01/09/2026
በሀዲያ ዞን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ብ/ኢን/ሥ/ኮሚሽን የ2019 በጀት ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት አፈጻጸም ገመገመ።
25/12/2018 ዓ.ም
ሆሳዕና
በሀዲያ ዞን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ብ/ኢን/ሥ/ኮሚሽን የ2019 በጀት ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት አፈጻጸም ገምግሟል። በግምገማው መድረክ የሆሳዕና ከተማ ብልጽግና ኢ/ስ/ም/ኮ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ደጉ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ኦረንቴሽን መድረክ አፈጻጸም እንዲሁም የእቅድና የፈጻሚ ዝግጅት ሪፖርት አቅርበው በኮሚሽን አባላት ውይይት የተደረገበት ሲሆን በቀጣይም በ2019 በጀት ዓመት ከብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ጋር ተግባቦት በመፍጠርና የጋራ አቋም በመያዝ ለፓርቲያችን ጥንካሬ እሴት የሚጨምሩ ጉዳዮች ላይ ሊሰራ እንደሚገባ ተነስቷል። በዚህም መሠረት ከዚህ በፊት በኢንስፔክሽን ወቅት በተደጋጋሚ የታዩና መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች በጽ/ቤቱ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ አንጬቴ አዲሴ ቀርቦ በስፋት ውይይት በማድረግ በቀጣይ በነዚህ ጉዳዮች ላይ ከፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ጋር ተግባቦት ለመፍጠር አቅጣጫ በማስቀመጥ የእለቱ መድረክ ተጠናቋል።
ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርት!