28/08/2026
በዞኑ የወጣቶችና የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጥና የሚስተዋሉ ጉድለቶችን በመቅረፍ ሁሉ አቀፍ ብልፅግና ለማስመዝገብ ይሰራል፤ አቶ ገዛኸኝ ገዝሙ
በኮንታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በዞኑ በፓርቲ መሪነት ባለፉት ጊዜያት በተሰሩ ስራዎች አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
መድረኩን የመሩት የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አቶ ገዛኸኝ ገዝሙ ብልፅግና ፓርቲ ሀገሪቷን ተረክቦ ተጨባጭ ለውጦችን ለማምጣት ሰፊ ስትራቴጂዎችን ነድፎ ወደ ተግባር በመግባት የህብረተሰቡን ህይወት በዘላቂነት ልለውጡ የሚችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።
በሂደቱም ከውስጥና ከውጭ ብዙ ፈተናዎች ቢያጋጥሙም ለፈተናዎች ሳይበገር በመስራቱ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ዘርፈ ብዙ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
በተለይም የኮርደር ልማት፣ የሞዴል መንደር፣ የሌማት ትሩፋትና ሌሎች ኢንሼቲቮችን ጨምሮ ሌሎች ሰፊ መደበኛ ተግባራት በትኩረት መከናወናቸውን የገለፁት አቶ ገዛኸኝ በቀጣይም የተቋማት ግንባታና ውስጠ ፓርቲ አደረጃጀት በማጠናከር ለበለጠ ውጤት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
በዞኑ የወጣቶችና የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጥና የሚስተዋሉ ጉድለቶችን በመቅረፍ ሁሉ አቀፍ ብልፅግና ለማስመዝገብ ይሰራል ያሉት ኃላፊው ሁሉም በየደረጃው መትጋት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የዞኑ ብልፅግና ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግኑኝነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ባሻ በላቸው ያለፈው በጀት ዓመት በሀገሪቱ ብሎም በዞኑ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በድል የተጠናቀቀበትና ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እየተካሄደ የሚገኝበት መሆኑን በማንሳት ከዚህ ስራ ጎን ለጎን የተለያዩ ኢንሼቲቮችና መደበኛ ተግባራት በተሳካ ሁኔታ የተከናወኑበት እንደሆነ ገልፀዋል።
የዞኑን የፖለቲካ አዝማሚያ ትንተና በማድረግ አስፈላጊ እሪምጃዎች እየተወሰዱ ውጤቶች መመዝገባቸውንም አክለዋል።
የዞኑ ብልፅግና ፓ/ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ እንግዳወርቅ ዶኖቾ በበኩላቸው በዞኑ በ279 ህብረቶች የተደራጁ 43,481 በላይ አባላት መኖራቸውን በመግለፅ ይህንን በማጠናከር ላይ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊመሩ እንደሚገባ አስረድተዋል።
በፓርቲ አሰራር በመመራት የጠባቂነት፣ የመረጃ አደረጃጀትና መሠል ችግሮችን በመቅረፍ የትኩረት አቅጣጫዎች በመከተል የህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የበለጠ መስራት ይገባናል ብለዋል።
በዞኑ በ2018 በጀት ዓመት ተቋማዊ ጥንካሬና ቅቡልነት ማሳደግ፣ ህብረ ብሄራዊ አንድነትና ሰላም ማጠናከር፣ የ2018 ሀገራዊ ምርጫ ስኬት ለቀጣይ የብልጽግና ጉዞ እድል ብቻም ሳይሆን ከፍተኛ አደራና ኃላፊነት የተሰጠበት በመሆኑ የመራጩንና መላውን ህብረተሰብ እኩል ለማገልገል ከምንም ጊዜ በላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባና ሌሎች ተቋማዊ አሰራሮችን ማጠናከር ላይ የትኩረት አቅጣጫዎች ተቀምጠው ወደ ተግባር መገባቱ በመድረኩ በቀረበው ሪፖርት ላይ የተገለፀ ሲሆን በዚህም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ዘርፈ ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግባራት መከናወናቸው ተገልጿል።
በዞኑ በፖለቲከና ህዝብ ግኑኝነት፣ በአደረጃጀት፣ በሴቶችና ወጣቶች ክንፎች፣ በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታና ሌሎች ዘርፎች አበረታች ስራዎች መሰራታቸው የቀረበ ሲሆን በ2019 በጀት ዓመትም የታየውን የማስፈፀም አቅም የበለጠ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተመላክቷል።
የመድረኩ ተሳታፊ አመራር አካላት ያለፈው ዓመት ከመቼውም ጊዜ በላይ ስኬት የተመዘገበበት ዓመት ስለመሆኑ ተናግረው የፓርቲ አደረጃጀቶችን የበለጠ ማጠናከር፣ የአቅም ግንባታ፣ ክትትልና ድጋፍ ስራዎችን ማሻሻልና የተጀመረውን ስራ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
በህዝብ ስነሱ በነበሩ ቀሪ ጉዳዮች ላይ በማተኮር መስራት ይገባል ያሉት ተሳታፊ አመራር አካላት በተለይም የአገ/ሎት አሰጣጥ ማሻሻል፣ የኑሮ ውድነትን ማርገብ፣ እንዲሁም በቀሪ የመሠረተ ልማትና የወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው ጠቁመዋል።
በመድረኩ የዞኑ ብልፅግና ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ገዝሙን ጨምሮ ሌሎች የዞን፣ የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደሮች የፓርቲ ስራ ኃላፊዎች እና የመንግስት ሰራተኛ የህብረት አመራሮች የተገኙ ሲሆን በቀጣይ በትኩረት በሚሰሩ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።
መድረኩ በ2018 በጀት ዓመት የላቄ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮችና ህብረቶች ማበረቻ ሽልማት በመስጠትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ግብ ስምምነት በመፈራረም እንዲሁም ባለ 8 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።
ዘገባው:-የኮንታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ቤት የህዝብ ግኑኝነት ነዉ።