06/09/2026
የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና ዋና ፅ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፋራህ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር መድረክ (Inter-Continental Dialogue among Political Parties - ICDPP) ላይ ለመሳተፍ ሴኡል፣ ደቡብ ኮሪያ ገብተዋል።
ከሴፕቴምበር 6 እስከ 9 ቀን 2026 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ከፍተኛ አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ከአፍሪካ፣ ኤሽያ፣ አውሮፓ፣ ላቲን አሜሪካ እና ሰሜን አሜሪካ የተወጣጡ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን በአሁን ወቅት የተሳታፊዎች እንኳን በደህና መጣችሁ መርሃ ግብር እየተደረገ ይገኛል።
ጉባኤው በዓለም አቀፍ ደረጃ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የጋራ ግንዛቤ እና ትብብር ማጠናከርን ዋና አላማው አድርጎ የተነሳ ሲሆን በቀጣይ ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።