከUNDP ፕሮጀክት ድጋፍ የተገኘ ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ ብር አጽድቋል።

ፕሮጀክቱ በከተማው በህውሀት ወረራ ወቅት የተለያየ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነልቦናዊ ጉዳት ለደረሰባቸው የማህበረሰብ ክፍሎች መልሶ ለማቋቋም ያለመ ሲሆን የተመደበው ገንዘብ ለግንባታ 41 ሚሊዮን713 ሺህ 4 64 ብር፣ለቀጥታ ድጋፍ 5 ሚሊዮን304 ሺህ ፣
ለግዥ 7 ሚሊዮን800 ሺህ ብርና
ለአቅም ግንባታ 9 ሚሊዮን 791 ሺህ 964 ብር
በጠቅላላ ድምር 64 ሚሊዮን606 ሺህ 428 ብር ጥቅም ላይ ለማዋል የታቀደ መሆኑን የሐይቅ ከተማ ገንዘብ ጽህፈት ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ ጌትነት ደረሰ ገልጸዋል።

አቶ ጌትነት አያይዘውም ከፕሮጀክቱ የተገኘውን ሀብት ለሚፈለገው አላማ በማዋል የማህበረሰባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በታቀደለት የጊዜ ገደብና በሚፈለገው ጥራት ለመስራት የሚመለከታቸው አካላት የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል ።

የሐይቅ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር መሃመድ በበኩላቸው ከፕሮጀክቱ የተገኘውን ሀብት ለሚፈለገው አላማ በማዋል የማህበረሰባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ሌላ ተጨማሪ ሀብት ለማግኘት የሚመለከተው አካል በፍትሀዊነት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የሐይቅ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘገባ ነው

የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት የ3ኛ ሩብ አመት መደበኛ ጉባኤውን አካሄደ ።ሚያዚያ 22/2018ዓ.ም(ሐይቅኮሙዩኒኬሽን) በጉባኤው  የሁለተኛ ሩብ አመት አጀንዳዎች ቀርበው ጸድቀዋል። የ3ኛ ሩብ አመ...
30/04/2026

የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት የ3ኛ ሩብ አመት መደበኛ ጉባኤውን አካሄደ ።

ሚያዚያ 22/2018ዓ.ም(ሐይቅኮሙዩኒኬሽን)

በጉባኤው የሁለተኛ ሩብ አመት አጀንዳዎች ቀርበው ጸድቀዋል። የ3ኛ ሩብ አመት የተቋማት፣ የቋሚ ኮሚቴዎች ሪፖርት እና የundp ፕሮጀክት እቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።

በመሆኑም የምክር ቤት አባላት በከተማ አስተዳደሩ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለው በከተማችን እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች በቆሻሻ ፣ በልቅ እንስሳትና ተልከስካሽ ውሻ እየተበላሹ በመሆኑ ለዚህ ችግር ማህበረሰቡና መንግስት በጋራ አፋጣኝ መፍተሄ ሊወስድ ይገባል፤ እንደ ከተማ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ፣ የሆስፒታል መግቢያ መንገድን ለመስራትና አላፊ የፌደራል መንገድን እንዲሰራ ጥያቄ ማቅረብን በተመለከተ ምን እየተሰራ ነው፤ በአለም አቀፍ ደረጃ የተፈጠረውን ቀውስ ተከትሎ የተፈጠረውን በነዳጅ አቅርቦት ችግር ምክንያት በትራንስፖርትና በመሰረታዊ ፍጆታ ሸቀጦችላይ ያለው የዋጋ ንረት የማህበረሰቡን ሸክም አክብዶታል ስለዚህ ችግሩን ለማቅለል የሚመለከተው አካል ምን እየሰራ ነው የሚሉና ሌሎች በርካታ ጉዳዬችን አንስተው በሚመለከታቸው የተቋም ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

የሐይቅ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር መሃመድ በማጠቃለያቸው ባለፈው ሩብ አመት የገቢ አሰባሰብን ጨምሮ ሌሎች በርካታ አመርቂ ተግባራትን ያከናወኑ መሆናቸውን ገልጸው በለጎ ሐይቅ ሪዞርት ዙሪያ እየለማ ያለውን የሙዝ ክላስተርን ማጠናከር፣በስራ እድል ፈጠራና በሸድ ግንባታ ላይ በቀሪ ወራቶች ያላሰለሰ ጥረት መደረግ እንዳለበት ጠቁመዋል።

በከተማው ያሉ የልማት ስራዎችን ከተሰሩ በኋላ ጠብቆ ከማቆየት አንጻር ማህበረሰቡ ደጋፊ ባለመሆኑ መዋቅሩ ከታች እስከ ላይ በቁርጠኝነት ሊሰራ ይገባል ያሉት አቶ ከድር ከአደባባይ እስከ ሪዞርቱ የሚሰራው የመንገድ ፕሮጀክት መሳካት የአካባቢው ማህበረሰብ፣ ተቋማትና አጋር አካላት ለነበራቸው ቀናነት አመስግነው በዚህ ፕሮጀክት የተነሱ የልማት ተነሽ ግለሰቦችና ተቋማት የሚገባቸውን ትክ ቦታና ካሳ ለመስጠት ዝግጅችንን ጨርሰናል ብለዋል።

መንግስት ለነዳጅ አቅርቦት እያደረገ ያለውን ጥረት ተከትሎ እየታዩ ያሉ የታሪፍ ጭማሬና የሸቀጦችን የዋጋ ንረት ወደ ነበረበት ለመመለስ የሚመለከተው አካል ጥብቅ ቁጥጥር በማድረግ የገበያ ማረጋጋት ስራው በትኩረት መሰራት እንዳለበት አንስተዋል።

አስከትለውም በundp ፕሮጀክት የተገኘውን ሀብት ለሚፈለገው አላማ በማዋል የማህበረሰባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና ሌላ ተጨማሪ ሀብት ለማግኘት የሚመለከተው አካል በፍትሀዊነት መስራት እንዳለበት አቶ ከድር አሳስበዋል።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እውን ለማድረግ የምርጫ ካርድ በማውጣት ሂደቱ ላይ የታየውን ርብርብ ምርጫውም ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የምክር ቤት አባሉ ፣ መላ ማህበረሰባችንና የጸጥታ ኃይላችን ያላሰለሰ ጥረት ሊያደርጉ ይገባል ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም የሐይቅ ከተማ አፈ ጉባኤ አቶ ግርማ ሞገስ በቀጣይ ተቋማት የሚፈጽሟቸውን የውሳኔ ሀሳቦች አስቀምጠው ጉባኤው ተጠናቋል።

የሐይቅ ከተማ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘገባ ነው

30/04/2026
20/04/2026
ቀን 12/08/2018እየተሰራ ያለው የኮሪደር ስራ የሐይቅ ከተማን ገፅታ የሚቀይር ነው ተባለ።የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ዛሬ በሐይቅ ከተማ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የልማ...
20/04/2026

ቀን 12/08/2018
እየተሰራ ያለው የኮሪደር ስራ የሐይቅ ከተማን ገፅታ የሚቀይር ነው ተባለ።
የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች ዛሬ በሐይቅ ከተማ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች በጎበኙበት ወቅት በከተማዋ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ስራ የከተማዋን ገፅታ የሚቀይርና ከተማዋ የቱሪስ መዳረሻ ለማድረግ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥርና ለኗሪዎቿ ምቹና ፅዱ ከተማ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል። ከተማ አስተዳደሩ ሙሉበሙሉ በራስ አቅም የኮሪደር ልማቱን ማከናወኑ የሚሰበስበውን ሀብት በጥንቃቄ ማስተዳደር መቻሉንና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉት ተግባራት ላይ የማዋል አቅሙን ከፍተኛ መሆኑን ማሳያ በመሆኑ ህብረተሰቡ ልማቱን በኔነው ስሜት ሊጠብቅና ሊንከባከብ ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም ቋሚ ኮሚቴው ከአደባባይ እስከ ገበታ ለሀገር ያለውን የመንገድ ስራ የጎበኘ ሲሆን ተቋራጭ ድርጅቱ ስራውን በተሻለ ፍጥነትና ጥራት እየሰራ መሆኑ አረጋግጠው ለቀጣይ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊስተካከሉ ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች የከተማና ተመሰረተ ልማት ፅ/ቤት ከተቋራጩ ድርጅት ጋር ተቀናጅቶ ሊሰራ ይገባል ያሉ ሲሆን ሳትኮን ኮንስትራክሽን ቀቀዋ ት/ቤት ጀርባ የሰራው የመንገድ ጠረጋና ድልድይ ስራ የማህበረሰቡን ጥያቄ የሚመልስና የመልካም አስተዳደር ችግርን የሚፈታ በመሆኑ ምስጋና በማቅረብ ጉብኝቱን አጠናቋል ።

አንድ ድምፅ ዋጋ አለዉ። ዋጋ ለአለው ድምፃችን ቀድመን እንመዝገብምርጫ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መሠረት ሲሆን፣ የዜጎች ነፃነትና መብት  የሚገለጽበት ዋነኛ መድረክ ነው። ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ...
02/04/2026

አንድ ድምፅ ዋጋ አለዉ።
ዋጋ ለአለው ድምፃችን ቀድመን እንመዝገብ

ምርጫ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መሠረት ሲሆን፣ የዜጎች ነፃነትና መብት የሚገለጽበት ዋነኛ መድረክ ነው።

ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ብቻ ሳይሆን ሕዝቡ የሥልጣን ባለቤት መሆኑን የሚያረጋግጥ ሕጋዊ ውል ነው።

ዜጎች በነፃነት የሚሰጡት ድምፅ የሀገሪቱን የወደፊት እጣ ፋንታ ይወስናል።

የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ ስኬታማ እንዲሆን የእያንዳንዱ ዜጋ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው። ንቁ ተሳትፎው የሚጀምረው የምርጫ ካርድ ከማውጣት ነው ።

የባሕር በር፦ አይቀሬው እውነታ!************** የግሎባላይዜሽን ትርክት ዓለም ላይ የበላይ በነበረበት በ20ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ እና በ21ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ "ዓለም ...
31/03/2026

የባሕር በር፦ አይቀሬው እውነታ!
**************

የግሎባላይዜሽን ትርክት ዓለም ላይ የበላይ በነበረበት በ20ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ እና በ21ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ "ዓለም ጠፍጣፋ ናት" የሚል ትርክትን አንግሦ ነበር።

ቴክኖሎጂ እና ጥሪት እንጂ የውኃ ዳርቻዎችንና ስትራቴጂክ ስፍራዎችን መቆጣጠር ዋጋ ቢስ ነው የሚል፤ የመልክአ-ምድርን አስፈላጊነት ያዳከሙት መስሎ ታይቶ ነበር።

ሆኖም ዛሬ ዓለም በታላላቅ ኃይላት ፍጥጫና በጂኦ-ፖለቲካዊ ፉክክር ውስጥ ስትወድቅ፣ ያ የቆየው እውነት ዳግም አገርሽቷል፦ "መልክአ-ምድር ዕድል ፈንታ ነው!"።

የአህጉራትና የሀገራት የጂኦ-ፖለቲካ ዕጣ ፈንታ ብዙ ጊዜ የሚወሰነው በባሕር ጠረፎችና ሞገዶች ላይ ባላቸው ቁጥጥርና ተፅዕኖ ነው።

የባሕር በር ያጡ ወይም ለማግኘት የጣሩ ሀገራት የወሰዷቸው እርምጃዎች ከባሕር ተነጥላ ኖራ ለማታውቀው ኢትዮጵያ ብዙ ቁም ነገር ይነግሯታል።

ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄን ስታነሳ በባዶ እጇ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ ያላት ስልታዊ አቀማመጥ፣ ግዙፍ የሰው ኃይልና እያደገ ያለው ኢኮኖሚ የራሳቸውን የመደራደር አቅም ይፈጥራሉ።

የማይቀረው አድማስ

የዓለም ታሪክ በግልጽ እንደሚያሳየው፣ 130 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት፣ ጥንታዊ የባሕር ሥልጣኔ ባለቤት የሆነችና በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ያለ ኢኮኖሚ ያላት ሀገር ከባሕር ተገልላ ልትኖር አትችልም።

ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር መመለሷ ለሌሎች ሥጋት ሳይሆን፣ የታሪክ ሚዛንን ማስተካከልና የአፍሪካ ቀንድን ወደ ብልፅግና ማዕከልነት የሚቀይር እርምጃ ነው። ባሕር የኢትዮጵያ ተፈጥሮአዊ ድንበር ነው፤ ወደ ባሕር ዳርቻዋ መመለሷም ብሩህ ለሆነው የወደፊት ጉዞዋ የማይቀሬ እርምጃ ነው።

ሙሉውን ዘገባውን በአስተያየት መስጫ ውስጥ ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ፤

በአዶኒያስ ወልደአረጋይ

ከ28 ሚሊዮን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል!ባሕር ዳር፡ መጋቢት 21/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ መጋቢት 18 ድረስ ከ28 ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ...
30/03/2026

ከ28 ሚሊዮን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል!

ባሕር ዳር፡ መጋቢት 21/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እስከ መጋቢት 18 ድረስ ከ28 ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡

ከተመዝጋቢዎቹ መካከል 15 ሚሊዮን 317 ሺህ 567ቱ ወንዶች ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 13 ሚሊዮን 47 ሺህ 743ቱ ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ተመልክቷል።

እርስዎስ ካርድዎን ቀድመው ይዘዋል? በጊዜ በመመዝገብ ድምጽወት ዋጋ እንዳታጣ ያድርጉ!
#ምርጫ #ኢትዮጵያ #ሰላም #አሚኮ

የአሚኮ ዘገባ ነው

ባሕር ዳር ፡- መጋቢት 18/2018ዓ.ም    የአፈ-ጉባዔና የምክትል አፈ-ጉባዔ አመራረጥ(1) በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 3 (4)መሠረት ምክር ቤቱን የሚመሩ አፈ-ጉባዔና ምክ...
29/03/2026

ባሕር ዳር ፡- መጋቢት 18/2018ዓ.ም

የአፈ-ጉባዔና የምክትል አፈ-ጉባዔ አመራረጥ

(1) በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 3 (4)መሠረት ምክር ቤቱን የሚመሩ አፈ-ጉባዔና ምክትል አፈ-ጉባዔ በምክር ቤቱ ይመረጣሉ፡፡

(2) አፈ-ጉባዔው የሚመረጠው በምክር ቤቱ የሥራ ዘመን መጀመሪያ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተወካይ ወይም በቀድሞው ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ወይም በቀድሞው ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባዔ የመድረክ መሪነት በሚመረጡ አስመራጭ ኮሚቴዎች ይሆናል፡፡

(3) የአፈ-ጉባኤው አመራረጥ በሚከተለው አኳኋን ይፈፀማል፡-

ሀ) ማንኛውም አባል እጩ አፈ-ጉባዔ መጠቆም ይችላል፣ ሲጠቁምም እጩውን በተመለከተ አጭር ማብራሪያ ማቅረብ ይኖርበታል፤
ለ) አንድ በእጩነት የተጠቆመ አባል በሌላ አንድ አባል መደገፍ ያለበት ሲሆን በአባላት 1/3ኛ ድምፅ ከተደገፈ በእጩ ተወዳዳሪነት ይመዘገባል፤
ሐ) ማንኛውም አባል ከአንድ እጩ በላይ መጠቆም ወይም እጩ ሆኖ እንዲቀርብ ድጋፍ መስጠት አይችልም፤
መ) የተጠቆሙ እጩዎች ስም ዝርዝር በፊደል ተራ ይመዘገባል፤ በዚሁ ቅደም ተከተል መሠረትም ድምፅ ይሰጣል፤
ሠ) የተወዳዳሪ ዕጩዎች ብዛት ከሶስት የማይበልጥ ሆኖ፤ ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል አብላጫ ድምፅ ያገኘ እጩ አባል አፈ-ጉባዔ ይሆናል፤
ረ) በተደረገው ምርጫ አብላጫ ድምፅ ያገኘ እጩ ከሌለ ከተሰጠው ድምፅ ውስጥ ከአስር በመቶ በታች ያገኘ ወይም ውጤቱ ከተገለፀ በኋላ ወዲያውኑ ራሱን ያገለለ እጩ ከውድድር ውጭ ሆኖ በቀሩት እጩዎች መካከል አንድ እጩ አብላጫ ድምፅ እስኪያገኝ ድረስ ምርጫው ይቀጥላል፤
ሰ) በእጩነት የቀረበው አንድ አባል ብቻ ቢሆንም የምክር ቤቱን አብላጫ ድምፅ ማግኘት
ይኖርበታል፤ ድምፅ አሰጣጡም እጅ በማውጣት ይከናወናል፤
ሸ) ከአንድ በላይ እጩ ሲቀርብ ምርጫው በሚስጥር ድምፅ አሰጣጥ ይከናወናል፡፡

(4) በዚህ አንቀፅ በንዑስ አንቀፅ (3) መሠረት የተመረጠው አፈ-ጉባዔ በመድረኩ ይገለፃል፣ የአፈ- ጉባዔነት ወንበሩን እንዲይዝም ይደረጋል፡፡

(5) የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ በሚሰጠው መመሪያ መሠረት ጽሕፈት ቤቱ የሚከተሉትን ተግባራት ያከናውናል፡-
ሀ) በዚህ አንቀፅ በንዑስ አንቀፅ (3) መሠረት እጩ ይመዘግባል፣
ለ) ለምርጫ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ያዘጋጃል፣ የድምፅ መስጫ ካርድ ያሰራጫል፣ ያሰባስባል፣ ይቆጥራል፣ ውጤቱንም ለመድረኩ መሪ ያሳውቃል፣
ሐ) ድምፅ የተሰጠባቸውና ግልፅ ያልሆኑ ወይም ለምርጫው ከተቀመጡ አሠራሮች ውጭ ድምፅ የተሰጠባቸው ካርዶች ሲያጋጥሙ በአስመራጭ ኮሚቴው ውሳኔ እንዲያገኙ ያደርጋል፡፡

(6) በዚህ አንቀፅ የተደነገገው የአፈ-ጉባዔ የአመራረጥ ሥርዓት ለምክትል አፈ-ጉባዔ አመራረጥም ተፈፃሚ ይሆናል፣ ይሁን እንጂ መድረኩ የሚመራው በአፈ-ጉባዔ ይሆናል፡፡

(7) የምክር ቤቱ የሥራ ዘመን ከማለቁ በፊት አፈ-ጉባዔው ወይም ምክትል አፈ-ጉባዔው በተለያዩ ምክንያቶች ሥራቸውን ቢለቁ በሥራ ላይ ባለው አፈ-ጉባዔ ወይም ምክትል አፈ-ጉባዔ መሪነት በዚህ አንቀፅ በተቀመጠው አሠራር መሠረት ከምክር ቤቱ አባላት መካከል እንዲመረጥ ይደረጋል፡፡

(8) የምክር ቤቱ የሥራ ዘመን ከማለቁ በፊት በተለያዩ ምክንያቶች አፈ-ጉባዔ እና ምክትል አፈ-ጉባዔው በአንድ ጊዜ ሥራቸውን ቢለቁ በዚህ ደንብ በአንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ (3) በተደነገገው መሠረት ምርጫው ይካሄዳል፡፡

-

ባሕር ዳር፡- መጋቢት 16/ 2018ዓ.ም አማራ ክልል ም/ቤትየምክር ቤቱ ዋና ዋና ሥልጣን እና ተግባራትምክር ቤቱ በብሔራዊ ክልሉ ሕገ-መንግሥት የተዘረዘሩት ሥልጣንና ተግባራት ያሉት ሲሆን ዋ...
25/03/2026

ባሕር ዳር፡- መጋቢት 16/ 2018ዓ.ም አማራ ክልል ም/ቤት
የምክር ቤቱ ዋና ዋና ሥልጣን እና ተግባራት
ምክር ቤቱ በብሔራዊ ክልሉ ሕገ-መንግሥት የተዘረዘሩት ሥልጣንና ተግባራት ያሉት ሲሆን ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡-
ሀ) ሕግ ማውጣት፤
ለ) መንግሥታዊ አካላትን መከታተል፣ መቆጣጠር፣የሥራ ኃላፊዎችን ለጥያቄ ይጠራል፣
አሠራራቸውን ይመረምራል፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘውም እርምጃ ይወስዳል ወይም ያስወስዳል፤
ሐ) የራሱን የተለያዩ ኮሚቴዎችና ሌሎች አስፈላጊ ክፍሎችን ያቋቁማል፣ ያደራጃል፤
መ) በምክር ቤቱ የሚሰየሙ፣ የሚሾሙ እና የሚመረጡ የክልሉ መንግሥት ባለሥልጣናትን መሰየም፣ መሾም፣ ማፅደቅ፣ መምረጥ እና መሻር፣
ሠ) አባላት ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር እንዲገናኙ ሁኔታዎችን ያመቻቻል እንዲሁም የወከለውን
ሕዝብ ፍላጎት እና ጥቅም ለማስጠበቅ የሚፈለግበትን ሌሎች ግዴታዎች ይወጣል፣
ረ) ሌሎች የምክር ቤቱ ሥልጣን የሆኑ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
ምክር ቤቱ ተግባራቱን ሲያከናውን የሚከተሉትን አጠቃላይ መርሆዎች መሠረት በማድረግ ይሆናል፡-
ሀ) በዕቅድ በመመራት ውጤታማነቱን በማረጋገጥ፤
ለ) ለተግባራቱ ውጤታማነት የሚረዳ ምቹ የሥራ ሁኔታን በመፍጠር፤
ሐ) የግልፅነት፣ የተጠያቂነትና የአሳታፊነት መርሕን በመከተል፤
መ) የአብላጫ ድምጽ በማክበር እና አነስተኛ ድምጽ እንዲሰማ በማድረግ፣ ተግባራትን በመገምገም፤
ረ) ተግባራትን በቡድንና በትብብር በማከናወን፤
ሰ) ሌሎች የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን በመከተል ይሆናል::
(3) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) የተዘረዘሩት መርሆዎች እንደሁኔታው ለኮሚቴ ተጣጥመው ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡

ስለ ምክር ቤቱ የሥራ ዘመን
(1) በሕገ-መንግሥቱ አንቀፅ 48(1) እና 54 (3)መሠረት የምክር ቤቱ የሥራ ዘመን አምስት ዓመት ነው፡፡
(2) በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 54(1) መሠረት የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ቢያንስ በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከናወን ይሆናል፤
(3) የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ካልተለወጠ በስተቀር፡-
ሀ) በጥቅምት ወር፣
ለ) በየካቲት ወር እና
ሐ) ከሠኔ ወር መጨረሻ እስከ ሐምሌ ወር መጀመሪያ ሳምንት ባለው ጊዜ ውስጥ ይካሄዳል::
(4) የምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ በማናቸውም ጊዜ ሊካሄድ ይችላል፡፡

በቀጣይ የምክር ቤቱ የሥራና የእረፍት ጊዜያትን እናጋራለን፡፡

ቀን 16/07/2018ዓ.ምሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠል ሁሉም ሃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ።የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት ለሴት የምክር ቤት አባላትና የቋሚ ኮሚቴ ተሰብሳቢዎች ስለ 7ተኛው ሀገራዊ ...
25/03/2026

ቀን 16/07/2018ዓ.ም
ሀገርን እንደ ሀገር ለማስቀጠል ሁሉም ሃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ።
የሐይቅ ከተማ ምክር ቤት ለሴት የምክር ቤት አባላትና የቋሚ ኮሚቴ ተሰብሳቢዎች ስለ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የሴቶች ተሳትፎ በተመለከተ ውይይት ባደረጉት ወቅት ሴት የምክርቤት አባላት ምርጫው ፍትሃዊ ፣ነፃና ሁሉን የህብረተሰብ አካል አካታች እንዲሆን እንሰራለን ።ሀገር እንደ ሃገር እንዲቀጥል ሁሉም ዜጋ የምርጫ ካርዱን በማውጣት ይሆነኛል የሚለውን የፓለቲካ ፓርቲ ወይም ተወዳዳሪ በመምረጥ ሃላፊነቱ ሊወጣ ይገባል ። እኛም እንደዜጋ የመምረጥ እና የመመረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታችን በመጠቀም ካርዳችንን በማውጣት ለሌሎች አርአያነታችንን እንወጣለን ብለዋል ።

23/03/2026

Address

Ethiopia Amhara Region
Haik

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haik ketema council office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share