EPSA Hawassa Hub

EPSA Hawassa Hub EPSS is the classic supplier founded by legal and governmental ways to supply pharmaceuticals based on the needs of all health facilities in Ethiopia.

የማርበርግ ቫይረስ ምላሽን ለማሳደግ የሚረዳ የሙኩራ ክትባት ለተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ሊሰጥ ነው፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ #የማርበርግ ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ...
05/12/2025

የማርበርግ ቫይረስ ምላሽን ለማሳደግ የሚረዳ የሙኩራ ክትባት ለተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ሊሰጥ ነው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

#የማርበርግ ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ 5,000 የማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት ከአሜሪካ መንግስት በድጋፍ የተገኘ ሲሆን፤ ክትባቱን ለኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት የአሜሪካ በኢትዮጵያ አምባሳደር አርቪን ማሲንጋ አስረክበዋል።

ክትባቱ በአርማወር ሃንሰን የምርምር ተቋም በሚመራ ፈጣን የደረጃ 2 ክሊኒካዊ ሙከራ ተደርጎለት ጥቅም ላይ እንደሚውል የገለጹት ክትባቱን የተረከቡት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሲሆኑ፣ የምርመራ ተቋሙ ከኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት ባለስልጣን ጋር በመተባበር ቁጥጥር እንደሚያደርግም አክለዋል። ክትባቱን ከህዳር 29 ቀን ጀምሮ መስጠት የሚጀመር ሲሆን የጤና ባለሙያዎችን እና ከፍተኛ ተጋላጭ ለሆኑ ቡድኖች ቅድሚያ ይሰጣል ብለዋል።

ዩናይትድ ስቴትስ በባርዳ እና በሳቢን የክትባት ተቋም በኩል ክትባቱን ተደራሽ ማድረጉን የገለጹት አምባሳደር ማሲንጋ፤ የማርበርግ ወረርሽኝ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ ጠንካራ አጋር መሆኗን ማረጋገጧን ተናግረዋል።

ጤና ሚኒስቴር ወርሽኙን ለመግታት ከሚመለከታችዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚላሽ አሰጣጡን አጠናክረዉ የቀጠሉ ሲሆን የቅኝትና ቁጥጥር ስራዉን ማጠናከር፣ የጤና ባለሙያዉንና ጤና ሰራተኞች ጨምሮ ተጋላጭ የሆኑትን በመጠበቅ ላይ ትኩረት በማድረግ የመከላከል ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።

ምንጭ ፣ጤና ሚንስቴር

የሐዘን መግለጫየኢትዮጵያ  የመድኃኒት  አቅራቢ አገልግሎት  የሐዋሳ  ቅርንጫፍ  ከፍተኛ  የቅዝቃዜ ሰንሰለት  ባለሙያ  በሆኑት  አቶ እሸቱ  የሱፍ ህልፈተ ህይወት የተሰማኝን  ጥልቅ ሐዘን ...
03/12/2025

የሐዘን መግለጫ
የኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሐዋሳ ቅርንጫፍ ከፍተኛ የቅዝቃዜ ሰንሰለት ባለሙያ በሆኑት አቶ እሸቱ የሱፍ ህልፈተ ህይወት የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን በራሴና በተቋማችን ስም እየገለጽኩ ለመላው ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ እንዲሁም ለመላው የተቋማችን ማህበረሰብ መጽናናትን እመኛለሁ።
አቶ እሼቱ የሱፍ ከሐገር ውጪና ሐገር ውስጥ በወሰዷቸው የ Cold Chain equipments installation and Maintainace ስልጠናዎችና ባካበቱት የዳበረ ልምድ ለህፃናትና እናቶች የሚሰጡት ክትባቶች ደህንነትና ፈዋሽነት እንዲጠበቅ ወሳኝ የሆነው የተቋማችን የቅዝቃዜ ሰንሰለት አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን ጉልህ ሚና የተጫወቱ ከፍተኛ ባለሙያ/Senior expert/ ነበሩ።
አቶ እሸቱ ከተቀጠሩበት የሐዋሳ ቅርንጫፍ በተጨማሪ የተቋማችን ዋና መ/ቤት እና በመላ ሐገሪቱ የሚገኙ የአገልግሎት መ/ቤታችን 19 ቅርንጫፎች እንዲሁም የመንግስት ጤና ተቋማትን የቅዝቃዜ ሰንሰለት በመግጠምና Preventive እና Corrective maintainance ስራ በመስራት ለህብረተሰቡ የሚሰራጩ የክትባት መድኃኒቶቸ ጥራታቸውና ደህንነታቸው የተጠበቁ እንዲሆኑ በማረግ ረገድ ጉልህ ሚና የነበራቸው የተቋማችን ብሎም የጤናው ሴክተር ዕንቁ ባለሙያ ነበሩ።

⚠️ የጥንቃቄ መልዕክት ‼️የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ህብረተሰቡ ያልተመዘገቡና የጥራት ደረጃ የማያሟሉ ፀረ ወባ መድኃኒቶችን እንዳይጠቀም አሳሰበ፦
21/12/2024

⚠️ የጥንቃቄ መልዕክት ‼️
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ህብረተሰቡ ያልተመዘገቡና የጥራት ደረጃ የማያሟሉ ፀረ ወባ መድኃኒቶችን እንዳይጠቀም አሳሰበ፦

የሚንስትሮች ምክር ቤት በመድሀኒት ፈንድ እና የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውሳኔ አስተላለፈ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የሚንስትሮች ምክር ቤት በመድሀኒት ፈንድ...
29/06/2024

የሚንስትሮች ምክር ቤት በመድሀኒት ፈንድ እና የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውሳኔ አስተላለፈ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የሚንስትሮች ምክር ቤት በመድሀኒት ፈንድ እና የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ በ37ተኛው መደበኛ ስብሰባ ላይ ሠኔ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ተከታዩን ውሳኔ አስተላልፏል።

ምክር ቤቱ የመድሀኒት ፈንድ እና የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት አድርጓል ፡፡

ጥራታቸው የተረጋገጠ መሠረታዊ መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋና ዘላቂነት ባለው መልኩ ለተጠቃሚው ሕብረተሰብ ማቅረብ የሚያስችል ዘመናዊ የመድኃኒት አቅርቦት ሠንሰለት ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

የሐዘን መግለጫከ የካቲት 1983 ዓ.ም  ጅምሮ ከ 33 ዓመታት በላይ   በኢትዮጵያ  የመድኃኒት  አቅራቢ አገልግሎት የሐዋሳ ቅርንጫፍ ግንባር ቀደም  ሠራተኛ    በነበሩት  በአቶ ታምራት  ...
16/06/2024

የሐዘን መግለጫ
ከ የካቲት 1983 ዓ.ም ጅምሮ ከ 33 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሐዋሳ ቅርንጫፍ ግንባር ቀደም ሠራተኛ በነበሩት በአቶ ታምራት ማዘንጊያ ድንገተኛ ህልፈተ ሞት የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን በራሴና በተቋማችን ስም እየገለጽኩ ለቤተሰቦቻቸው፣ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለስራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ!

ለሁሉም ጤና ተቋማት (በEPSS ሀዋሳ ከቅርንጫፍ ስር ለሚትገለገሉ)፡-  የክትባት እጥረት የገጠማችሁ ከዝህም በፊትም እንደተለመደዉ የጤና ተቋማችዉን ዉክልና ፣ Coldbox, ሞደል-19ን እና...
19/05/2024

ለሁሉም ጤና ተቋማት (በEPSS ሀዋሳ ከቅርንጫፍ ስር ለሚትገለገሉ)፡- የክትባት እጥረት የገጠማችሁ ከዝህም በፊትም እንደተለመደዉ የጤና ተቋማችዉን ዉክልና ፣ Coldbox, ሞደል-19ን እና የተቋማችሁ ባለሞያ መሆናችሁን የሚገልጽ የመስርያ ቤታችሁን መታወቂያ ካርድ ኮፒ በመያዝ መጥታችሁ መወሠድ የምትችሉ መሆኑን (በድጋሚ) በአክብሮት እናስታውቃለን።

EPSS HAWASSA HUB!!

!!

https://www.youtube.com/watch?v=iYgs_W6wRqg
27/04/2024

https://www.youtube.com/watch?v=iYgs_W6wRqg

የኢትዮጵያ መድሐኒት አቅርቦት አገልግሎት የሀዋሳ ቅርንጫፍ ለህክምና ተቋማት የሚሰጠው አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችለውን ሶፍትዌሮችን ተግባራዊ እያደረገ ስለመሆኑ ...

25/01/2024

በEPSS ሀዋሳ ቅርንጫፍ ሥር የምቲገለገሉ ጤና ተቋማት በሙሉ ፣ ወርያዊ RRF እና VRF ወደ EPSS ሀዋሳ ቅርንጫፍ ስታመጡ ወይም የሚታመጡ ተቋማት እና ዞኖች ያመጣችሁትን RRF እና VRF ቆጥራችሁ ማስረከብ ያለባችሁ ለሚመለከተው ሰዉ ብቻ መሆኑን በተደጋጋሚ ለክልሎች እና ለዞኖቻችሁ የነገርናቸዉ ጉዳይ ብሆንም ፣ አሁንም ተቋማት መድኃኒትን እና ክትባት በጊዜዉ እንዳያገኙ እና ለመረጃ ልዉዉጥ ትልቅ ችግር ሆኖ ስለምታይ የሚመለከታችሁ አካላት እንድታስተካክሉ እያልን በድጋሚ ለማስታወስ ያህል ነዉ።
አለበለዚያ ለጽዳት ፣ ለጥበቃ... ሰጥታችሁ ብጠፋባችሁ ተጠያቂዎች እራሳችሁ መሆናችሁን እወቁ።

ሌላ የተሻለ አማራጭ!!ከኢትዮጵያ መድኋኒት አቅርቦት አገልግሎት ከሀዋሳ ቅርንጫፍ መድኃኒት በአካል መጥታችሁ መግዛት ለምትፈልጉ ተቋማት ሁሉ፣ የግዥ ዝርዝር መድሀኒቶችን ወደተቋማችን ከመምጣታች...
11/08/2023

ሌላ የተሻለ አማራጭ!!

ከኢትዮጵያ መድኋኒት አቅርቦት አገልግሎት ከሀዋሳ ቅርንጫፍ መድኃኒት በአካል መጥታችሁ መግዛት ለምትፈልጉ ተቋማት ሁሉ፣

የግዥ ዝርዝር መድሀኒቶችን ወደተቋማችን ከመምጣታችው በፊት ከስር በፎቶ ላይ ባለዉን web-site ላይ online ገብታችሁ መድሀኒት ልስቶቻችሁን ወደ ተቋማችን ከመምጣታቸው በፊት ማስገባት አለባችሁ።

ቀላል እና ቀልጣፋ ነዉ ተጠቀሙት፣ በተቋማችን ዉስጥ ያለዉን process ያሳጥራል እና ያቀላጥፋል!!!

እንኳን ደስ አለን!በተቋማችን ተግባራዊ እያደረግን  የቆየናቸው የሪፎርም ስራዎች  በመድኃኒት ክምችት አስተዳደርና መጋዘን አያያዝ  ስርዓት (Warehousing and Inventory Manag...
24/08/2022

እንኳን ደስ አለን!
በተቋማችን ተግባራዊ እያደረግን የቆየናቸው የሪፎርም ስራዎች በመድኃኒት ክምችት አስተዳደርና መጋዘን አያያዝ ስርዓት (Warehousing and Inventory Management System) ረገድተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው።

ከአመታት በፊት ይሳካሉ ተብለው የማይታሰቡ ዕቅዶች ዕውን እየሆኑ ነው። ከዚህ በፊት ወራትን ይወስድ የነበረው አመታዊ የመድኃኒት ቆጠራ ሂደት በ 3 ቀናት ማጠናቀቅ ችለናል።

በሚሊዮኖች ብር የነበረውን አመታዊ የመድኃኒት ጉድለት/ብክነት/ በ 2014 በጀት ዓመት ወደ 5,123.93 ብር ለማውረድ ችለናል።

በዚህ ረገድ በዋናው መ/ቤት እና በቅርንጫፎች የመጣውን ተጨባጭ ውጤት ምክንያት በማድረግ የተቋማችን የቦርድ ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ በተገኙበት የአፈፃፀም ግምገማና የሽልማት ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን ባስመዘገብነው ውጤት ተሸላሚ ሆነናል።

እንኳን ደስ አለን!
ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ከፍተኛ ርብርብ ያደረጋችሁ የተቋማችን ሰራተኞች ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ!!!!

Address

Sidama National Regional State
Hawassa
16

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 09:00 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:00
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Telephone

+462124068

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EPSA Hawassa Hub posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share