05/09/2026
በሐረሪ ትራንስፖርትእና መንገድ ልማት ቢሮ የመሶብ ቤተሰብ አባላት የሐረር መቄዶንያ አረጋውያን መጦሪያ ማዕከልን ጎበኙ።
ሐረር፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም. — በሐ/ት/መ/ል/ቢሮ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት የመሶብ ቤተሰብ አባላት ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣትና ለአረጋውያን ያላቸውን ክብርና አክብሮት ለመግለጽ በሐረር የሚገኘውን መቄዶንያ አረጋውያን መጦሪያ ማዕከል ጎበኙ።
የመሶብ ቤተሰብ አባላቱ በጉብኝታቸው ወቅት ከማዕከሉ አረጋውያን ጋር ጥሩ ጊዜ በማሳለፍ የደስታና የአጋርነት ስሜት የፈጠሩ ሲሆን፣ ማዕከሉ ለአረጋውያኑ የሚሰጠውን እንክብካቤና አገልግሎትም ተመልክተዋል።
በተጨማሪም ለአረጋውያኑ ያላቸውን አጋርነትና ድጋፍ በተግባር ለማሳየት የንጽህና መጠበቂያ የገላና የልብስ ሳሙናዎችን በድምሩ 3,500 ብር የሚገመት ድጋፍ አበርክተዋል።
የመሶብ ቤተሰብ ሰብሳቢ አቶ ጃዕፈር ኢብራሒም በጉብኝቱ ወቅት በሰጡት አስተያየት፣ “ይህ ጉብኝት ማኅበራዊ ግዴታችንን ከመወጣት ባለፈ፣ ለአገር ባለውለታ የሆኑትን አረጋውያን ለመንከባከብና ለማስደሰት ትልቅ ዕድል ፈጥሮልናል” ብለዋል።
በማዕከሉ የሚገኙ አረጋውያንም ለተደረገላቸው ሰብአዊ ድጋፍና እንክብካቤ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል። እንዲህ ያሉ የማኅበራዊ ኃላፊነት ተግባራት አረጋውያን የሚሰማቸውን ተስፋና ደስታ ከማጠናከር ባለፈ፣ በማኅበረሰቡ ውስጥ የመረዳዳትና የአጋርነት ባህልን ለማጎልበት የሚያበረክቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የመሶብ ቤተሰብ አባላት በቀጣይም መሰል የማኅበራዊ ድጋፍና በጎ ተግባራትን በማጠናከር ለመቀጠል ቃል ገብተዋል።
በሐ/ት/መ/ል/ቢሮ
የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት
የመሶብ ቤተሰብ አባላት
ሐረር