ሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት

ሀራ ከተማ  አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ፅህፈት ቤት ኦፊሻል የፌስቡክ ገፅ ነው።

የሀራ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በሐሙስ ገበያ ላይ የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ  እየሰራ ነው፤ሀራ፣ ሐምሌ ፣9፣ 2018 ዓ.ም – የሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በከ...
16/07/2026

የሀራ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በሐሙስ ገበያ ላይ የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እየሰራ ነው፤
ሀራ፣ ሐምሌ ፣9፣ 2018 ዓ.ም – የሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት በከተማዋ ትልቁ የገበያ ማዕከል በሆነው “ሐሙስ ገበያ” ላይ የተቀናጀ የቁጥጥርና የክትትል ስራ እያከናወነ ነው።

ጽ/ቤቱ የሸማቹን ማህበረሰብ ጤንነት ከመጠበቅ ባሻገር፣ ህጋዊ የንግድ ስርዓትን ለማስፈን ባደረገው በዚህ የአሰሳ ስራ በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጿል። በቁጥጥር ስራው ወቅት የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ለጤና ጎጂ የሆኑ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡ ጥብቅ ክትትል የተደረገ ሲሆን፣ የህግ ጥሰት ፈጽመው የተገኙ ምርቶች ከገበያው እንዲወገዱ ተደርጓል።

በተጨማሪም፣ የንግድ ፈቃድ ሳይኖራቸው የንግድ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበሩ አካላት ከገበያው እንዲወገዱ በማድረግ፣ የዘርፉን ህጋዊነት የማስከበር ስራ ተሰርቷል። ይህ እርምጃ ህጋዊ ግዴታቸውን እየተወጡ የሚሰሩ ነጋዴዎችን ተወዳዳሪነት የሚያረጋግጥና የሸማቾችን መብት የሚያስጠብቅ መሆኑን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ያሲን ሙሐመድ ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅት በተከናወነው የቁጥጥር ስራ አማካኝነት በገበያው ላይ የተሻለ የምርት አቅርቦት መፈጠሩና የንግድ እንቅስቃሴውም በህጋዊ ማዕቀፍ ውስጥ እየተመራ መሆኑን የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች ገልጸዋል።

ጽ/ቤቱ በቀጣይም የህገ-ወጥ ንግድ እንቅስቃሴዎችን ለመከላከልና የገበያ ስርዓቱን ለማዘመን የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል። ሸማቾችም በገበያ ወቅት የገዙትን ምርት የጥራት ምልክትና የአገልግሎት ጊዜ መፈተሽ እንደሚገባቸው ጽ/ቤቱ መልእክቱን አስተላልፏል።

ሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት

የንግድ ፈቃድ እድሳት የ2019 በጀት ዓመት የንግድ ፈቃድ እድሳት ከነገ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚከናወን መሆኑን እንገልጻለን።
07/07/2026

የንግድ ፈቃድ እድሳት

የ2019 በጀት ዓመት የንግድ ፈቃድ እድሳት ከነገ ከሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚከናወን መሆኑን እንገልጻለን።

በሀራ ከተማ አስተዳደር "ህጋዊ፣ ተደራሽ እና ዘመናዊ የንግድና ግብይት ስርአት እንገነባለን" በሚል መሪ ቃል የንግድ ቀን ተከበረ በሀራ ከተማ አስተዳደር "ህጋዊ፣ ተደራሽ እና ዘመናዊ የንግድ...
03/07/2026

በሀራ ከተማ አስተዳደር "ህጋዊ፣ ተደራሽ እና ዘመናዊ የንግድና ግብይት ስርአት እንገነባለን" በሚል መሪ ቃል የንግድ ቀን ተከበረ

በሀራ ከተማ አስተዳደር "ህጋዊ፣ ተደራሽ እና ዘመናዊ የንግድና ግብይት ስርአት እንገነባለን" በሚል መሪ ቃል የንግድ ቀን በድምቀት ተከብሯል። በዕለቱ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና የንግዱ ማህበረሰብ የተገኙ ሲሆን፣ የንግድ ስርአቱን ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የመወያያ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ኢንጂነር ሙሐመድ ሰኢድ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር የከተማዋን የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግ የንግዱን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርግ እና ህጋዊ የሆነ የንግድ እንቅስቃሴ መፍጠር ውይይቱ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባው አያይዘውም፣ የንግድ ስርዓቱን ግልጽነት ባለው መልኩ ለማዘመን አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የሀራ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈንታው በበኩላቸው፣ የንግድ ስርዓት መዘመን ለከተማዋ አጠቃላይ ልማት ያለው ሚና የላቀ መሆኑን ጠቅሰው፣ የንግድ ማህበረሰቡ በህጋዊ መስመር በመንቀሳቀስ ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ የበኩሉን ሚና ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያሲን ሙሐመድ በበኩላቸው በከተማዋ ያለውን የንግድ እንቅስቃሴ ከህገ-ወጥነት ነጻ ለማድረግ፣ የገበያ መረጃን ተደራሽ ለማድረግ እና ዘመናዊ የግብይት ስርአቶችን ተግባራዊ ለማድረግ ጽ/ቤቱ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በውይይቱ ላይ የታደሙ የንግዱ ማህበረሰብ ተሳታፊዎች የንግድ ስርአቱን ለማዘመን የሚደረገውን ጥረት ሙሉ በሙሉ እንደሚደግፉ እና ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

በመጨረሻም በበጀት ዓመቱ ለንግድ ስርአቱ አስተዋጽኦ ያደረጉ ለአጋርና ለባለድርሻ አካላት እውቅና በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

የሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት የ11 ወራት የስራ አፈጻጸም ተገመገመ፤ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሱፐርቪዥን ቡድን በሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማ...
24/06/2026

የሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት የ11 ወራት የስራ አፈጻጸም ተገመገመ፤

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሱፐርቪዥን ቡድን በሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት በመገኘት፣ የቢሮ እና የመስክ ምልከታ አደረገ፤

የሱፐርቪዥን ቡድኑ በጽህፈት ቤቱ ቆይታው የ11 ወራት የስራ አፈጻጸምና የእቅድ ክንውንን ዝርዝር ግምገማ ያካሄደ ሲሆን፤ በመስክ ምልከታው ደግሞ የመደበኛ ገበያዎችን፣ የህብረት ስራ ሸማቾች ማህበራትን እና የነዳጅ ማደያዎችን ተዘዋውሮ በመመልከት ነባራዊ ሁኔታውን ገምግሟል።

በግምገማው የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ አስተያየታቸውን የሰጡት የቡድኑ አባላት፣ ጽህፈት ቤቱ በምልከታው የታዩትን ጥንካሬዎች በማስፋትና ድክመቶችን ደግሞ ለቀጣዩ በጀት ዓመት ማስተካከል እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በመጨረሻም የሱፐርቪዥን ቡድኑ ከሀራ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈንታው በለጠ ጋር በመሆን፣ የጽህፈት ቤቱን አጠቃላይ የስራ አፈጻጸምና የመስክ ምልከታውን የገመገሙ ሲሆን፤ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ጉዳዮች ላይም ውይይት ተደርጓል።

ሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት
የአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ Amhara Trade And Market Development Bureau

19/06/2026

የኢትዮጵያ ወደ ቱርክ የሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ ገቢ በ35 በመቶ በላይ አድጓል።

(አዲስ አበባ ፡ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም) ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ ከ2021 እስከ 2025 ባሉት አምስት ዓመታት ወደ ቱርክ ኤክስፖርት ካደረገቻቸው ምርቶች ያገኘችው ገቢ በአማካኝ በ35 ነጥብ 64 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል፡፡

የሀገሪቱ የወጪ ንግድ ገቢ እ.ኤ.አ በ2022 ካጋጠመው ጊዜያዊ መቀዛቀዝ በፍጥነት በማገገም፣ ከ2023 እስከ 2025 ባሉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት ተስፋ ሰጪ እና ቀጣይነት ያለው አስደናቂ ዕድገት ማስመዝገብ ችሏል።

በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ በ2021 ወደ ቱርክ ከላከቻቸው ምርቶች ካገኘችው 46 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ዓመታዊ ገቢ በመነሳት፣ በ2025 ይህንን አፈጻጸም ከ103 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማሳደግ ችላለች።

በአምስት ዓመታቱ አጠቃላይ አፈጻጸም ኢትዮጵያ ወደ ቱርክ የተለያዩ ምርቶችን በመላክ በአጠቃላይ 298 ሚሊዮን 430 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ገቢ ያገኘች ሲሆን፣ ይህም በአማካይ በየዓመቱ የ59 ሚሊዮን 686 ሺህ ዶላር የወጪ ንግድ ምርት መላኳን ያሳያል።

ይህ ቀጣይነት ያለው የዕድገት ጉዞ እ.ኤ.አ በ2024 በ67 ነጥብ 60 በመቶ ጭማሪ በማሳየት ዓመታዊ ገቢውን ወደ 77 ሚሊዮን 663 ሺህ ዶላር ያሳደገው ሲሆን፣ በ2025 ደግሞ ዕድገቱ የ33 ነጥብ 56 በመቶ ተጨማሪ ጭማሪ በማስመዝገብ ዓመታዊውን ገቢ ከ103 ሚሊዮን 547 ሺህ ዶላር በላይ እንዲደርስ አድርጎታል።

በዚህ የወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ከፍተኛውን የገቢ ድርሻ የያዙት የኢትዮጵያ ምርቶች የቅባት እህሎች፣ ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶች፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የአትክልት ውጤቶች፣ ጨርቃጨርቅ እና አልባሳት ናቸዉ።

19/06/2026
29/05/2026

አዲሱ የንግድ ፖሊሲ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መሠረት ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት የተደረጉ የንግድ ዘርፎችን ሪፎርም ያጠናክራል።
* * * * * *
በሚኒስትሮች ምክር ቤት የፀደቀው አዲሱ የንግድ ፖሊሲ፣ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መሠረት ቀደም ሲል ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩትን የገቢ፣ የወጪ፣ የጅምላና የችርቻሮ ንግድ ሥራዎችን ለውጭ ባለሀብቶች ለመክፈት የተጀመረውን የሪፎርም ሥራ ይበልጥ እንደሚያጠናክር ተገልጿል።

የውጭ ባለሀብቶች በእነዚህ የንግድ ዘርፎች ላይ እንዲሳተፉ መፍቀድ ለአገር ውስጥ አምራቾች ሰፊ የገበያ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፣ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግርን ለማስፋፋት፣ በጥራት የማምረትን አቅምና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ እንዲሁም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ የጎላ ጥቅም ያስገኛል።

በተመሳሳይ ሁኔታ የውጭ ባለሀብቶች በገቢ፣ ወጪ፣ ጅምላና ችርቻሮ ንግድ ሥራዎች ላይ መሰማራታቸው ለሸማቾች ሰፊ አማራጭን የሚያስገኝ ከመሆኑም በላይ፣ በገበያው ውስጥ ጤናማ ውድድር እንዲፈጠር በማድረግ ሸማቾች በተሻለ ዋጋ ጥራት ያለው ምርትና አገልግሎት የማግኘት ዕድላቸውን በእጅጉ ያሰፋዋል።

ከሁሉም በላይ የንግድ ልውውጥ መጨመሩ የሀገሪቱን አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) የሚያሳድግ ሲሆን፣ በማምረት፣ በትራንስፖርትና በንግድ ዘርፎች ከፍተኛ የሥራ ዕድልን ከመፍጠሩም ባሻገር የውጭ ምንዛሬ ገቢን በማሳደግ በሀገራትና በሕዝቦች መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ይታመናል።

አዲሱ የንግድ ፖሊሲ እነዚህ ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት የተደረጉ የንግድ ዘርፎች በተግባር ላይ በሚውሉበት ወቅት የሚያጋጥሙ ማነቆዎችንና ተግዳሮቶችን ለመቀነስ እንዲሁም አጠቃላይ ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ በእጅጉ ያግዛል።

ግንቦት 21/2018 ዓ.ም
MoTRI

በኢትዮጵያ የንግድ ታሪክ የመጀመሪያው የሆነውና ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን ከተቋቋመ ከ118ዓመታት በኋላ አገራዊ የንግድ ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቋል።               * * * ...
26/05/2026

በኢትዮጵያ የንግድ ታሪክ የመጀመሪያው የሆነውና ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን ከተቋቋመ ከ118ዓመታት በኋላ አገራዊ የንግድ ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቋል።
* * * *
የኢትዮጵያ የንግድ ዘርፍ የሚመራበት ወጥ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ተዘጋጅቶ ዛሬ በሚኒስትሮች ምክር ቤት በይፋ ጸድቋል ።

የንግድ ዘርፉ ለአጠቃላይ የሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዕድገት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው የላቀ አስተዋፅዖ እና የዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተር ቢሆንም፣ እስካሁን ራሱን የቻለ ወጥ ፖሊሲ ባለመኖሩ የገቢና ወጪ ንግዱ ቅንጅትና መናበብ ሲጎድለው ቆይቷል ።

ቀደም ሲል ንግድን የሚመለከቱ የፖሊሲ ጉዳዮች በተለያዩ የሴክተር ፖሊሲዎች፣ አዋጆችና ደንቦች ውስጥ በተበታተነ ሁኔታ መገኘታቸው ዘርፉን በተሟላ ሁኔታ ለመምራት ትልቅ መሰናክል ሆኖ የቆየ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት የሀገሪቱ የንግድ ሥርዓት ፍትሃዊ ውድድር የሚጎድለው፣ የተለያዩ ሕገ-ወጥነትና ብልሹ አሠራሮች የበዙበት፣ እንዲሁም ሸማቾችን ያማረሩ የግብይት ሁኔታዎች የሚስተዋሉበት ሆኖ አልፏል ።

ከዚህም በተጨማሪ የወጪ ንግዱ በተበታተነ ሁኔታ በበርካታ ተቋማት የሚመራ በመሆኑ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪነቱን ማረጋገጥ ሳይችል መቆየቱ ይታወቃል ።

ይህንን ሰፊ ክፍተት ለመሙላት በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተዘጋጀውና ዛሬ የጸደቀው ታሪካዊው የንግድ ፖሊሲ፣ የነፃ ገበያ ሥርዓቱን በተሻለ ሁኔታ ለመምራትና የዘርፉን ተግዳሮቶች በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ ፋይዳ አለው ።

ፖሊሲው የተቀረፀው በአገሪቱ እየተገነባ ባለው 9የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ሥርዓት ማዕቀፍ ውስጥ ሲሆን፣ ይኸውም የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓትን ወጥ በሆነ እሳቤ ለመምራት፣ የወጪ ንግድን በግብርና ምርቶች ላይ ካለው ጥገኝነት ማላቀቅ፣ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎችን ከዓለም አቀፍ ውድድር ለመጠበቅ ጊዜያዊ የታሪፍና የማበረታቻ ድጋፎችን ለመስጠት እንዲሁም የሸማቾችን መብትና ደህንነት በተደራጀ መልኩ ለማስጠበቅ ትልቅ መሠረት የሚጥል ነው ።

ፖሊሲው የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የአስር ዓመቱን የልማት ዕቅድ መነሻ አድርጎ የተዘጋጀ በመሆኑ ሀገራዊ ፋይዳው እጅግ የጎላ ነው ።

ይህ ሰነድ በአሁኑ ወቅት መዘጋጀቱና መጽደቁ በንግዱ ማኅበረሰብ እና በግሉ ዘርፍ ላይ ከፍተኛ ተገማችነትንና መተማመንን የሚፈጥር ሲሆን፣ የግሉ ዘርፍ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ዋና ሞተር ሆኖ እንዲያገለግል መንግሥት ምቹ ከባቢያዊ ሁኔታን እንደሚፈጥር ይታመናል ።

በተለይም የንግድ ሕጎች፣ ደንቦችና አሠራሮች በየጊዜው ከመለዋወጥ ወጥተው፣ ለሁሉም የንግድ ተዋናዮች ግልጽ፣ ተጠያቂነት የሰፈነባቸውና ቀድሞ "ተገማች" እንዲሆኑ የሚያደርግ በመሆኑ፣ የግሉ ዘርፍ ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም አቀፍ የንግድ ምህዳር ውስጥ የረጅም ጊዜ ዕቅዶቹን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲመራና ኢንቨስትመንቱን እንዲያሰፋ ሙሉ መተማመንን ይፈጥርለታል ።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የምታካሂደውን የዓለም ንግድ ድርጅት (WTO) አባልነት ድርድር፣ የአህጉራዊ (AfCFTA) እና የቀጣናዊ የንግድ ስምምነቶች ውህደትን ወጥ በሆነ እሳቤ ለመምራት የሚያስችል ይፋዊ ሰነድ በመሆኑ፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን (FDI) በመሳብ ረገድ ለዓለም አቀፍ ነጋዴዎችና ባለሀብቶች ከፍተኛ ተገማችነትን የሚሰጥ ነው ።

ግንቦት 18/2018 ዓ.ም
MoTRI

Address

Hara Gebeya

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሀራ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share