Hadiya zone Government Communication

Hadiya zone Government Communication የሀድያ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የሆነ የመንግሥት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት በመገንባት መንግስትና ሕዝብን ማገናኘት

This is the offical facebook home page of Hadiya Zone Communication

‹ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የሆነ የመንግሥት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት በመገንባት መንግሥትንና ሕዝብን ተጠቃሚ በማድረግ አንድ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማኀበረሰብን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ ነው።

ምክር ቤቱ የዞኑን የምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በሙሉ ድምፅ አፀደቀየሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ...
02/09/2026

ምክር ቤቱ የዞኑን የምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በሙሉ ድምፅ አፀደቀ

የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው የዞኑን የ2018 በጀት ዓመት የምክር ቤት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2019 ዕቅድ ለምክር ቤቱ ቀርበው በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ነሐሴ 27/2019 ዓ.ም (ሀዲያ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ)-ሆሳዕና

የበጀት ዓመቱን የምክር ቤት ዕቅድ አፈፃፀም ርፖርት ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤዋ ክብርት ወ/ሮ አለሙነሽ ክፍሌ ባለፈው በጀት ዓመት ምክር ቤቶች የመንግሥትና የህዝብ ሀብት በአግባቡ በሥራ ላይ ማዋላቸውን የመከታተል ሥራ ማከናወኑን በሪፖርቱ አመላክተዋል ።

በተያዘው በጀት ዓመት ምክር ቤቶች ባለፈው ዓመት በዕቅድ አፈፃፀም ላይ የተስተዋሉ የመልካም አስተዳደርና በአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ለመፍታት በትኩረት እንደሚሠራም በሪፖርቱ ተብራርቷል።

ምክር ቤቶች የህዝብ ያለአግባብ የምባክነውን ሀብት የማስመለስ ሥራ በትኩረት ይሠራል ያሉት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ ተቋሙ የመንግስትን መመሪያዎችና ደንቦችን ለህዝብ የማድረስና የማስገንዘብ ኃላፊነት እንደሚወጣ አስረድተዋል።

የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ
ባለፈው በጀት ዓመት ምክር ቤቱ እናቶችንና ህፃናትን በበጎ አገልግሎት ሥራ የመደገፍና የማጠናከር ሥራ ማከናወኑን አብራርተዋል።

ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልማት እንደመጣ ከተፈለገ ምክር ቤቶችን ማጠናከርና መደገፍ እንደሚገባ ዋና አፈ-ጉባኤዋ ገልጸዋል።

ምክር ቤቱ በቀረበው የምክር ቤት ዕቅድ አፈፃፀምና በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ላይ አስተያየቶችና ማብራሪያ ከተሰጠ በኋላ በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።

በደገለ በምቦሬ

የሀድያ ዞን ምክር ቤት የ2019 በጀት ዓመት ከ15.4 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ።።ሆሳዕና፣ ነሐሴ 27/2019 (ሀዲያ ዞን  ኮሙኒኬሽን)።።የሀድያ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር ...
02/09/2026

የሀድያ ዞን ምክር ቤት የ2019 በጀት ዓመት ከ15.4 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ

።።ሆሳዕና፣ ነሐሴ 27/2019 (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)።።

የሀድያ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት 27ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ የዞኑን የ2019 በጀት ዓመት 15 ቢሊዮን 490 ሚሊዮን 720 ሺህ 181 ብር የሥራ ማስፈጸሚያ በጀት በሙሉ ድምፅ አፀደቀ።

በጉባኤው ላይ የዞኑን የሀብት አከፋፈል ቀመር ያቀረቡት የምክር ቤቱ የኢኮኖሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሳሙኤል ዘመድኩን እንደተናገሩት፤ የተመደበው በጀት በዞኑ ለሚከናወኑ የልማት ሥራዎችና የመንግሥት አገልግሎቶች የሚውል በመሆኑ፣ በቁጠባና ለታለመለት ዓላማ ብቻ ሥራ ላይ መዋል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

የዞኑ ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ዱናሞ በበኩላቸው፣ የተከፋፈለው በጀት የዞኑን ማዕከል ጨምሮ በዞኑ ሥር ለሚገኙ የወረዳና የከተማ አስተዳደሮች በፍትሐዊነት የተሸነሸነ መሆኑን ገልጸዋል። ኃላፊው የበጀት ምንጮቹን ዝርዝር እንደሚከተለው አቅርበዋል።

፨፨፨፨፨የበጀት ምንጮች ዝርዝር፨፨፨፨፨

👉ከክልል መንግሥት ድጎማ (ግምጃ ቤት)፦ 6,648,869,314.00 ብር
👉ውስጥ ገቢ በድምሩ 8,800,266,573.00 ብር
👉ከዞኑ መደበኛ ገቢ፦ 6,513,380,037.00 ብር
👉ከማዘጋጃ ቤት ገቢ፦ 1,831,725,938.00 ብር
👉ከጤና ተቋማት ገቢ፦ 231,343,799.00 ብር
👉ትምህርት ተቋማት ገቢ፦ 223,816,189.00 ብር
👉ከውጭ ዕርዳታ፦ 41,584,904.00 ብር
👉ጠቅላላ የፀደቀ በጀት፦ 15,490,720,181.00 ብር

የምክር ቤቱ አባላት በቀረበው የበጀት ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ የዞኑን የገቢ አቅም ማሳደግ እንደሚገባና የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ ብቻ መዋል እንዳለበት በማስመር በጀቱን በሙሉ ድምፅ አፅድቀውታል።

የሀድያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛው ቀን ውሎው ቀጥሎ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል።

በደገለ ባምቦሬ

የመምሪያውን ተጨማሪ መረጃዎች ለማግኘት !
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/17kWmHxKrx/
በቴሌግራም
https://t.me/Hadiya_zone_communication
በቲዩተር
https://x.com/HadiyagovCom
በኢንስታግራም
https://www.instagram.com/hadiyazonecommnuication
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/
በቲክቶክ
https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-934AKXOx6Eq
አማራጮችን ይጠቀሙ!!
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

02/09/2026

የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ተኛ ዓመት የስራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤ ! HADIYYI ZOO’N ARANCHI MI’N SOO’L KO’L TOMMII SOO’L BAX HIINCHI LAMIYYII LAMA’LLI BEYYAMMI \DUMMICHCHA.

02/09/2026

HADIYYI ZOO’N ARANCHI MI’N SOO’L KO’L TOMMII SOO’L BAX HIINCHI LAMIYYII LAMA’LLI BEYYAMMI \DUMMICHCHA. Live

02/09/2026

HADIYYI ZOO’N ARANCHI MI’N SOO’L KO’L TOMMII SOO’L BAX HIINCHI LAMIYYII LAMA’LLI BEYYAMMI \DUMMICHCHA.

ምክር ቤቱ የዞኑን የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ በሙሉ ድምፅ አፀደቀ።።ሆሳዕና፣ነሐሴ 27/2019 (ሀዲያ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን)።።የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት የሥራ ...
02/09/2026

ምክር ቤቱ የዞኑን የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ በሙሉ ድምፅ አፀደቀ

።።ሆሳዕና፣ነሐሴ 27/2019 (ሀዲያ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን)።።

የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤ በሁለተኛ ቀን ውሎው የዞኑን የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣ በተያዘው ዓመት ህዝቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሠራ ገልጸዋል።

ዋና አስተዳዳሪው አክለውም በበጀት ዓመቱ የሚከተሉት ዋና ዋና ጉዳዮች አፅንኦት ተሰጥቷቸው እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፦
👉የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመንና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት
👉በሁሉም አካባቢዎች የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ሥራዎችን ማስፋፋት
👉የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የከተሞች ዕድገትና የከተማ-ገጠር የልማት ትስስርን ማጠናከር
👉የገቢ አሰባሰብን በማሻሻል ራስን የመቻል ጥረትና ኢንቨስትመንትን መሳብ

የምክር ቤቱ አባላት በቀረበው ዕቅድ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወኑ ተግባራት በደረጃ ተለይተው በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ አንስተዋል።
ከዚህ አኳያ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና መሠረተ ልማት ዘርፎች ለተነሱ ጥያቄዎች በዞኑ ዋና አስተዳዳሪና በሚመለከታቸው የተቋም ኃላፊዎች ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ምክር ቤቱ የቀረበውን መሪ ዕቅድና በተሰጡ ምላሾች ላይ ተመሥርቶ ከተወያየ በኋላ ዕቅዱን በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል።

በደገለ በምቦሬ

የመምሪያውን ተጨማሪ መረጃዎች ለማግኘት !
በፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/17kWmHxKrx/
በቴሌግራም
https://t.me/Hadiya_zone_communication
በቲዩተር
https://x.com/HadiyagovCom
በኢንስታግራም
https://www.instagram.com/hadiyazonecommnuication
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/
በቲክቶክ
https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-934AKXOx6Eq
አማራጮችን ይጠቀሙ!!
ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት *******************እየተጠናቀቀ በሚገኘ...
02/09/2026

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
*******************

እየተጠናቀቀ በሚገኘው 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶችን እንዳስመዘገበች የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ የዘንድሮ የጳጉሜን ቀናት የሚከበሩበትን ዓውድ፣ የቀናቱን ስያሜ እና መሪ መልዕክት ይፋ ያደረገበትን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

መግለጫውን የሰጡት የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ “ጳጉሜን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ወር ብሎ ለማክበር የሚያስችሉ ስኬቶች እየተጠናቀቀ ባለው ዓመት መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡

ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ቴክኖሎጂ ነክ ዓመታዊ ስኬቶችን በመግለጫቸው ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ የጳጉሜን ቀናት በልዩ ልዩ ስያሜዎች እና ኹነቶች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አመላክተዋል፡፡

ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተሳተፉበት ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተካሄደበት፣ ኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን በፅኑ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ አካታች እና የነበሩ ልዩነቶችን በመፍታት የጋራ ትልሞች ላይ እንዲተኮር የሚያስችል ሀገራዊ ምክክር በስኬት የተጠናቀቀበት፣ የውስጥ አንድነቷ የተጠናከረ እና የዲፕሎማሲ ዐቅሟ ያደገች ኢትዮጵያ የታየችበት ዓመት እንደነበር አንስተዋል፡፡

ከኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አንጻር የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ለመፍጠር በወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ ቀውሶች ጭምር ታልፎ ስኬት የተመዘገበበት፣ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር የተቻለበት፣ የዕዳ ጫና በከፍተኛ ደረጃ የቀነሰበት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅም ከ1.5 ትሪሊዮን ብር የተሻገረበት፣ የኢንዱስትሪ ምርታማነት እና የውጭ ምንዛሪ ግኝት ታሪካዊ ዕድገት ያስመዘገበበት፣ የወጪ ንግድ ገቢ ከ10.2 ቢሊዮን ዶላር የተሻገረበት፣ በአንድ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ብቻ ከ13.2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የኢንቨስትመንት የመግባቢያ ሰነድ የተፈረመበት እና በአብዛኛው የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወደ ማውጣት ደረጃ የተሸጋገሩበት፣ የግብርና ምርት እና ምርታማነት በጋ ከክረምት በግብዓት አቅርቦት ታግዞ በከፍተኛ ደረጃ የጨመረበት ስኬታማ ዓመት ነበር፡፡

የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ያስቻሉ ከ100 በላይ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቶች የተስፋፉበት፣ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በፅኑ መሠረት የሚያስቀምጥ እና ማኅበራዊ መስተጋብርን የሚያጎለብት ስኬታማ ምክክር የተደረገበት፣ የሕዝቡን የማኅበራዊ መሻቶች ለማሳካት ሰፋፊ የበጎ አድራጎት እና የመሠረተ ልማት ማስፋፋት ሥራዎች የተከወኑበት በውጤቱም ኢትዮጵያን ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበት ዕድገት ማሸጋገር የተቻለበት ዓመት እንደነበር አቶ ከበደ በመግለጫቸው አመላክተዋል፡፡

በታዳሽ ኃይል አቅርቦት፣ ግዙፍ መሠረታዊ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት እና አዳዲስ መሠረተ ልማቶችን ወደ ግንባታ በማስገባት የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶችንም ዳስሰዋል፡፡

የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ እና የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጀመር ከሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል በሚኒስትር ዴኤታው በአብነት ተነሥተዋል፡፡

እነዚህን ስኬቶች፣ ከተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እና በዕቅድ ከተያዙ ሀገራዊ ትልሞች ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ መሆኗንም አመላክተዋል፡፡

የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል የጋራ መሪ መልዕክት ይከበራሉ፡፡

ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፣ ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን፣ ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን፣ ጳጉሜን 4- የኅብር ቀን እና ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን በሚሉ ስያሜዎች እንደ ቅደም ተከተላቸው በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበሩ ያስታወቁት ሚኒስትር ዴኤታው ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል፡፡

ዜጎች በአዲስ ዓመት ለግል ስኬቶቻቸን እንደሚያቅዱት ሁሉ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ብልጽግናም የሚጫወቱትን ሚና ታሳቢ እንዲያደርጉ፣ የመንግሥትን ፖሊሲ እና ስትራቴጂ እንዲሁም ዕቅድ ተገንዝበው ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ ለማነሣሣት ቀናቱ እንደሚከበሩም ገልጸዋል፡፡

የጳጉሜን ቀናቱን ስያሜ መሠረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄዎች፣ የበጎ አድራጎት እና ማዕድ ማጋራት ተግባራት፣ ነፃ ጤና ምርመራ፣ የደም ልገሳ፣ የፓናል ውይይት እና መሰል መርሐ ግብሮች እንደሚኖሩ መግለጻቸውን የአገልግሎቱ መረጃ አመላክቷል፡፡EBC

02/09/2026
02/09/2026

ቀጥታ ከሀድያ በህል አዳራሽ የሀድያ መንግስት ኩሙኑኬሽን!

የሰዎች እርስ በርስ የመረዳዳት ባህል  ዘመናትን የተሻገረ ነው :-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) (ሆሳዕና፣ነሐሴ 27/2018)(ሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽን )ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ...
02/09/2026

የሰዎች እርስ በርስ የመረዳዳት ባህል ዘመናትን የተሻገረ ነው :-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

(ሆሳዕና፣ነሐሴ 27/2018)(ሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽን )

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ልኡካን ቡድን በጽ/ቤታቸው አቀባበል አደረጉ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የረጅም ዘመናት ታሪክ አለው ብለዋል።

የሰዎች እርስ በርስ የመረዳዳት ሂደት ዘመናትን የተሻገረ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ በአድዋ ታሪክ ወጣቶች እና ሴቶች ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውሰዋል።

ሴቶች ቀለብ ማዘጋጀት ወጣቶች ደግሞ በአርበኝነት ሀገርን የማዳን ትግል ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል።

ወጣቶች ሚዛናዊ አስተሳሰብ እንዲሰርጽ በማድረግ በሀገር እድገት ላይ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባም አመላክተዋል።

ወጣቶች በቴክኖሎጂው ዘርፍ የሚኖራቸውን ተወዳዳሪነት በማላቅ ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባም ጠቅሰዋል።

ወጣቶች ለህዝቦች አንድነት እና ትስስር በጋራ መስራት እንዳለባቸው የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህም ኢትዮጵያ የጀመረችውን ጉዞ ማጠናከር ይጠበቃል ሲሉም አብራርተዋል።

ክልሉ በአጭር ጊዜ ተመስርቶ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ በርካታ አብነታዊ ስራዎችን ተግባራዊ ማድረጉን ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በክልሉ የልማት ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ በመገንባት ስራ ማስጀመር መቻሉን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት፣የመሰብሰቢያ አዳራሽ እና ቤተ መንግስት በስድስት ወራት ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።

በክልሉ በሁሉም ዘርፍ የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እያደገ ስለመምጣቱም ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ በበኩላቸው "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ሀሳብ "እየተካሄ ያለው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በህዝቦች መካከል ጠንካራ አንድነት እና ትስስር ይፈጥራል ብለዋል።

የዘንድሮውን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ልዩ የሚያደርገው ኢትዮጵያ በልማት፣በሰላም በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ በላቀ ከፍታ ለመሻገር በምታደርገው ማዕቀፍ ውስጥ በሆነችበት ጊዜ መሆኑን አቶ ጌታቸው ጠቁመዋል።

በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ወጣቶችን በማቀናጀት አካባቢን ከመቀየር ባሻገር የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እና ወዳጅነትን እንደሚያጠናክር ኃላፊው አስታውቀዋል።

በአለም አቀፍ ደረጃ ወጣቶች ድንበር ተሻግረው እንዲሰሩ ማድረግ በመቻሉ የወጣቶችን አቅም ከማሳደጉም ባሻገር አህጉራዊ አንድነትና ትስስር እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል።

ወጣቶች ከተለያዩ የአለም አቀፍ ክፍሎች ተንቀሳቅሰው በማህበረሰብ ልማት በአካባቢ ጥበቃ እና በትምህርት ዘርፍ አገልግሎት እየሰጡ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶች ጉዳይ እና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ኮሚሽነር ማርቆስ ማቲዎስ እንደገለጹት በክልሉ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋና አቅርበዋል ።

የክልሉ መንግስት ወደ ቀድሞ ቤታችን ሲልከን በደም የተጋመደ አንድነታችንን ይበልጥ እንድናጠናክር ነው ብለዋል።

ከወንድሞቻችን ጋር በደም ልገሳ፣ማዕድ ማጋራት ችግኝ ተከላ እና በሌሎችም የበጎ ፈቃድ ስራዎች ላይ ተሳትፎ እንደሚያደርጉም ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።

ወጣቶቻችንን ሀብት ከማዳን ባለፈ ለወገኖቻችን በነጻ የምንሰጠው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አብሮነትን በማጠናከር ረገድ የጎላ አበርክቶ አለው ብለዋል።

የክልሉ ወጣቶች ክንፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወጣት አብዱ ድንቁ እንደገለጸው በክልሉ ያለውን እምቅ የመልማት አቅም በማጠናከር በሁሉም ዘርፍ የላቀ ውጤት ተመዝግቧል ብሏል።

በክልሉ ለተመዘገበው የላቀ ውጤት የአመራር ቁርጠኝነት እና የስራ ባህል ለውጥ መሆኑን ወጣት አብዱ አስረድቷል።

የክልሉ ኮሙኒኬሽን

Address

Centeral Ethiopia Region
Hossana

Telephone

+251465551908

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya zone Government Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share