Hadiya Zone Lemo Woreda Government Communication Affairs

Hadiya Zone Lemo Woreda Government Communication Affairs Central Ethiopia Regional Government Hadiya Zone Lemo Woreda Government Communication Affairs office Hossana ,Ethiopia

በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በተመረጡ ትምህርት ቤቶች በጤናና በስርዓተ-ምግብ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።ሆሣዕና፣ግንቦት28/2018ዓ.ም(ሌሞ ኮሚዩኒኬሽን)በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት በ...
05/06/2026

በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በተመረጡ ትምህርት ቤቶች በጤናና በስርዓተ-ምግብ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።

ሆሣዕና፣ግንቦት28/2018ዓ.ም(ሌሞ ኮሚዩኒኬሽን)

በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ለሁለት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን፣ለስርዓት-ምግብ ፎካል እና ለተማሪዎች በስርዓተ-ምግብ አዘገጃጀት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡

በዕለቱም ስልጠናውን የሰጡት በወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ዳንኤል ሙሉጌታ ስለ ምግብ ምንነት፣ አስፈላጊነት እና ምድቦች ሰፊ ስልጠና በሰጡበት ወቅት እንዳሉት የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የስርዓተ-ምግብ ችግርን ለመፍታት የሚሠራ መሆኑን በመግለጽ የህፃናት የመቀንጨር አስከፊነት እንደ ሃገር የሚያደረሰውን አሉታዊ ተፅዕኖ በውል በመረዳት የፕሮግራሙን ተግባር ዳር ለማድረስና ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር ሁላችንም መረባረብ ይገባናል ብለዋል፡፡

አቶ ዳንኤል አያይዘውም ስርዓተ-ምግብ ላይ መስራት ሃገርን መገንባት እና ትውልድን ማስቀጠል በመሆኑ በተወሰደው ስልጠና ልክ ተግባሩም በትኩረት መሰራት እንዳለበት በማሳሰብ በቀጣይ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከር የፕሮግራሙን ዓላማ ከግብ ማድረስ አለብን ብለዋል፡፡

በስልጠናው ላይ የተገኙት የታችኛው አምቢቾና የሹሩሞ ዱባንቾ አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ርዕሳነ መምህራን በሰጡት አስተያየት ስልጠናው ትምህርት ቤቶች የጓሮ አትክልት ሰርቶ ማሳያ ለመስራት ከቦታ መረጣ ጀምሮ የጓሮ አትክልቶችን እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን አቀናጅተው እንዴት መምራት እንዳለባቸው ግንዛቤ እንዳገኙ ገልጸዋል፡፡

ዘጋቢ:-ዕፁብ አዳነ

በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት አስተባባሪነት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት መልቲ ሴክተሮች አዘጋጅነት በሴቶች ገቢ ማስገኛ መንገዶች እንዲሁም ስርዓተ-ምግብ አተገባበር...
05/06/2026

በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት አስተባባሪነት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት መልቲ ሴክተሮች አዘጋጅነት በሴቶች ገቢ ማስገኛ መንገዶች እንዲሁም ስርዓተ-ምግብ አተገባበር ዙሪያ በታችኛው አምቢቾ ቀበሌ ለሚገኙ ነፍሰ ጡርና አጥቢ እናቶች ስልጠና ተሰጠ።

ሆሣዕና፣ግንቦት28/2018 ዓ.ም(ሌሞ ኮሚዩኒኬሽን)

የሌሞ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ባርኮት ሚሻሞ በስልጠናው ወቅት እንደተናገሩት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት መሠረት የህፃናትን የመቀንጨር ችግር ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነም በመግለጽ በፕሮግራሙም የሴቶች የልማት ህብረት በቀበሌው እንዲቋቋም የተደረገው የሴቶችን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከልና የሴቶችን የልማት ጥያቄዎች በራሳቸው አቅም ምላሽ እንዲያገኙ ለማስቻል መሆኑን ጠቁመዋል።

በዕለቱም ስልጠናውን የሰጡት በወረዳው ሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ መልካሙ ከባሞ በበኩላቸው ሴቶች በኢኮኖሚ፣በማህበራዊ እንዲሁም በፖለቲካ ዘርፍ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተው ሴቶች በሁሉም ዘርፎች ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆን አለባቸው ብለዋል ።

አቶ መልካሙ አያይዘውም ሴቶች የራሳቸውን ገቢ እንዴት መፍጠርና ማሳደግ እንዳለባቸው እንዲሁም የህፃናትን የመቀንጨር ችግር ለመቀነስ በወረዳው በ2 ቀበሌያት ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

በወረዳው የህፃናትን የመቀንጨር ችግር ለመቀነስ መንግስት እየሰራ መሆኑን አብራርተው የህፃናትን የመቀንጨር ችግር ለመቀነስ ባለው መሬት የተለያዩ የጎሮ አትክልቶችን በማምረት የተመጣጠነ ምግብ ማግኘት እንደሚቻል ገልፀው በፕሮጀክቱ ዓላማ ላይ ትኩረት በማድረግ የህፃናትን የመቀንጨር ችግር ዜሮ ፐርሰንት ለማድረስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንዳለባቸውም አቶ መልካሙ ከባሞ አብራርተዋል ።

የስልጠናው ተሳታፊዎችም ከስልጠናው ባገኙት ዕውቀት በስርዓተ-ምግብ አተገባበር ዙሪያና እና የራሳቸውን ገቢ በቀላሉ እንዴት ማግኘት እንደሚችሉ ግንዛቤ እንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል።

ዘጋቢ:-ዕፁብ አዳነ

በሀድያ ዞን የሌሞ ወረዳ አስተዳደር በድህረ-ምርጫና የቀጣይ ተግባራት ዙሪያ ውይይት አደረገ።ሆሣዕና፣ግንቦት28/2018(ሌሞ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን) የሌሞ ወረዳ በድህረ-ምርጫና የቀጣይ ተግባራት ...
05/06/2026

በሀድያ ዞን የሌሞ ወረዳ አስተዳደር በድህረ-ምርጫና የቀጣይ ተግባራት ዙሪያ ውይይት አደረገ።

ሆሣዕና፣ግንቦት28/2018(ሌሞ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን)

የሌሞ ወረዳ በድህረ-ምርጫና የቀጣይ ተግባራት ዙሪያ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ከሀድያ ዞን፣ከወረዳውና ከቀበሌ ከመጡ አመራሮች ጋር ውይይት አድርጓል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሼቦ ኡሊሶ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ከቅድመ-ምርጫ እስከ ድህረ-ምርጫ ድረስ በሰላም እንዲጠናቀቅ አመራሩ፣ህብረተሰቡ እና የፀጥታ መዋቅር በጋራ በመቀናጀት ላሳዩት ድጋፍና ትብብር ምስጋና አቅርበዋል።

የሌሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴ በበኩላቸው የወረዳው አመራሮችና ግንባር ቀደም አባላት ሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ላደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበው በቀጣይም እያንዳንዱ ተቋም የተቋሙ ዕቅድ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ በመገምገምና ቀጣይ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ሊረባረብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ ከበደ በድህረ-ምርጫ መስራት የሚጠበቅብንን ሁሉ በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ መስራት እንደሚገባ አሳስበው ባለፉት ጊዜያት በድክመት የተገመገሙና ያልተፈቱ የህዝብ ጥያቄዎችን በድህረ-ምርጫ ወቅት ተግባራትን ለይተን በመስራት ህዝብ መንግስት ላይ የጣለውን እምነት መፈጸም ለሁሉም ባለድርሻ አካላት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል።

ዘጋቢ:-ዕፁብ አዳነ

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አስተባባሪነት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት መልቲ ሴክተሮች አዘጋጅነት ለአጥቢና ነፍሰ ጡር እናቶች የስርዓተ ምግብ ምንነት፣የህፃናት ምግብ አዘገጃጀትና አመ...
04/06/2026

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አስተባባሪነት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት መልቲ ሴክተሮች አዘጋጅነት ለአጥቢና ነፍሰ ጡር እናቶች የስርዓተ ምግብ ምንነት፣የህፃናት ምግብ አዘገጃጀትና አመጋገብ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።

ሆሣዕና፣ግንቦት 27/2018 ዓ.ም(ሌሞ ኮሚዩኒኬሽን)

የሌሞ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት በታችኛው አምቢቾ ቀበሌ ለሚገኙ ነብሰ ጡርና አጥቢ እናቶች ለህፃናት የተስተካከለ አካላዊና አእምሮአዊ እድገት እንዲኖራቸው በተግባር የተደገፈ ስልጠና ተሰጥቷል።

በስልጠናውም ንቁ አዕምሮ ያለው ትውልድ ለመፍጠር የእናቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ እናቶች የተሻለ ትውልድ ለመፍጠር የተመጣጠነ ምግብ በማዘጋጀትና ልጆቻቸውን ሊንከባከቡ እንደሚገባ የገለጹት የሌሞ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የእናቶችና ህፃናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪ አቶ ፀጋዬ አበበ ለእናቶች በተግባር የታገዘ ስልጠና መስጠት ያስፈለገው እናቶች ከስልጠናው በኋላ በአካባቢያቸው ከሚገኙ አትክልትና ፍራፍሬዎች፣የእንስሳት ተዋዕፆችን በአይነት በአይነት በማዘጋጀት ከመቀንጨር ነፃ የሆነ ትውልድን መፍጠር እንዲቻል በቤታቸው ተግባራዊ ማድረግ ስለሚገባቸው መሆኑንንም አስረድተዋል።

በስርዓተ ምግብ ዙሪያ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮጀክት አላማ አድርጎ በያዘው አቅጣጫ መሠረት የታችኛው አምቢቾ ቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ለእናቶች ገለጻ ያደረጉ ሲሆን የተመጣጠነ ምግብ አዘገጃጀት በተግባር የማዘጋጀት ስራ ሰርተው ለህፃናት እና ለእናቶች አቅርበዋል።

በዕለቱ የተገኙ እናቶችም የተመጣጠነ ምግብ አዘጋጅተው ለህፃናት በማቅረብ በኩል ያለባቸውን የአሰራር ክፍተት ሥልጠናው ግንዛቤ እንደፈጠረላቸውና ገልጸዋል።

ዘጋቢ:-ዕፁብ አዳነ

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ የበሌሳ የመጀመሪያ ደረጀ ሆስፒታል ተጀምሮ በበጀት እጥረት ምክንያት ከቆመበት የማስቀጠል መርሃ ግብር በበሌሳ ከተማ ተካሂዷል።ሆሣዕና፣ግንቦት 27/2018ዓ.ም(ሌሞ ኮሚ...
04/06/2026

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ የበሌሳ የመጀመሪያ ደረጀ ሆስፒታል ተጀምሮ በበጀት እጥረት ምክንያት ከቆመበት የማስቀጠል መርሃ ግብር በበሌሳ ከተማ ተካሂዷል።

ሆሣዕና፣ግንቦት 27/2018ዓ.ም(ሌሞ ኮሚዩኒኬሽን)

ሆስፒታሉ በህብረተሰቡ ትብብር ተጀምሮ ግንባታው በበጀት እጥረት ምክንያት ለረጅም ግዜ የተቋረጠ ሲሆን በዛሬው መርሃ ግብርም የግንባታ ስራዉን ለማስቀጠል በዋናነት የዋቸሞ ዩንቨርስቲ በይፋ የተረከበ ሲሆን ሙሉ በሙሉ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ግንባታውን እንደሚያጠናቅቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቃል ገብተዋል ፤በትብብርም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ፣የሀድያ ዞን አስተዳደር እና የሌሞ ወረዳ አስተዳደር ከህዝቡ ጋር በመሆን አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ ግንባታውን እንደሚያጠናቅቁትም ገልጸዋል።

በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ፣የዋቸሞ ዩንቨርስቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ እንዲሁም የሌሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴን ጨምሮ የክልል፣የዋቸሞ ዩንቨርስቲ መኔጅመንት አባላትና የሌሞ ወረዳና የበሌሳ ቀበሌ አመራሮች፣የባህል ሽማግሌዎችና የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

ዘጋቢ:-ዕፁብ አዳነ

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።‎ግንቦት 24 በሀገር አቀፍና በክል...
03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።

ግንቦት 24 በሀገር አቀፍና በክልል ደረጃ የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሌሞ ወረዳ በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴ ለመላው የወረዳው ሕዝብና ባለድርሻ አካላት በሙሉ ታላቅ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎ዋና አስተዳዳሪው ልዩና የላቀ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ያለምንም የጸጥታ ሥጋት በስኬት እንዲጠናቀቅ ቀንና ሌሊት በቁርጠኝነት ሲንቀሳቀሱ ለነበሩት ለፖሊስ ሠራዊት፣ ለሚሊሻ አባላትና በአጠቃላይ ለፀጥታ መዋቅሮች ነው።

‎በመቀጠልም ምስጋናቸውን ሕገ-መንግሥታዊ የመምረጥና የመመረጥ መብቱን በሰለጠነ መንገድ የተጠቀመውን የወረዳውን ሕዝብ ለሀገራዊ የዴሞክራሲ ልምምድ ያበረከተው ታሪካዊ አስተዋጽኦና ያሳየው ወደር የሌለው ጨዋነት ለምርጫው ስኬት ቀዳሚውንና አንበሳውን ድርሻ መውሰዱን ገልጸዋል።

‎አስተዳዳሪው አያይዘውም ምርጫውን በበሰለ የፖለቲካ አመራርና በተደራጀ አግባብ ሲያስተባብሩ ለነበሩት ለወረዳው አስተባባሪዎች፣በየደረጃው ላሉ አመራሮችና አባላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎በተለይም በወረዳው ባሉ የምርጫ ክልሎች በሌሞ 01፣በሶሮ 02 እና በኮንተብ 03 የምርጫ ክልሎች በዕጩነት የቀርቡ ተመራጮች እንዲሁም የምርጫ ሥራዎችን በነቃ ተሳትፎ ሲያስተባብሩ ለነበሩት የብልጽግና ፓርቲ አባላት የላቀ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

‎ለምርጫው ሰላማዊነት፣ ፍትሐዊነትና ዴሞክራሲያዊነት የበኩላቸውን ቀና እና ታሪካዊ አስተዋጽዖ ላበረከቱት ለሌሞ ወረዳ ነዋሪዎች፣ለተለያዩ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ለወጣቶች፣ ለሀገር ሽማግሌዎች፣ ለሃይማኖት አባቶችና ለታዛቢ አካላት በሙሉ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎በወረዳው ሥር በሚገኝ እያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ፣ ሥልጡንና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ተጀምሮ በስኬት እንዲጠናቀቅ መላው ሕዝብ ያሳየው ጨዋነትና ከፍተኛ ንቃት የሚደነቅ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው በድጋሚ ገልጸዋል።

‎በመጨረሻም መራጮች በተባበረ ክንድ ሀገርን በጸና መሠረት ላይ ለማቆም ሲሉ በተለያየ የሌሊት ጨለማና ብርድ፣ የቀን ፀሐይ ሀሩር፣ የዝናብና የጤና ሁኔታ ሳይበግራቸው ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመውረድ ድምፃቸውን በነፃነትና በደስታ ስሜት መስጠታቸውን የጠቆሙት አስተዳዳሪው ለዚህ የሀገር ፍቅር ቁርጠኝነታቸው ላቅ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

‎ይህ የሕዝብ የበላይነትና አሸናፊነት የታየበት ታላቅ መድረክ መሆኑን በመግለጽ "በዚህ ታሪካዊ ሂደት ኢትዮጵያ መርጣለች! ኢትዮጵያ አሸንፋለች!" ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

አቶ ታደለ ደምሴ
‎የሌሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ

‎ኢትዮጵያ መርጣለች! ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን የወረዳው ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ ።ሆሣዕና፣ግንቦት 25/2018 ዓ.ም(ሌሞ ኮሚዩኒኬሽን...
02/06/2026

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን የወረዳው ሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ ።

ሆሣዕና፣ግንቦት 25/2018 ዓ.ም(ሌሞ ኮሚዩኒኬሽን)

በሀዲያ ዞን ሌሞ ወረዳ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላም መጠናቀቁን የወረዳው ሠላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተሻለ የሱፍ አስታውቀዋል ።

በወረዳው በሁሉም ቀበሌያት ባሉት የምርጫ ጣቢያዎች በትናንትናው ዕለት ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 6:00 ሰዓት ያለ ምንም የፀጥታ ችግር በሰላማዊ መንገድ ዜጎች ድምፃቸውን ይበጀኛል ብለው ለሚያስቡት ፓርቲ መስጠታቸውን የገለጹት የወረዳው ሠላምና ፀጥታ ኃላፊ አቶ ተሻለ በቅድመ-ምርጫና በምርጫው ዕለት አጠቃላይ ሂደቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱና ከተቋሙ ጋር ለተባበሩ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የሌሞ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር አሸናፊ መኔቦ በወረዳው 7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በቂ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸው ዜጎች በወረዳው በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች በትናንትናው ዕለት ሰላማዊ በሆነ መልኩ መምረጥ መቻላቸውን ጠቁመው በዛሬው ዕለትም ከሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቁሳቁስ ዕቃዎች ወደ ማዕከል የገቡ መሆኑን ገልጸዋል።

#ኢትዮጵያ መርጣለች_አሸንፋለች!

ዘጋቢ:-ዕፁብ አዳነ

ሕዝቡ ሕጋዊ ካልሆኑ ከማንኛውም ምንጮች ከሚወጡ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች በትላንትናው ዕለት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በከፍ...
02/06/2026

ሕዝቡ ሕጋዊ ካልሆኑ ከማንኛውም ምንጮች ከሚወጡ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች በትላንትናው ዕለት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በከፍተኛ ንቃት እና ትዕግሥት ድምፃቸውን ስለሰጡ አመስግኗል።

በምርጫ ሕጉ መሠረት ውጤት በቦርዱ ይፋ እስከሚሆን ድረስም በትዕግሥት እንዲጠብቁ እና ሌሎች አካላትም ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ከማሰራጨት እንዲቆጠቡ፤ ሕዝቡም ከመሰል መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ ቦርዱ አሳስቧል። (EBC)

"ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅ እና ሊገመግም የሚችል ማን ነው?" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያውያንን ፅናት፣ ሀገር ወዳድነት እና ለሀገረ-መንግሥት ግንባታ ...
02/06/2026

"ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅ እና ሊገመግም የሚችል ማን ነው?"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያውያንን ፅናት፣ ሀገር ወዳድነት እና ለሀገረ-መንግሥት ግንባታ ያለችውን ቁርጠኝነት የገለጹበት መልዕክት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ስራ ያስጀመሩበት ሥነ ሥርዓት በምስል፡-
02/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ስራ ያስጀመሩበት ሥነ ሥርዓት በምስል፡-

Address

Hossana

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya Zone Lemo Woreda Government Communication Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share