09/12/2025
የሆለታ እንስሳት ልማት ማዕከል የተሻሻሉ ጊደሮችን ለገበሬዎች የማስተላለፍ መርሃ ግብር አካሄደ።
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
👉 የሆለታ እንስሳት ልማት ማዕከል በማዕከሉ የተሻሻሉ ጊደሮችን በአካባቢው ለሚገኙና ከሁሉም ቀበሌዎች ለተውጣጡ ገበሬዎች ግልፅ በሆነ መንገድ ዕጣ የማውጣት እና በወጣላቸው ዕጣ መሠረት የማስተላለፍ መርሃ ግብር አካሄደ።
👉 በመርሃ ግብሩ ላይም ክቡር አቶ አዲሱ አረጋ የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር , ክቡር አቶ ፍቅሩ ረጋሳ የእንስሳትና አሳ ሃብት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ, ክቡር አቶ ቶሌራ ደበላ የኦሮምያ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ, ክቡር አቶ እሸቱ በቀለ የሆለታ ከተማ ከንቲባ , ክቡር ዶ/ር አስራት ጤራ የኢንቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር , ክቡር ዶ/ር አራርሳ ዱጉማ የማዕከሉ ዋና ሃላፊ ,እንዲሁም ከግብርና ሚኒስቴር የመጡ የበላይ ሃላፊዎች ,የሆለታ ከተማ የበላይ ሃላፊዎች, የኢንቲትዩቱ የበላይ ሃላፊዎች, የማዕከሉ ሃላፊዎች, አባ ገዳዎች እንዲሁም ከሁሉም ቀበሌዎች የተውጣጡ ገበሬዎች እና የማዕከሉ ሰራተኞች ተገኝተውበታል።
👉 በዕለቱም የሆለታ ከንቲባ ክቡር አቶ በቀለ እሸቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል, በመቀጠል ክቡር ዶ/ር አስራት ጤራ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ስለ ኢንስቲትዩቱ ለተገኙ እንግዶች ገለፃ አድርገዋል። በመጨረሻም ክቡር አቶ አዲሱ አረጋ የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀገራችን በግብርናው ዘርፍ ስላለችበት ሁኔታ ገለፃ አድርገው ለወደፊትም የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።
👉 በስተመጨረሻም የሆለታ እንስሳት ልማት ማዕከልን በመጎብኘት የመርሃ ግብሩ ፍፃሜ ሆኗል።
መርሃ ግብሩንም በቪዲዮ ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።
ህዳር 30 | 2018 ዓ.ም
ሆለታ