Haik ketema council office

Haik ketema council office ምክር ቤቶች የህዝብ ሉአላዊነት መገለጫ መድረኮች ናቸው

06/08/2026

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን ነገ ሀምሌ 23 እንደሚጀምር ተገለጸ።

​የአማራ ክልልምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፋንቱ ተስፋዬ 6ኛ ዙር 5ኛ የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባዔን አሰመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል ።

አፈጉባዔዋ በመግለጫቸው የ2018 በጀት ዓመት የአስፈፃሚ አካላት እቅድ ክንውን፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የዋና ኦዲተር የእቅድ አፈፃፀሞች ቀርበው በውይይት እንደሚጸድቁ ተናግረዋል ።
በተጨማሪም በባለፈው ዓመት ጥቅም ላይ የዋለው ተጨማሪ በጀት ቀርቦ እንደሚጸድቅ በመግለጫው አንስተዋል ።

በጉባዔው የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ የበጀት እቅድ ቀርቦ በውይይት እንደሚጸድቅም ጠቁመዋል ።
ጉባዔው የመጨረሻ ጉባዔ በመሆኑ የ6ኛው ዙር የሥራ ዘመን ምክር ቤቱ በአምስት ዓመታት ያከናወናቸውን ጥቅል ተግባራት ሪፖርት ቀርቦ የሚገመገምበት መሆኑን አንስተዋል ።
የክልሉ የልማት እና የመልካም አሥተዳደር ሥራዎችን በተመለከተም ውይይት ይደረጋል ብለዋል ።
ምክር ቤቱ ባለፉት 5 ዓመታት ሕግ የማውጣት፣ የክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም የሕዝብ ውክልና ኃላፊነቱን ሲወጣ
መቆየቱን አንስተዋል ።
የሕዝቡን የመልማት፣ የፍትሕና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችሉ 32 አዋጆች፣ ሁለት ደንቦች እና ሁለት ሞሽኖች ጸድቀው ሥራ ላይ መዋላቸውንም ገልፀዋል ።

06/08/2026

Address

Ethiopia Amhara Region
Haik

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Haik ketema council office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share