31/05/2026
🚶♂️🌿 መንገዶቻችን ለሰዎች፤ ጤናማ ማህበረሰብና ዘላቂ የመንገድ ደህንነት መሠረት!
══════
በዘመናዊ ከተሞች ውስጥ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ብቻ ሳይሆን ለሰዎች የጤና፣ የመዝናኛ፣ የማህበራዊ ትስስርና የአካባቢ ጥበቃ ማዕከላት መሆን እንደሚችሉ እያሳየ ያለ ተግባር የ“ሞተር አልባ ቀን” ፕሮግራም ነው።
በሐረሪ ክልል በየሳምንቱ በሚካሄደው ይህ ልዩ እንቅስቃሴ ህብረተሰቡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳየ ያለው ንቁ ተሳትፎ፣ ፕሮግራሙ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትና ተወዳጅነት እያገኘ መምጣቱን በግልጽ ያረጋግጣል።
ይህ እንቅስቃሴ ጤናማ አኗኗርን ከማበረታታት ባሻገር፣ ንጹህ አየር፣ ደህንነቱ የተጠበቀ መንገድ፣ የተሻለ የከተማ ኑሮ እና የተጠናከረ ማህበራዊ ትስስር ለመፍጠር ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
የዚህ ሳምንት የሞተር አልባ ቀን ፕሮግራም
በሸንኮር ወረዳ “ሰላም ጎዳና” ለ 116ኛ ጊዜ
በሐኪም ወረዳ (ከ4ኛ ቶታል እስከ ኦጋዴን አንበሳ) ለ 30ኛ ጊዜ
የተካሄደው ፕሮግራም በህፃናት፣ በወጣቶች፣ በአዛውንቶች፣ በሴቶች እና በሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ሰፊ ተሳትፎ ታጅቦ በደማቅና በአስደሳች ሁኔታ ተካሂዷል።
🏃♂️🚴♀️ በፕሮግራሙ የተከናወኑ ዋና ዋና እንቅስቃሴዎች
✅ ሩጫ
✅ የባይስክል ጉዞ
✅ የቡድን ስፖርቶች
✅ የኳስ ቅብብሎሽ
✅ የገመድ ዝላይና የህፃናት መዝናኛ ጨዋታዎች
✅ የአካል ብቃት ማሳያዎች
✅ የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ መልዕክቶች
ፕሮግራሙ እያመጣ ያለው አዎንታዊ ለውጥ
ጤናማና ንቁ ማህበረሰብ መፍጠር
የአየርና የድምፅ ብክለትን መቀነስ
ማህበራዊ አንድነትን ማጠናከር
የመንገድ ደህንነት ባህልን ማዳበር
ቤተሰብና ማህበረሰብን በጋራ ማቀራረብ
የሞተር አልባ ቀን ፕሮግራም ከስፖርትና ከመዝናኛ እንቅስቃሴ በላይ የሆነ፣ ጤናማ አኗኗርን፣ አካባቢ ጥበቃን፣ የመንገድ ደህንነትን እና ማህበራዊ አንድነትን የሚያጎለብት ዘላቂ ማህበራዊ ንቅናቄ ሆኖ ቀጥሏል።
የህብረተሰቡ እየጨመረ የመጣ ተሳትፎም እነዚህ እሴቶች በሕዝባችን ዘንድ እየሰረፁ መምጣታቸውን ያሳያል።
ስለዚህ ለትውልድ የሚተላለፍ ይህን መልካም ተሞክሮ በቀጣይነት ማጠናከርና የሁሉንም ክፍል ተሳትፎ ማሳደግ ይገባል።
👉 “መንገድን ለሰው ስንሰጥ፣ ከተማችንን ለሕይወት እናዘጋጃለን!”
👉 “ዛሬ የምንወስደው እርምጃ፣ የነገ ጤናማ፣ ንጹህና ዘላቂ ከተማችን መሠረት ነው!”
የሐረሪ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ
የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት
ግንቦት 23/2018 ዓ.ም
ሐረር