የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኮሚዩኒኬሽን

የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኮሚዩኒኬሽን Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኮሚዩኒኬሽን, Political organisation, Central Ethiopia Region, Hadiya Zone, Hossana.

ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት ከመንግስት ጥረት ባሻገር የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚያስፈልግ ተገለጸሆሳዕና፤ ነሐሴ 18/12/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሕጋዊ የ...
24/08/2026

ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመግታት ከመንግስት ጥረት ባሻገር የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ

ሆሳዕና፤ ነሐሴ 18/12/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀዲያ ዞን ሕጋዊ የውጭ አገር የሥራ ስምሪት "የዉጭ ሀገር የሥራ ስምሪት አቋራጭ መንገድ የለዉም" በሚል መሪ ቃል ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

መድረኩ በሀዲያ ዞን ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ መምሪያ፣ በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያና በቴክኒክና ትምህርት ስልጠና መምሪያ ቅንጅት መዘጋጀቱም ተመላክቷል።

ለንቅናቄዉ መድረክ ዉይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ በአቶ አብርሃም ባቦሬ እና በአቶ አዲሴ አዉቶ ቀርቦ ዉይይት ተካሂዷል።

የሀዲያ ዞን ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ መምሪያ ኃላፊ አቶ አብርሃም ባቦሬ በወቅቱ እንደተናገሩት፥ ወጣቶች በአካባቢያቸዉ እንዲረጋጉ መንግስት ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር እስካ ቀበሌ ድረስ በርካታ ሥራዎችን እየሰረ ይገኛል ብለዋል።

አክለዉም በበጀት ዓመቱ ከ7 ሚሊዮን በላይ ገንዘብ ከክልል መንግስት መዉረዱን ጠቁመዉ፥ ይህም ገንዘብ በየመዋቅሩ ማህበር ተደራጅተዉና ቢዝነስ ፕላን አዘጋጅተዉ ለተዘጋጁ ወጣቶች መሰራጨቱን ያሳወቁት አቶ አብርሃም፥

በዘርፉ መንግስት በተቋም ግንባታ ላይ አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዉ፤ ይህ ማለትም በሰዉ ሀይልና በመረጀ ተደራሽነትና ማዘመን ላይ ጠንከራ ስራ መስራት ነዉ ብለዉ፥

ይህ መድረክ በተዋረድ በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች መካሄድ እንዳለበትና ሪፖርት ለሚመለከታቸዉ አካላት በተቀመጠለት መርሃ ግብር መሰረት መድረስ አለበት ብለዋል።

በመድረኩ የተገኙት የሀዲያ ዞን ሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲሴ አውቶ በበኩላቸዉ፤ የመድረኩ ዋና ትኩረት ግንዛቤ የመፍጠር፣ ስልጠና የመስጠትና የሥራ ዕድል ፈጠራ ናቸዉ ብለዋል።

ትልቁ የመንግስት ግብ ለራሱ፣ ለቤተሰቡና ለሀገሩ የሚጠቅም ዜጋ መፍጠር ነዉ ያሉት አቶ አዲሴ አዉቶ፥

ለዚህም በሀይማኖት ተቋማት፣ በዕድሮችና መሰል ማህበራዊ መድረኮች ላይ በማህበረሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዉጭ ሀገር እና ለሀገር ዉስጥ የሥራ ስምሪት ለሚፈልጉ ዜጎች ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጀምሮ በየደረጀዉ ያሉ ባለድርሻ የሆኑ ተቋማት በርካታ ሥራዎችን በመሥራት ላይ እንደምገኙ ገልፀዉ፥ ዘርፉ ለተገልጋዮች የተሳለጠ አገልግሎት እንዲሰጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥረት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

ከመድረኩ ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

27ኛው ሀገር አቀፍ የጤና ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ነውሆሳዕና፣ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት በሆሳ...
24/08/2026

27ኛው ሀገር አቀፍ የጤና ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው

ሆሳዕና፣ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት በሆሳዕና ከተማ የሚካሄደውን 27ኛውን ሀገር አቀፍ የጤና ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተቀናጀ መልኩ እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚዘጋጀው ይህ ጉባኤ በጤና ዘርፉ የተመዘገቡ ውጤቶችንና የተገኙ ልምዶችን በመገምገም የጤና ሥርዓቱን ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው።

በዚህ ሀገር አቀፍ መድረክ ከሁሉም ክልሎች የተወጣጡ እንግዶች፣ በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች፣ የጤናውን ዘርፍ የሚደግፉ አጋር ድርጅቶች እና የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ተሳታፊ እንደሚሆኑም ጠቅሰዋል።

ከጉባኤው ጎን ለጎን ተሳታፊዎች የተለያዩ የጤና ተቋማትንና የልማት ሥራዎችን እንደሚጎበኙ ያነሱት አቶ አሸናፊ፤ በዚህም ለሌሎች አካባቢዎች በተሞክሮነት ሊወሰዱ የሚችሉ ሥራዎችን ማጋራት እንደሚገባ አመልክተዋል።
የፊት አመራሩ የሚመራው ዐቢይ ኮሚቴም ከንዑስና ከቴክኒክ ኮሚቴዎች ጋር በመቀናጀት የተከናወኑ ሥራዎች የደረሱበትን ደረጃ አሁናዊ ግምገማ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።

የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ በበኩላቸው፤ በብሔር ብሔረሰቦች በዓል ወቅት በኮሚቴነት ያገለገሉ አካላትን በጤና ጉባኤው አስተባባሪነት በማካተት፣ ያካበቱትን ልምድና ተሞክሮ በመጠቀም ጉባኤው በስኬት እንዲጠናቀቅ በትኩረት ይሠራል ብለዋል።

አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መሰረታዊ የአገልግሎት ግብዓቶችን በማሟላት ለጉባኤው እንግዶች የሚመጥን ጥራት ያለውና ተገቢ አገልግሎት እንዲሰጡ ቀጣይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግም ዋና አስተዳዳሪው አረጋግጠዋል። አክለውም ኮሚቴው የድርጊት መርሃ ግብር በማዘጋጀት የጉባኤውን ሥራ ከያሆዴ በዓል ዝግጅት ጋር በማስተሳሰር በቅንጅት ማከናወን እንዳለበት አሳስበዋል።

የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል ከተከናወኑ ሀገራዊ ሁነቶች የተገኘውን ልምድና ተሞክሮ በመጠቀም የጤና ጉባኤውን በስኬት ለማጠናቀቅ እንደሚሠራ ገልፀዋል። ጉባኤው የከተማዋን የንግድ፣ የቱሪዝምና የመስተንግዶ ዘርፎችን በማነቃቃት ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴውና ለልማት ጉዞው አዎንታዊ አበርክቶ እንደሚኖረውም አመልክተዋል።

የከተማዋ ሕብረተሰብ እንግዶችን በአክብሮትና በፍቅር በመቀበል ለጉባኤው ስኬት የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክትም ጥሪ አቅርበዋል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤም በቆይታው ዘመናዊና ከእጅ ንክኪ ነፃ የሆኑ የጤና አገልግሎቶች ለተሳታፊዎች ተሞክሮ ሆነው እንደሚቀርቡ ገልፀዋል።

ከመስከረም 28/2019 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በሚካሄደው በዚህ ሀገር አቀፍ ጉባኤ ላይ ከ2 ሺህ በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በተካሄደው የግምገማ መድረክ የክልል፣ የዞን፣ የሆሳዕና ከተማና የሌሞ ወረዳ የመንግስትና የፓርቲ ከፍተኛ ኃላፊዎች እንዲሁም የጤና ዘርፍ አመራሮች ተገኝተዋል።

የዉጭ ሀገር የሥራ ስምሪት የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ በህጋዊ መንገድ ብቻ መሄድ አለባቸዉ ሲሉ አቶ መሳይ ተስፋዬ አሳሰቡ፤ሆሳዕና፤ ነሐሴ 18/2018 በሀዲያ ዞን የዉጭ ሀገራት የሥራ ስምሪት ዞናዊ...
24/08/2026

የዉጭ ሀገር የሥራ ስምሪት የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ በህጋዊ መንገድ ብቻ መሄድ አለባቸዉ ሲሉ አቶ መሳይ ተስፋዬ አሳሰቡ፤

ሆሳዕና፤ ነሐሴ 18/2018 በሀዲያ ዞን የዉጭ ሀገራት የሥራ ስምሪት ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ ''የዉጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አቋራጭ መንገድ የለዉም'' በሚል መሪ ቃል በሆሳዕና ተካሄዷል።

በመርሃ ግብሩ ተገኝተዉ መድረኩን የመሩት በሀዲያ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖላቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የመንግስት ረዳት ተጠሪዉ አቶ መሳይ ባስፋዬ ባስተላለፉት መልዕክት፥ በዞናችን ይህ ተግባር ከንቅናቄ ተግባራት አንዱ ተደርጎ ሊመራ ይገባል ብለዋል።

የብልፅግና ፓርቲ እና መሪዉ መንግስት ዋናዉ መርህ የዜጎችን ሁለንተናዊ ክብር፣ዳህንነትና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነዉም ብለዋል።

ዜጎች በሀገራቸዉ ሰርተዉ እንዲለወጡ ሰፋፊ የሥራ ዕድሎች የተፈጠሩ ቢሆንም በዓለም አቀፍ ደረጀ ያለዉን የሥራ ገበያ አማራጭ ለመጠቀም ለሚፈልጉ ዜጎች ህጋዊ፣ዳህንነቱ የተጠበቀና ክብራቸዉን የሚያስጠብቅ የሥራ ስምረት መዘርጋት የመንግስት ኃሊፊነት እንደሆነ የተናገሩት አቶ መሳይ፤

በቀደሙት ዓመታት በርካታ ወገኖቻችን በህገወጥ ደላሎች ተታለዉ በበረሃና በባህር ሲሰደዱ የደረሰባቸዉ እንግልት፣የሕይዎት መጥፋትና የአካል መጉደል መለስ ብለን ሲናስብ እጅግ ዘግናኝ ነዉ ብለዉ፤ አሁን መንግስት ያመቻቸዉን ህጋዊ መንገድ መከተል በእጅጉ አስፋላጊ መሆኑን መገንዘብ ወሳኝ ነዉ ብለዋል።

በዘርፉ ያሉዉን የአመለካከት ችግር ለመፍታት በየማህበራዊ መሰረቱ በሚገኙ የህበረተሰብ ክፍሎች ላይ የግንዛቤ ሥራ ማዘዉተር እንደሚያስፈልግም ኃላፊዉ አሳስበዋል።

አጀንዳዉን ህዝባዊ መሰረት ማስያዝ፣ለተግባሩ ባለቤት የሆነ ተቋም መፍጠርና የመረጀ አያያዝና ልዉዉጥ ስርዓት ማዘመንና የስራ ሪፖርቶችን በወቅቱ ለሚመለከታቸዉ አካላት ማድረስ ትኩረት ከሚሹ አበይት ጉዳዮች ተጠቃሽ እንደሆኑ የተናገሩት አቶ መሳይ

የሀይማኖት ተቋማት መሪዎችን ፣ የሀገር ሽማጊሌዎችንና ተዋቂ ግለሰቦችን በማሳተፍ በህዝባዊ መድረኮ በመምከር መንግስት በህጋዊ መንገድ የሚሄዱን ዜጎች ሀላፊነት እንደሚወስድ በማስረዳት ወንድም እህቶቻችንን እንታደግ ብለዉ፥

ለዚህም ጉዳዩ የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት በሙሉ በቁርጠኝነትና በተከታታይነት ጠንካራ ስራ መሥራት ይጠበቃል ብለዋል።

ሳምንታዊ መልዕክትኢትዮጵያ አሸንፋለች!ኢትዮጵያ ታላቅ የፖለቲካ ምዕራፍ ያበሰረውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤን በድል አጠናቃለች። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ለዓመታት ያካሄደው ሰፊ የምክክር ሂደት በ...
24/08/2026

ሳምንታዊ መልዕክት

ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

ኢትዮጵያ ታላቅ የፖለቲካ ምዕራፍ ያበሰረውን ሀገራዊ ምክክር ጉባኤን በድል አጠናቃለች። ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ለዓመታት ያካሄደው ሰፊ የምክክር ሂደት በአራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት መሠረታዊ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በመመካከር ተጠናቋል።

በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግሥት የሀገራችንን የቆየ የፖለቲካ ስብራቶችን በኃይልና በግጭት ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ በማሳተፍ በሀሳብ፣ በውይይትና በምክክር ለመፍታት የወሰነው ውሳኔ ትልቅ ፍሬ አፍርቷል።

ከአራት ዓመታት በፊት በአዋጅ ቁጥር 1265/2021 የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፥ ከቀበሌ ጀምሮ እስከ ዲያስፖራ ድረስ በሰፊ የህዝብ ተሳትፎ አጀንዳዎችን ሰብስቦ፣ የሀገራችንን መሠረታዊ ጥያቄዎች ወደ ሀገራዊ ውይይት መድረክ አምጥቷል። ይህ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን የወከሉ አራት ቁልፍ ባለድርሻ አካላትን በአጠቃላይ 4 ሺህ ተሳታፊዎችን፣ ከ150 በላይ አማካሪዎችንና 8 ባለ 500 ተመካካሪ ንዑስ ቡድኖችን ያሳተፈ ሰፊ የምክክር ሂደት ሆኗል። ሂደቱም ኮሚሽኑ በመረጠው የምክክር ስነ ዘዴ አላማውን ማሳካት ችሏል። ኋላቀር የጠብመንጃ ፖለቲካ መንገድም ያከተመለት አካሄድ መሆኑን በግልጽ መስክሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሀገራዊ ምክክሩ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል በተመለከተ “ፖለቲካችን በጠንካራ ቃላት ይጀምርና በጠንካራ እርምጃ ይጠናቀቃል፤ ይህ ክፍተት አንድ ጊዜና ለሁልጊዜ መቆም አለበት” የሚል ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ማለት የፖለቲካ ባህላችንን ከግጭት ወደ ውይይት፣ ከኃይል ወደ ሀሳብ፣ ከመሸነፍና ከማሸነፍ የዜሮ ድምር አስተሳሰብ ወደ የጋራ መፍትሔ እና መግባባት ማሸጋገር ነው። በዚህ ዕሳቤ ላይ የፀኑ ኢትዮጵያዊያን ለሀገራቸው ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ለምክክር በቀረቡ አጀንዳዎች ዙሪያ የመፍትሔ ሀሳቦችን አፍልቀዋል። በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ የመነጋገር የመከራከር የመደማመጥ የመፍትሔ መንገዶችን የመጠቆም ባህል አዳብረዋል።

የመደመር ፍልስፍናም ልዩነትን በመካድ ሳይሆን ልዩነትን በመቀበል፣ መደማመጥን በማስፋት፣ እኔነትን ወደ እኛነት በማሸጋገር የጋራ እውነትና የጋራ መፍትሄ መፈለግን ያስቀድማል። በዚህ መንፈስ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሀገራችንን የፖለቲካ ባህል ለመቀየር ትልቅ መሠረት ጥሏል።

ላለፉት 40 ቀናት የተመከረባቸው የሀገረ-መንግሥት ግንባታ፣ የመንግሥት አወቃቀርና የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፌዴራል ከተሞች ጉዳይ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ ተቋማዊ ግንባታና የሕግ የበላይነት፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ ፀረ-ሙስናና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ሰላም ግንባታን ያካተቱ ስምንቱ መሰረታዊ አጀንዳዎች የሀገራችንን የዛሬ ችግሮች ብቻ ሳይሆን፣ የነገ ትውልድ የሚገነባባቸውን የፖለቲካ፣ የማኅበራዊ ሰላም፣ የተቋማትና የኢኮኖሚ መሠረቶች የያዙ ናቸው።

በመሆኑም የሀገራዊ ምክክሩ ድል አሁናዊ አጀንዳ ብቻ ሳይሆን ለነገ ኢትዮጵያ የተጣለ መሠረት ጭምር ነው። የምክክሩ መጠናቀቅ ምክረ ሀሳቦቹን ወደ ተግባር የማዋል አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ ስለሆነ የሁሉም ኢትዮጵያዊን፣ ባለድርሻ አካላት፣ የፖለቲካ ኃይሎችና ተቋማት ቀጣይ ተሳትፎ ይጠበቃል ለዚህም በቁርጠኝነት ልንተጋ ይገባል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በሀዲያ ዞን የዉጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መካሄድ ጀመረ።ሆሳዕና፤ ነሐሴ 18/2018 መድረኩ በዋናነት ለዜ...
24/08/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በሀዲያ ዞን የዉጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መካሄድ ጀመረ።

ሆሳዕና፤ ነሐሴ 18/2018 መድረኩ በዋናነት ለዜጎች በዉጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ከመፍጠር ጋር ተያይዞ እየተሰሩ ያሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በሚመለከት ባለድርሻ አካላት የሚመክሩበት እንደሆነ ተመላክቷል።

ሰዉ ተኮሩ የብልፅግና ፓርቲ እንዲሁም አስፈፃሚዉ መንግስት የዜጎችን ሁለንተናዊ ክብር እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የዞኑ ባለድርሻ የሆኑ ተቋማት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተዉ አበረታች ዉጤት ለማስመዝገብ እንዲሰሩ እንደሚጠበቅ በመድረኩ የተነሰ ሲሆን

በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ምክክር እንደሚደረግና ቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥ ይጠበቃል።

በመርሃ ግብሩ የሀዲያ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖላቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ መሳይ ተስፋዬ፣የዞኑ ምክር ቤት ም/ል አፈ ጉባዔ ክብርት ወ/ሮ ዓለምነሽ ክፍሌን ጨምሮ የሚመለከታቸዉ የዞን፣የወረዳዎችና የከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አመራሮች ተገኝተዋል።

የፌዴራል የድጋፍና ክትትል ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ዓ/ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አፈጻጸምን በመገምገም ላይ ይገኛል ሆሳዕና ነሀሴ 18/2018 ዓ.ም መድረኩ...
24/08/2026

የፌዴራል የድጋፍና ክትትል ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ዓ/ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አፈጻጸምን በመገምገም ላይ ይገኛል

ሆሳዕና ነሀሴ 18/2018 ዓ.ም

መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ፤ አጠቃላይ ሀገራዊ ጉዟችን ለብሔራዊ መግባባት፣ ለዘላቂ ሰላምና ለሁለንተናዊ ብልጽግና ስኬት እጅግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ኃላፊው በንግግራቸው እስከ መስከረም ወር የሚዘልቀው የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፤ በ15ቱም የትኩረት መስኮች የተመዘገበው የእስካሁን አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ሰፊ ውይይት እንደሚደረግበት ገልጸዋል።

አክለውም ከሪፖርት ግምገማው ባሻገርም፣ የፌዴራሉ የሱፐርቪዥን ቡድን በቀጣይ ቀናት ወደ ዞን፣ ወረዳና ቀበሌዎች ድረስ በመውረድ የተሰሩትን ስራዎች በአካል እንደሚመለከቱም ጠቁመዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የፌደራል የሴቶች ክንፍ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የሱፐርቪዥን ቡድን አስተባባሪ ወይዘሮ አሰለፍ ታደሰን ጨምሮ ከፌዴራል የመጡ የስራ ኃላፊዎች፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዐቢይና ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

በመድረኩ በማዕከላዊ ኢትዮጵያክልል መንግስት የ2018 ዓ.ም
የክረምት ወራትየበጎ ፈቃድአገልግሎትየእስካሁን አፈጻጸም
ሪፖርት በክልሉ የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ እየቀረበ ሲሆን በቀጣይ ውይይት የሚደረግበት ይሆናል።

 #ኢትዮጵያ አሸንፋለች !!
24/08/2026

#ኢትዮጵያ አሸንፋለች !!

በልዩነት ላይ በተመሠረተ ፖለቲካ የሚመራው የፖለቲካ ንግድ ግቡን ለማሳካት በሤራ ትንታኔ ላይ ይንጠለጠላል፡፡ በልዩነት ውስጥ የጠላትነት ትርክትን በመፍጠር አንዱን የተጨቆነና አደጋ የተጋረጠበ...
24/08/2026

በልዩነት ላይ በተመሠረተ ፖለቲካ የሚመራው የፖለቲካ ንግድ ግቡን ለማሳካት በሤራ ትንታኔ ላይ ይንጠለጠላል፡፡ በልዩነት ውስጥ የጠላትነት ትርክትን በመፍጠር አንዱን የተጨቆነና አደጋ የተጋረጠበት፣ ሌላውን ደግሞ ጨቋኝና አደጋ ፈጣሪ በማድረግ አግላይ ትርክቶች ይፈጠራሉ፡፡ የተጨቆነውና አደጋ የተጋረጠበት ፍርሃት ይፈጠርበታል፡፡ በሌላኛው ወገን ላይ ደግሞ ጥላቻ እንዲፈጠርበት ይደረጋል፡፡

የመደመር መንግሥት ገጽ 371

በክረምት ወራት የሚደረጉ የስፖርት ውድድሮች ተተኪ ተጫዋቾችን ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገለጸሆሳዕና ነሐሴ 17/2018 በሌሞ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት አዘጋጅነ...
23/08/2026

በክረምት ወራት የሚደረጉ የስፖርት ውድድሮች ተተኪ ተጫዋቾችን ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተገለጸ

ሆሳዕና ነሐሴ 17/2018 በሌሞ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት አዘጋጅነት ለ21 ቀናት ሲካሄድ የቆየው የ2018 ዓ.ም የ"ያሆዴ ካፕ" የክረምት ወራት እግር ኳስ ውድድር ዛሬ ፍጻሜውን አግኝቷል።

በውድድሩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የሌሞ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙልጌታ ገብሬ እንደገለጹት፤ የውድድሩ ዋና ዓላማ ለሀዲያ ሌሞ እግር ኳስ ክለብና ለሌሎች ደረጃዎች ግብዓት የሚሆኑ ታዳጊ ተጫዋቾችን ማፍራት ነው ።

አክለውም የክረምት ወራት የስፖርት ሁነቶች ወጣቶች በስፖርቱ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ዕድል ከመፍጠሩ ባሻገር፣ ከአረጋውያንና አቅመ ደካሞች ቤት እድሳት ጋር ተያይዞ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲሳተፉና በወረዳው የሚገኙ 33 ቀበሌያት ማህበራዊ ትስስራቸውን እንዲያጠናክሩ ማስቻሉን አብራርተዋል።

የሌሞ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ከበደ በበኩላቸው፤ ውድድሩ ለታዳጊዎች ትልቅ እድል የፈጠረ መሆኑን ጠቁመው፣ ወጣቶች በስፖርታዊ ጨዋነት ራሳቸውን በማብቃት ለሀገር ስኬት አጋዥ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

በጽሕፈት ቤቱ የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ሚሻሞ በሰጡት አስተያየት፤ ለውድድሩ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራ ቢሆንም በዘንድሮው መርሃ ግብር 20 ቀበሌያት ብቻ በመሳተፋቸው መጠነኛ የተሳትፎ መቀዛቀዝ መታየቱን ጠቁመዋል።

አክለውም በዞን ደረጃ ቅኝት የተደረገላቸው ከ17 ዓመት በታች የፕሮጀክት ስልጠናዎች ድጋፍና ክትትል የሚሹ በመሆናቸው የሚመለከተው አካል እገዛ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

በተጨማሪም በሆሳዕና ዙሪያ በሚገኙ ቀበሌያት ከከተማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይወረሩ የይዞታ ማረጋገጫ በመስጠት ማካለል መቻሉን አብራርተዋል።

በዕለቱ በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ በዱባንቾ ቀበሌ እና በሰሜን በሌሳ ቀበሌ መካከል የተደረገው ጨዋታ መደበኛ ሰዓት 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከተሎ፣ በተሰጠው የመለያ ምት ዱባንቾ ቀበሌ 5 ለ 3 በማሸነፍ የ2018 ዓ.ም የ"ያሆዴ ካፕ" ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል። ( )

Address

Central Ethiopia Region, Hadiya Zone
Hossana

Telephone

938488197

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኮሚዩኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share