የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Hossana
  • የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ይህ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው ።

የዕቅድ ግብ ስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ!ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም ሆሳዕና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ዘርፎችና ተጠሪ ተቋማት ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከክልሉ ሚሊሻ...
26/08/2026

የዕቅድ ግብ ስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ!

ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም ሆሳዕና

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ዘርፎችና ተጠሪ ተቋማት ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከክልሉ ሚሊሻ ጽ/ቤት እና ከክልሉ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ጋር የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የግብ ስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ፣ ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች በተገኙበት ከቢሮዉ ተጠሪ ተቋማት ጋር በ2019 በጀት ዓመት ታቅደው በሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ላይ የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ተጠሪ ተቋማት በበኩላቸዉ የዕቅድ ግብ ስምምነት ሰነዱ ሲፈርሙ ባስተላለፉት መልእክት በሁሉም ተቋማት መካከል የሚደረገውን የትብብር ሥራዎች ለማጠናከር፣ የዕቅድ አፈጻጸምን በውጤታማነት ለመከታተል እና የተቋማቱን የጋራ ግቦች ለማሳካት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገለፀዋል።

የፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ከሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እና ከአራት የዘርፍ አመራሮችና ከሶስቱም ተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር የተከናወነ ሲሆን፣ በቀጣይ በጀት ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይም ውይይት ተደርጓል።

ህብረተሰቡን የመረዳዳት ባህሉን ይበልጥ ማጎልበት ያስፈልጋል=====ነሀሴ 14/2018 የሀላባ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ከሀይማኖት ተቋማት ጋር በመቀናጀት እና በማስተባበር ያሰባሰቡትን አልባ...
20/08/2026

ህብረተሰቡን የመረዳዳት ባህሉን ይበልጥ ማጎልበት ያስፈልጋል
=====

ነሀሴ 14/2018 የሀላባ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ከሀይማኖት ተቋማት ጋር በመቀናጀት እና በማስተባበር ያሰባሰቡትን አልባሳት ለሀላባ ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም አስረክበዋል።

በዚህ ወቅት የሀላባ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ሙደስሪ ጉታጎ እንደገለጹት ህብረተሰቡን የመረዳዳት ባህሉን ይበልጥ ማጎልበት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በዞኑ የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ በክረምት ወራት ላይ በርካተ የበጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር የበጎ ስራዎችን እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

በዞኑ ድጋፍ ከሚሹ አካላት መካከል የህግ ታራሚዎች ተጠቃሽ ናቸው ያሉት አቶ ሙደስሪ በዚህም የተለያዩ አልባሳት፣ ማበርከታቸውን አመላክተዋል።

በየዓመቱ የዞኑ ማህበረሰብና ሌሎች አካላትን በማሳተፍ ጠያቂ ያጡ ታራሚዎች ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የማረሚያ ተቋሙ በማህበረሰቡ ውስጥ ችግር የሚፈጥሩ አካላትን ማረም እንደሆነ አንስተው የፀጥታ መምሪያ ከተጠሪ ተቋማት ከማረሚያ ተቋም በጋራና በቅንጅት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የሀላባ ዞን ፍትህ መምሪያ ሀላፊ አቶ ገራሙ ሱንክቻ በበኩላቸው በማረሚያ ተቋሙ ከዚህ በፊት የሚስታወሉ ችግሮችን በመቅረፍ ታራሚዎች ታንፀው እንዲወጡ እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች መልካም የሚባሉ መሆኑን አንስተዋል።

ለዚህም ፍትህ መምሪያ በቅርበት ከተቋሙ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን የገለጹት አቶ ገራሙ ሰንክቻ የተደረገው ድጋፍ በመምሪያውና በራሳቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

ታራሚዎች ታርመውና ታንፀው አምራች ዜጋ ሆነው እንዲወጡ ለማስቻል እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

የሀላባ ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ሀላፊ ሁሴን ጉንታ በበኩላቸው የህግ ታራሚዎች የህብረተሰቡ አንድ አካል ከመሆናቸው መነሻ የማረምና የማነፅ ስራውን በተሻለ ጥራት አገልግሎት ለመስጠት እየሰራ ያለውን ተግባር ጥሩ እንደሆነ ተናግረዋል።

በተቋሙ ከማረምና ከማነፅ ባለፈ ታራሚዎች የተለያዩ የሙያ ዓይነቶችን እንዲቀስሙ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀው በግቢ ውስጥ የተለያዩ ግብርና ልማት ስራዎች እያከናወኑ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በመሆኑም የዞኑ መንግስት ታራሚዎች ያሉበትን ሁኔታ በመረዳት የተለያዩ ድጋፎች ማድረጉን በማመስገን በቀጣይም ለማረሚያ ተቋሙ የሚደረጉ ድጋፎች መጠናከር አንዳለባቸው ገልጸዋል።

ይህንንም በጠየቅነው መሰረት የተገባውን ቃል ወደ ተግባር በመቀየር የፀጥታ መምሪያው ቅድሚያ ሰጥተው ለማረሚያ ተቋሙ ድጋፍ በማድረገቸው ሀላፊው በተቋሙና በታራሚዎች ስም በማመስገን በቀጣይም ለማረሚያ ተቋሙ የሚደረጉ ድጋፎች መጠናከር አንዳለባቸው አሳስበዋል።

በርክክቡ ላይ የሀላባ ዞን ምክር ቤት ህግና ፍትህ መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሁሴን ኢብራሂም፣ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ኑሪዬ፣ የዞኑ ሚሊሻ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመቹ ወርቅቾ፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

መረጃዉ የሀላባ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ነዉ።

ድህረ-ምርጫ ማህበረሰብ ውይይት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ" በሚል መሪ ቃል በሀላባ ዞን ከተለያዩ ማህበረሰብ ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው..ነሀሴ 7/2018 ሆሳዕና"ድህረ-ምርጫ ማህበረሰብ ውይይት...
13/08/2026

ድህረ-ምርጫ ማህበረሰብ ውይይት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ" በሚል መሪ ቃል በሀላባ ዞን ከተለያዩ ማህበረሰብ ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው..

ነሀሴ 7/2018 ሆሳዕና

"ድህረ-ምርጫ ማህበረሰብ ውይይት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ" በሚል መሪ ቃል በሀላባ ዞን ከተለያዩ ማህበረሰብ ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ ሀጂ ኑሪዬ እንደገለጹት የዞኑን ዘላቂ ሠላምና የተረጋጋ ልማት ለማረጋገጥ መንግስት፣ ህዝብ፣ የሀይማኖት ተቋማት እና የሀገር ሽማግሌዎች የጋራ ሀላፊነት እንዳለባቸውም ገልጸዋል።

ምርጫው ከተካሄደ በኋላ በሀላባ ዞን የሚገኘውን የሰላምና የመረጋጋት ሁኔታ በጋራ ለመገምገም፣ በምርጫ ሂደቱ የተከሰቱ ልዩነቶችንና ቅሬታዎችን ከሉም በሰላማዊ መንገድ ለመመልከት እንዲሁም ከምርጫ በኋላ የሚኖረውን የሰላም፣ የመቻቻልና የመግባባት ሁኔታ ይበልጥ ለማጠናከር ነው ብለዋል።

ድህረ-ምርጫ ሰላም የምርጫው መጨረሻ ሳይሆን፣ የቀጣይ የማህበረሰብ ሰላም መነሻ ነው ያሉት አቶ ሀጂ።

በምርጫ ሂደት ተወዳዳሪዎች ሊለያዩ እና የሀሳብና የፖለቲካ ልዩነትም ሊኖር ይችላል ብለዋል።

አያይዘውም ልዩነታችን ወደ ግጭት እንዳይቀየር፣ የምርጫ ውጤት በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ እንዲቀበል እና የማህበረሰቡ የጋራ ጥቅም ከፖለቲካ ልዩነት በላይ እንዲቆም ሁላችንም ሀላፊነት አለብን ብለዋል።

በተለይም የዞን አመራርና ሁሉም ባለድርሻ አካላት በድህረ-ምርጫ ወቅት የሚነሱ ቅሬታዎችን፣ አለመግባባቶችንና የሰላም ስጋቶችን በቅድሚያ በመለየት በውይይት፣ በምክክርና በህጋዊ ሂደት እንዲፈቱ የሚያደርጉት ሚና እጅግ ወሳኝ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት፣ የህግ የበላይነትን ለማክበርና ለማህበረሰቡ ሰላማዊ አርአያ ለመሆን የሚጠበቅባቸውን ሚና መወጣት ይገባቸዋል ብለዋል።

የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ደግሞ ያላቸውን የማህበረሰብ ተፅዕኖ በመጠቀም ሰላምን፣ መቻቻልንና ይቅርታን ለማጠናከር የላቀ ሚና አላቸው ብለዋል።

የጸጥታና የፍትህ ተቋማትም ህግን በእኩልነትና በግልፅነት በማስከበር፣ ማንኛውንም የግጭት ስጋት በቅድሚያ በመለየት እና በህጋዊ መንገድ በመፍታት ለዞኑ ሰላምና መረጋጋት ወሳኝ አስተዋፅኦ ማበርከት ይጠበቅባቸዋል ሲሉም አሳስበዋል።

ዛሬ የሚደረገው ውይይት ያለፈውን ብቻ ለመገምገም ሳይሆን፣ ከምርጫ በኋላ ያለውን የሀላባ ዞን ሰላምና መረጋጋት እንዴት በዘላቂነት እናጠናክር የሚለውን ጥያቄ በጋራ ለመመለስ ነው ብለዋል።

በዚህ መድረክ ላይ ሁሉም በነፃነት፣ በሀላፊነትና በመከባበር ሀሳብን እንድናካፍል፣ ችግሮችን ብቻ ከማንሳት ይልቅ ተግባራዊ መፍትሔዎችን እንዲንጠቁም፣ እንዲሁም ከዚህ ውይይት በኋላ በጋራ ልንፈጽማቸው የሚገቡ ተጨባጭ የስራ
አቅጣጫዎችን እንዲወስኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ሰላም የአንድ ተቋም ሀላፊነት አይደለም ያሉት አቶ ሀጂ ኑሪዬ የሁላችንም የጋራ ሀላፊነት ነው ብለዋል።

ድህረ-ምርጫን በሰላም ማስተዳደር ማለት የሀላባን
ሰላም፣ አንድነትና የጋራ እድገት መጠበቅ ማለት ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የማዕከላዊ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ደምስ ገብሬ በበኩላቸው የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች የበርካታ ህዝብ ተወካዮች በመሆናቸው የአከባቢውን ሠላም ለማስጠበቅ ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ገልጸዋል።

በመድረኩ ላይም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ዶ/ር ፈለቀች ተ/ማርያም በድህረ-ምርጫ የማህበረሰብ ውይይት ለዘላቂ ሰላም ግንባታ በሚል የመወያያ ሰነድ እየቀረቡ ይገኛል።

በውይይቱ ላይም የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊና የሠላም ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ እንዳለ ወ/አማኑኤል፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ አብርሃም በርታ፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ገመዳ መሀመድ፣ የዞኑ አመራሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የሴቶችና የወጣቶች ተወካዮች፣ የጸጥታና የፍትህ ተቋማት ተወካዮች ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

መረጃዉ የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ነዉ።

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ(ሆሳዕና ፦ ነሐሴ 6/2018)  የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ወቅታዊ ክልላዊ ጉዳዮች አስመልክ...
12/08/2026

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ

(ሆሳዕና ፦ ነሐሴ 6/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ወቅታዊ ክልላዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በሰጡት መግለጫ ክልሉ በአዲስ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ የክልሉን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል።

የሰላሙ ባለቤት ህዝብ በመሆኑ ከህዝብና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በተሰሩ ስራዎች አበራታች ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል ነው ያሉት።

በክልሉ ሰላም ወዳዱ ህብረተሰብ በሁሉም አካባቢዎች በሰላም ወጥቶ በሰላም በመግባት የ24 ሰዓት እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ሌተ ተቀን እየተሰራ ነው።

የፀጥታ መዋቅሩ እስከታችኛው ቀበሌ መዋቅሮች ድረስ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት እና ከፀጥታ ምክር ቤት ጋር በተሰሩ የትብብር ስራዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገበ ስለመሆኑ በጋዜጣዊ መግለጫቸው አብራርተዋል።

የክልሉ መንግስት ከየትኛውም ተግባር ይልቅ የሰላምና ፀጥታ ተግባርን ተቀዳሚ ስራ አድርጎ እየሰራ እና ድጋፍና ክትትል እያደረገ እንደሆነም አቶ ተመስገን አብራርተዋል።

ክልሉን በሁሉም ልማት ዘርፎች የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን በሰላም ፀጥታም ችግር የሌለበት እና ሰላሙ የተረጋገጠ ክልል እንዲሆን በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው በተሰሩም ስራዎች ክልሉ ልማትና ዕድገትን እያፋጠነ ይገኛል።

ምንም እንኳ የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ቢሆንም በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ችግሮች እንዳሉ በመግለጫቸው አብራርተዋል።

በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ በዋልጋ እና ዳርጌ አካባቢ ነዋሪ ህዝብ ለዘመናት በአብሮነትና አንድነት የኖረ እንዲሁም የህብረ ብሔራዊነት እሴት መገለጫው የሆነ ህዝብ መሆኑንም ኃለፊው ተናግረዋል።

እሴቱንም በመጠቀም በግብርና ልማት ስራ ሞዴል የሆኑ አርሶአደሮች የሚኖሩበት አካባቢ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ በተቃራም ከተለያዩ ጽንፈኛ ቡድኖች ጋር በመቀናጀት ጫካ የገቡ ሽፍታዎች መኖራቸውንም ጠቅሰዋል።

እነዚህ ሽፍታዎች ንብረት ከመዝረፍ ባለፈ በመግደል እንዲሁም በባህልና በሀይማኖት ፀያፍ የሆኑ ድርጊቶችን በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።

ቡድኑ የሚያደርሰው ጉደት ብሔር ተኮር እንደሆነ የገለፁት አቶ ተመስገን እራሳቸውን ቀስ በቀስ ፋኖ ነን የሚል ስያሜ ሰጥቶ በመንቀሳቀስ ህዝቡ ትልቅ ጉዳት ሲያደርሱ ቆይተዋል።

እነዚህ ሽፈታዎች በብዛት ወንጀል የሚፈጽመው በአካባቢ የሚኖሩ በጉራጌ ማህበረሰብን ጨምሮ በአጎራባች ዞኖች ላይ ባሉ በኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች፣ ከምባትኛ እና በሌሎች ቋንቋ ተናጋሪዎች ላይ ትኩረት አድርገው ነው ጥቃት የሚፈጽሙት።

ተግባሩ በሌሎች በሀገሪቱ በሚኖሩ ህዝቦች ላይ አንድነትን የሚፈታተን እና ልዩነትን የሚያጎላ እጅግ አደገኛ ሴራ እንደሆነ ተገምግሞ እና ሽፍታዎቹ ስርዓት እንዲይዙ እስከ ቦታ ድረስ በመሄድ ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን በጋዜጣዊ መግለጫቸው አብራርተዋል።

በውይይቱም የቡድኑ አካሄዱ አደገኛና ፀረ ህዝብ እንደሆነ መግባባት የተቻለ ሲሆን ሽፍታዎቹ የቀረበላቸውን የሰላም አማራጮች ተጠቅሞ ወደ ህብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ መግባባት ላይ ተደርሰዋል።

በድኑ ከገቡበት እኩይ ተግባራት ተላቀው በሚፈልጉበት የስራ መስክ መሰማራት እንዳለባቸው ከህብረተሰቡ መግባባት ተፈጥሯል።

በመሆኑም አንዳንዶቹ መንግስት ያመቻቸውን የሰላም አማራጭ ተጠቅሞ የመጡት የተሃድሶ ስልጠና እና ትምህርት ተሰጥቷቸው ወደ ህዝቡ እንዲቀላቀሉ ተደርገዋል ብለዋል።

አንዳንዶቹ ደግሞ ከገቡበት እኩይ ተግባራቸው ወጥቶ በሰላማዊ መንገድ ለመንግሥት እጅ እንዲሰጡ እና በሰላም እንዲኖር በተደጋጋሚ ጥር ቢደረግም አሻፈረኝ በማለታቸውን ተይዘው ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉንም ገልፀዋል።

አንዳንድ አሻፈረኝ ያሉ ሽፍታዎች ሳይሰሩ፣ ሳይደክሙ፣ ንፁህ ዜጋን በመግደል መክበርን መሰረት ያደረጉ እና በዝርፊያ እና በንጥቂያ መኖርን የለመዱ በመሆናቸው መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ ለመቀበል ፈቃደኛ አልሆኑም ብለዋል።

መንግስት የህዝብን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ህገ መንግስታዊ ኃላፊነት የተጣለበት በመሆኑ የክልሉ መንግስት ከፌዴራል እና ከኦሮሚያ ክልል መንግስት በጋራ ህግ የማስከበር ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነም የቢሮ ኃላፊው አብራርተዋል።

ሽፍተን ተቆጣጥሮ ነፃና ሠላማዊ አከባቢ በመፊጠር የህዝቦችን ደህነት ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው።

እነዚህ ሽፍታዎች የጦር መሳሪያ በመታጠቅ በግድያ ላይ የተሰማሩ እና በመንግሥት ፀጥታ አካላት ላይ ጭምር ጉዳት ያደረሱ አካላት እንደነበሩ እና በትክክል የተረጋገጠባቸው ሽፍታዎች እንደሆኑም አብራርተዋል ።

በመሆኑም በቅንጅት በተሰሩ ስራዎች የመንግስትን የሰላም አማራጮችን አንቀበልም ባሉ ሽፍታዎች ላይ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ነው ያሉት።

ተጨባጭ ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ የክልሉን መልካም ገፅታን ለማጠልሸት የሚሰሩ ኃላፊነት በጎደላቸው ሀሰተኛ ሚዲያዎች አሉባልታና ከእውነት የራቀ መረጃ እያሰራጩ ይገኛሉ።

የነዚህ ሚዲያዎች ሀሰተኛ መረጃ በማስረጃ ያልተደገፈ እንዲሁም ክልሉን የማይመጥን እና የህዝቦችን የእርስበርስ አንድነትን የሚሸረሽር እንደሆነም ገልፀዋል።

መንግስት የህዝብን ሰላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚወስደው እርምጃ ብሔር ተለይቶ የሚወሰድ እርምጃ ተብሎ በሀሰተኛ ሚዲያዎች የሚሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ እንደሆነም ገልፀዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ይስተዋል የነበረውን የፀጥታ መደፍረስ ከአካባቢው ህብረተሰብ፣ከኦሮሚያ ክልልና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት አካባቢው ላይ አንፃራዊ ሰላም እንዲሰፍን ተደርጓል።

እንዲሁም በማስቃን እና ማረቆ አካባቢ ያለውንም ችግር ለመፍታት ጥናት እየተደረገ መሆኑን በመግለፅ በጥናቱ ውጤት ላይ ውይይት በማድረግ ችግሩ በጋራ ለመፍታት እየተሰራ ነው።

በሌላ መልኩ ደግሞ በክልሉ እኖር ኤነር መገር እና በቆሴ አካባቢ ሲከሰት የነበረውን አለመግባባት ለመቅረፍ ከሁሉም ማህበረሰብ ጋር ውይይት በማድረግ ችግሩን በጥናት ለመመለስ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ሽፍተን ተቆጣጥሮ ነፃና ሠላማዊ አከባቢ በመፊጠር የህዝቦችን ደህነት ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው።

እነዚህ ሽፍታዎች የጦር መሳሪያ በመታጠቅ በግድያ ላይ የተሰማሩ እና በመንግሥት ፀጥታ አካላት ላይ ጭምር ጉዳት ያደረሱ አካላት እንደነበሩ እና በትክክል የተረጋገጠባቸው ሽፍታዎች እንደሆኑም አብራርተዋል ።

ዜጎች በሀገራቸዉ በየትኛውም አከባቢ በነፃነት የመኖር መብታቸዉ የተከበረ ሲሆን ይህን የሚፃረር አስተሳሰብ እና ድርጊትን በጋራ መታገል ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም ህዝቡ በሀሰተኛ ሚዲያዎች ከሚሰራጩ አሉባልታዎች እራሱን እንዲጠብቅ እንዲሁም ወንጀለኞችን ለህግ አሳልፎ በመስጠት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች በሆሳዕና ማረሚያ ተቋም የመስክ ምልከታና ለታራሚዎች የአልባሳት ድጋፍ አደረጉ።ሆሳዐዕና ፦ ነሐሴ 6/2018 ዓ.ምየማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና...
12/08/2026

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች በሆሳዕና ማረሚያ ተቋም የመስክ ምልከታና ለታራሚዎች የአልባሳት ድጋፍ አደረጉ።

ሆሳዐዕና ፦ ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት “የታረዘን እናልብስ” በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ማረሚያ ተቋም እርምት ላይ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች የአልባሳት ድጋፍ አደረገ።

በድጋፍ ርክክቡ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በክልሉ በርካታ ሰው ተኮር ሥራዎች መከናወናቸውን በመግለፅ የፀጥታ መዋቅሩ ሰላምና ፀጥታን ከማስከበር ጎን ለጎን ባለው አቅም ሁሉ ለሕብረተሰቡ ደራሽነቱን በማረጋገጥ የማኅበረሰብ ተኮር የበጎ ፈቃድ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል።

ኃላፊው እንዳሉት በተለይም በማረሚያ ተቋማት የሚገኙ ዜጎችን መደገፍ ሰብዓዊነትን ከማሳየት ባለፈ ከማረምና ማነፅ ባለፈ መልሶ ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ ጥሩ ሞራል እንደሚሆናቸዉ በማሰብ የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና ከሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ሃይማኖት ተቋማት ፎረም ጋር በመተባበር ይህን ድጋፍ ማድረጋቸዉን በመግለፅ በተቋሙ ጊቢ በህግ ታራሚዎች የተሰሩ ሥራቸዉን በመመልከታቸዉ ደስ እንደተሰኙ ገልፀዋል።

የሆሳዕና ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ኮማንደር ዘውዱ ድኖሮ በበኩላቸው ለታራሚዎች የተደረገው የአልባሳት ድጋፍ አበረታችና አርአያነት ያለው በጎ ተግባር መሆኑን ገልጸው ድጋፉን ላደረጉ አካላት ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በሆሳዕና ከተማ ለሚገኙ ከ1ሺህ በላይ አቅመ ደካማ ወገኖች የአልባሳት ድጋፍ አደረገ(ሆሳዕና፦ ነሐሴ 5/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ...
11/08/2026

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በሆሳዕና ከተማ ለሚገኙ ከ1ሺህ በላይ አቅመ ደካማ ወገኖች የአልባሳት ድጋፍ አደረገ

(ሆሳዕና፦ ነሐሴ 5/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ''የታረዘን እናልብስ''በሚል መሪ ቃል ከክልሉ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና ከሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ሃይማኖት ተቋማት ፎረም ጋር በመተባባር ለአቅመ ደካማ ወገኖች የአልባሳት ድጋፍ አድርገዋል።

በድጋፍ ርክክብ መርሃ -ግብር የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እንደተናገሩት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በክልሉ በርካታ ሰው ተኮር ስራዎች ተሰርተዋል።

የፀጥታ መዋቅር ሠላምና ፀጥታን ከማስከበር ጎን ለጎን ባለው አቅም ሁሉ ለህብረተሰቡ ደራሽነቱን እያረጋገጠ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ይህ በጎ ተግባር ለአንድ ጊዜ ብቻ ፍላጎት ለማሟላት የሚደረግ ስራ ሳይሆን በትውልድ ላይ መልካም ዘር መዝራት እንደሆነ በመግለፅ ቀጣይ ትውልድ የመደጋገፍና መተባበር ልምዳቸውን እንዲያጎለብቱ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

የሰው ልጅ የህሊና እርካታ ማግኘት የሚችለው የተቸገሩትን ሲረዳ እንደሆነ የገለፁት አቶ ተመስገን መረዳዳት የእርስበርስ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚያጠናክር እንደሆነ ገልፀዋል።

በሆሳዕና ከተማ የተደረገው በጎ ተግባር የሚቀጥል እንደሆነ በመጠቆም ይህ መልካም ስራ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል።

የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትልና የሰላም እሴት ግንባታና ብዝሃነት አያያዝ ዘርፍ ኃላፊ አቶ እንዳለ ወ/ አማኑኤል እንደገለፁት የሀይማኖት ተቀዳሚ ተግባራቸው ሰላምን ለትውልድ መስበክ፣ፍቅርና አንድነትን ማስተማር እንደሆነ ተናግረዋል።

የተቸገረውን መርዳት የመንፈስ እርካታን የሚሰጥና የበጎነት ማሳያ ነው ብለው መደጋገፍ፣ መተሳሰብ እና መረዳዳትን ሀይማኖታዊ አስተምህሮ ዋነኛ ተግባር ነው ሲሉም ገልፀዋል።

የሀይማኖት አባቶች የህብረተሰቡ የህሊና ማዕከል እና የሞራል መስታወት በመሆናቸው ይህን መልካም ስራ በየ ቤተእምነታቸው የበለጠ ማስረጽ ይገባቸዋል ብለው በእለቱ የተደረገው ድጋፍም ከ1 ሺህ በላይ ለሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎች የተደረገ ድጋፍ እንደሆነ ተናግረዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ በበኩላቸው በየትኛውም ሀይማኖት ተቋማት መደጋገፍና መረዳዳት ግንባር ቀደም ተግባር እንደሆነ ገልፀዋል።

በጎነትን ማድረግ ለራስም ይሁን ለሀገር ግንባታ የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ በመሆኑ በቀጣይም በተለያዩ ምክንያቶች ለተቸገሩ ወገኖች ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ ሁሉም ሰው የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ድጋፍ የተደረገላቸውም በተደረገው ድጋፍ መደሰታቸውን በመግለፅ የመተባበር እና የመደጋገፍ ባህል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ገልፀው ይህን የኢትዮጵዊነት እሴት የበለጠ ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።

በመጨረሻም ቡድኑ በሆሳዕና ከተማ ማረሚያ ተቋም ለሚገኙ ታራሚዎች የአልባሳት ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም የታራሚዎች አያያዝን በማየት በተቋሙ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ተመልክቷል ።

11/08/2026
በሀዲያ ዞን ብሔራዊ የሰላም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስልጠና መድረክ ተካሄደ።።ሆሳዕና፣ሐምሌ 23/2018 (ሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽን)።።የሰላም ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ...
30/07/2026

በሀዲያ ዞን ብሔራዊ የሰላም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስልጠና መድረክ ተካሄደ

።።ሆሳዕና፣ሐምሌ 23/2018 (ሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽን)።።

የሰላም ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን እና ከሆሳዕና ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶችና ሴቶች ክንፍ ጋር በመቀናጀት ብሔራዊ የሰላም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የስልጠና መድረክ አካሄደ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የሰላም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ እንዳለ ወ/አማኑኤል በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት፣ "በጎ ፈቃደኝነት" የሰዎች መልካም ፈቃድ ብቻ ሳይሆን የፍቅር፣ የርህራሔ እና የጋራ ኃላፊነት መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል።

በየዓመቱ የሚካሄደው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የወጣቶችን እምቅ አቅም እና የሴቶችን ጠንካራ ማህበራዊ መሰረት በማስተባበር፣ የማህበረሰባችንን ዘላቂ ችግሮች የምንቀርፍበት ዋና መሳሪያችን ነው ብለዋል።

አያይዘውም በአካባቢያቸው ያሉ ወጣቶችና ሴቶችን የማንቀሳቀስ፣ የማስተባበር እና ውጤታማ ሥራዎችን የመሥራት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ረዳት የመንግስት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፍሰሃ ታደሰ በበኩላቸው፣ የ2018 በጀት ዓመት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራትን ለማከናወን የጋራ መግባባት ተፈጥሮ በ16 ተግባራት ላይ የጋራ ዕቅድ ተይዞ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቁመዋል።

አክለውም የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማህበረሰብን በማሳተፍ በጎነትን፣ አብሮነትን እና ትብብርን እንዲሰርጽ በማድረግ ማህበራዊ ትስስርን፣ ሰላምን እና ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን ለማጎልበት ወሳኝ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል።

የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ሀብታሙ ዮሴፍ እና የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፀጋነሽ ደመቀ በየበኩላቸው፣ ወጣቱን በበጎ ተግባር በማሰማራት እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ለተቸገሩ ማህበረሰብ በመስጠት ሰብአዊ ግዴታቸውን በቁርጠኝነት ማወጣት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ፀጋዬ ያሲን በበኩላቸው፣ የበጎ ሥራ ለሚቀበለው ሰው ብቻ ሳይሆን ለሰጪውም ትልቅ በረከት መሆኑን ጠቁመው፤ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲሳተፉ ችግር ፈቺነትን እና ከሰው ጋር የመግባባት ጥበብን እንደሚማሩ ገልጸዋል። እውነተኛ ደስታ የሚገኘው ለራስ በመኖር ሳይሆን ለሌሎች ተስፋ መሆን ሲቻል ነው ብለዋል።

የኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ልየው መዝገቡ የስልጠና ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት፣ የበጎ ተግባር መደጋገፍና ማህበራዊ ወንድማማችነትን ማጠናከር፣ የተቸገሩትን መርዳት፣ አረጋውያንን መንከባከብ እና ልጆችን ማስተማር የህሊና እርካታን ብቻ ሳይሆን የወደፊት ሀገራችንን ጠንካራ የሰላም መሠረት ለመገንባት የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።

በዕለቱ በተደረገው ስልጠና የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት፣ አመራሮች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች እና ሌሎችም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

ዘገባው፡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  ፖሊስ ኮሚሸን ቢሮ እና የትምህርትና ሥልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለሥልጣን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነውን የአንድ አቅመ ደካማ አባት ቤት የግንባታ ሥ...
30/07/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሸን ቢሮ እና የትምህርትና ሥልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለሥልጣን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነውን የአንድ አቅመ ደካማ አባት ቤት የግንባታ ሥራ በዶዮገና ከተማ አስጀምረዋል ።

ሐምሌ 23/2018 ዓ/ም ዶዮገና

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን የ2018 ዓ/ም የክረምት የበጎ ሥራ መርሐ ግብር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሸን ቢሮ እና የትምህርትና ሥልጠና ጥረትና ቁጥጥር ባለሥልጣን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነውን የአንድ አቅመ ደካማ አባወራ ቤት ግንባታ ሥራ በዶዮገና ከተማ በይፋ አስጀምረዋል ።

የቤት ግንባታውን በቦታው ተገኝተው ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ካሣ እንደገለጹት ይህ የመኖሪያ ቤት ግንባታ በፖሊስ ኮሚሸን ቢሮ፣ የትምህርትና ሥልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለሥልጣን፣ በከተማ አስተዳደር እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማስተባበር በጥራት ተሠርቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለባለቤቱ ርክክብ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

ይህ ተግባር ከግለሰብ ጀምሮ የማህበረሰብ፣ የክልል፣ የሃገርና የትውልድ ሃብትና ቅርስ ከመሆን አልፎ ሃገር የሚያፀና እና መልካም ተግባር የሚዘራ አሻራ መሆኑንም ኮሚሽነር ሽመልስ ካሣ ተጨምረው ገልፀዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የትምህርትና ሥልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለሥልጣን አቶ ራመቶ ቦካ በክረምቱን ወራት የሚከናወነው ይህ የበጎ ፈቃድ ሥራ ዓመታትን ያስቆጠሩና ያረጁ የአቅመ ደካማ ግለሰቦች መኖሪያ ቤቶችን በዘመናዊ እና ምቹ በሆነ መልኩ ለመሥራት ያለመ ነው ብለዋል ።

አቶ ራመቶ አክለዉም ይህ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር የዜጎችን ማህበራዊ ትስስርና መረዳዳትን የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ በክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ ምክንያት ሊቸገሩ የሚችሉ ወገኖችን ችግር ቀድሞ ለመቅረፍ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

የዶዮገና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ግሩም ወ/ማሪያም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡ የቆየ እሴት መሆኑን በመርሃ-ግብሩ ላይ የገለፁ ሲሆን ዛሬ የተጀመረው የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ስራ መንግስትና የከተማዋ ነዋሪዎች ለአቅመ ደካሞች ያላቸውን ፍቅር እና አጋርነት የሚያሳዩበት እንደሆነ ተነግሯል፡፡

አቶ ግሩም አክለዉም የዘንድሮው የክረምት ወራት ቤት የመገንባት መርሃ-ግብር በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ ባለሀብቶችን፣ በጎ አድራጊዎችንና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በስፋት በማስተባበር የሚያከናወን እንደሆነ ገልጸዋል ።

በዕለቱ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በዕለቱ ክቡር እንግዶች፣ በከተማ አስተዳደሩ አስተባባሪ አካላት፣ አመራሮች እንዲሁም በተለያዩ አካላት ተካሄዷል ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ በአረቅጥ ከተማ አረንጓዴ አሻራ በማኖርና  ለአንዲት እናት የቤት ግንባታ ስራ አስጀመረ ።ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
30/07/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ በአረቅጥ ከተማ አረንጓዴ አሻራ በማኖርና ለአንዲት እናት የቤት ግንባታ ስራ አስጀመረ ።

ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና)

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል ሀገራዊ መሪ ቃል በጉራጌ ዞን አረቅጥ ከተማ በመገኘት አረንጓዴ አሻራ በማኖርና ለአንዲት አቅመ ደካማ እናት የቤት ግንባታ ስራ አስጀመረ።

በማስጀመሪያ መርሐግብሩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ተመስገን ካሳ፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በህብረተሰቡ ዘንድ መረዳዳትን፣ አብሮነትንና ዘላቂ ሰላምን የሚያጠናክር መሆኑን አብራርተዉ የሚተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የአካባቢዉ ነዋሪ ኃላፊነት እንዲወስድ ጠቁመዋል።

ኃላፊው በንግግራቸው የበጎነትን ጥልቅ ማህበራዊ ትርጉም ሲያስረዱ "ዛሬ የምንተክለዉ ችግኝና የምንሰራው ቤት ብቻ ሳይሆን ተስፋን እና ወንድማማችነትን ጭምር ነው፤ የግለሰብ ቤት ሲስተካከል ማህበረሰብ ይስተካከላል፤ ማህበረሰብ ሲስተካከል ደግሞ ሐገር ትበለፅጋለች።" በማለት አስገንዝበዋል።

አቶ ተመስገን አያይዘውም የሰላም እና ፀጥታ ስራ ከህብረተሰቡ ሁለንተናዊ እድገትና ማህበራዊ ደህንነት ጋር በቀጥታ የተቆራኘ መሆኑን ጠቅሰው፣ በጎነት የሰላም መሰረት በመሆኑ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን አሻራ ሊያሳርፍ ይገባል ብለዋል።

በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የአረቅጥ ከተማ ከንቲባ አቶ መንግስቱ ሹሜ በበኩላቸው፣ የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ይህንን የተቀደሰ በጎ ተግባር በከተማቸው መጀመሩ ትልቅ ክብር መሆኑን ገልጸው፣ ለተደረገው የቤት መስራት ድጋፍ በከተማው አስተዳደርና በነዋሪዎች ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

ከተማ አስተዳደሩ የተጀመረው የቤት ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአቅመ ደካማዋ እናት ርክክብ እንዲደረግ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ከማድረግ ወደኋላ እንደማይልም አረጋግጠዋል።

ከንቲባው አክለውም ወጣቶች፣ ባለሀብቶች፣ የመንግስት ሰራተኞች እና መላው የከተማው ነዋሪዎች በቀጣዮቹ የክረምት ወራት በሚከናወኑ በጎ ተግባራት ላይ በንቃት እንዲሳተፉና አቅመ ደካሞችን የመደገፍ ባህልን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል። በጎነት የኢትዮጵያውያን የቆየ እሴት መሆኑን በማስታወስ፣ ይህን መልካም ባህል ትውልዱ ጠብቆ ሊያቆየው እንደሚገባም ተናግረዋል።

ለአቅመ ደካማዋ እናት የሚገነባው ቤት በውስጡ አስፈላጊውን መሰረታዊ ግብዓቶች ያሟላ እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን፣ እናትየውም በተደረገላቸው ድጋፍ የተሰማቸውን ጥልቅ ደስታ ገልጸው አካባቢውን እና አስተባባሪዎቹን መርቀዋል።

በክረምት ወራት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ማህበረሰባዊ ትስስርን ከማጠናከር ባሻገር፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍና አካባቢን በመንከባከብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ። የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮም የህዝብን ደህንነት ከማስጠበቅ ዋና ተልዕኮው ጎን ለጎን፣ ይህንን ማህበራዊ ኃላፊነት በመወጣት ረገድ አርአያነት ያለው ተግባር ፈጽሟል። የዘንድሮው መሪ ቃል የሚያመላክተውም እያንዳንዱ ዜጋ በሚያደርገው በጎ ተግባር የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ማፋጠን እንደሚቻል ነው።

የዕለቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሐግብር ማጠናቀቂያ ላይ በክብር እንግዶቹ እንዲሁም በከተማው ነዋሪዎች እና በወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ሰፊ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ተከናውኗል። ይህ የችግኝ ተከላ አካባቢን ከመጠበቅና የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ፣ ዛሬ የተዘራው በጎነት ነገ አድጎ የሰላም እና የልማት ጥላ ሆኖ እንደሚያገለግል ታምኖበት የተከናወነ መሆኑ ተጠቁሟል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የዘንድሮውን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በደም ልገሳ፣ በትምህርት ማጠናከሪያ፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ አቅመ ደካሞችን በማቋቋም፣ እንዲሁም የትራፊክ ደህንነትን በማረጋገጥ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በስፋት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም መረዳት ተችሏል።

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share