02/09/2026
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀላባ ዞን ሴቶች ክንፍ በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ አድራጎት ድጋፍ አደረጉ
ሆሳዕና ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም
"በጎነት ለእህትማማችነትና ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት!" በሚል መሪ ሀሳብ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀላባ ዞን የሴቶች ክንፍ ልዑካን ቡድን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ በመገኘት እህትማማችነትና ወንድማማችነት የሚያጠናክር ወሰን ተሻጋሪ የበጎ አድራጎት ድጋፍ አበርክተዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ ኤልሳቤት ሽመልስ በስነ-ስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልእክት እንደገለጹት፤ የሴቶች ክንፍ አባላት በክልሉ በሚካሄዱ መደበኛና ወቅታዊ የንቅናቄ አጀንዳዎች ላይ ግንባር ቀደም በመሆን የመሪነት ሚናቸውን ሲወጡ ቆይተዋል፤ አሁንም አጠናክረው ቀጥለዋል።
ኃላፊዋ አክለውም በክረምት ወራት በየደረጃው የሚገኙ የሴቶች ክንፍ አመራሮችና አባላት ባደረጉት የተቀናጀ እንቅስቃሴ በርካታ አርአያነት ያላቸው ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።
ወ/ሮ ኤልሳቤት እንደገለጹት በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ በክልሉ በተለዩ 14 የንቅናቄ አጀንዳዎች ላይ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ዘርፈ-ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
የበጎ አድራጎት ስራው በዋናነት በመንግስትና በህብረተሰቡ ብቻ ሊሸፈኑ የማይችሉ፣ የኢኮኖሚ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና በእድሜ የገፉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ፍላጎት ለማሟላት ያለመ መሆኑንም አስረድተዋል።
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዳነ ወጫቶ ከቅርብ ጊዜ ወድህ የተጀመረው በጎ ፍቃድ አገልግሎት የብልጽግና ፓርቲ አንዱ ዓለማ ነው ያሉ ስሆን የአቅም ውስንነት ያለባቸው ሰዎችም በዚህ በጎ ተግባር ተደራሽ እየተደረጉና መጠለያ እያገኙ መሆኑን ጠቁመዋል።
አቶ አደነ ወጫቶም የሀላባ ዞን ወሰን ተሻጋሪ በጎ ፍቃደኞችን ስለተግባራቸውም አመስግነዋል።
የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፍ አቶ ፈይሳ ሙንድን የበጎ አድራጎት ስራው ከቁሳቁስ ድጋፍ በላይ በዞኖች እና በወረዳዎች መካከል ያለውን እህትማማችነት፣ አብሮነትና ወንድማማችነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም «በጎነት የቋንቋና የወሰን ገደብ የለውም። "ሴትናት በራሱ ደግናት" ማለት ነዉ ያሉት አቶ ፈይሳ የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥና አቅመ ደካሞችን መደገፍ የሁልጊዜም ትኩረታችን ነው» ብለዋል።
መርሃ-ግብሩ በክልሉ ባሉ ሁሉም መዋቅሮች እየተከናወነ የሚገኝ ስሆን ተግባሩ የሰብዓዊነት ግዴታም ጭምር መሆኑ ነው በሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የሴቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሀሊማ ወርቁ ተናግረዋል።
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጎዴቦ ጆርጋ እንደ ሀገር አቀፍ የተጀመረው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ ያለ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ጎዴቦ ተግባሩን የማስቀጠል ኃላፊነት የሁሉም ግለሰብ ኃላፊነትና አደራ ጭምር በመሆኑ ልዩ ትኩረት በየደረጃው ልደረግ ይገባል ብለዋል።
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የሴቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብርቅነሽ መንደሮ በበኩላቸው በሴቶች የሚጀመር በጎ ተግባር ሁል ጊዜ ቀጣይነት ያለውና ከቅንነት የሚመነጭ ፍጹም ተግባር ነው ያሉ ስሆን ተግባሩ በእኛ ሴቶች የሚገታ ሳይሆን ሁሉም ግለሰብ ጋ መዳረስ አለበትም ብለዋል።
አክለውም እኛ ሴቶች የበጎነት ተምሣሌቶች የሰላም ባለቤቶች መሆናችንን ጭምር ይህ መርሃግብር በግልጽ የሚናገር ነው በማለት አገልግሎቱ ዛሬ ብቻ ሚፈጻም ሳይሆን የዘወትር ተግባር ነው ብለዋል።
በተመሳሳይ ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ለአቅመ ደካማ ወገኖች የሚደረገውን ድጋፍ ለማጠናከር በተከናወነ የበጎ አድራጎት ተግባር፤ ለአንድ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ የአዲሱ መኖሪያ ቤት ግንባታን ለመጀመር የሚያስችሉ መሠረታዊ ቁሳቁሶች ድጋፍ የተደረጉ ሲሆን፣ ድጋፉ የቤተሰቡን የኑሮ ጫና በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተገልጿል።
ለተጨማሪ መረጃ፦
በቴሌግራም፦ https://t.me/CentralERProsperity
በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/CentralEthiopiaRegionprosperitypartyBranchoffice
በቲክቶክ፦tiktok.com/
ቲውተር፦ https://x.com/central94872?t=PyH4QvYNmJyPb4xLPJhGzQ&s=08
ዩቲዩበ=https://youtu.be/31PATodXf20?si=I5ZKltV2OayDr2Ca
ዌብሳይት https://www.cerprosperity.org.et/