Awi Communication

Awi Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Awi Communication, Government Official, Spantov.

16/03/2026
10/03/2026
ማንነትን ለመለየትና የተጠያቂነትን አሰራር በተገቢው ተግባራዊ ለማድረግ የፋይዳ መታወቂያ ጠቀሜታው የጎላ ነው ፦አቶ ወሃቤ ፀጋ የዳንግላ ወረዳ ተቀዳሚ ም/አስተዳዳሪ  የካቲት 17/2018ዓም ...
24/02/2026

ማንነትን ለመለየትና የተጠያቂነትን አሰራር በተገቢው ተግባራዊ ለማድረግ የፋይዳ መታወቂያ ጠቀሜታው የጎላ ነው ፦አቶ ወሃቤ ፀጋ የዳንግላ ወረዳ ተቀዳሚ ም/አስተዳዳሪ

የካቲት 17/2018ዓም ዳንግላ ኮሙኒኬሽን

በአዊ ብሔረሰብ አስተዳዳር በዳንግላ ወረዳ በብሔራዊ ፋይዳ መታወቂያ አወጣጥና ጠቀሜታ ዙሪያ የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡

በምክክር መድረኩ ላይም የወረዳ አመራሮች፣የኢትዮጵያን ንግድ ባንክ ዳንግላ ቅርጫፍ እና የኢቲዮ ቴሌኮም የዳንግላ አገልግሎት ማዕከል የስራ ኅላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የዳንግላ ወረዳ ተቀዳሚ ም/አስተዳዳሪ አቶ ወሃቤ ፀጋ የፋይዳ መታወቂያ ትክክለኛ የህዝብ ቁጥርን በተገቢው ለማወቅ፣የአርሶ አደሩን የመሬት ባለቤትነትን ለማረጋገጥ እና የኢኮኖሚ እድገትን ለመጨመር ያግዛል ብለዋል፡፡ ዘላቂነት ያለው ገቢን ለማሳደግና የሚፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለመቀነስም ድርሻው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ማንነትን ለመለየትና የተጠያቂነትን አሰራርን በተገቢው ተግባራዊ ለማድረግ የፋይዳ መታወቂያ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው የግብርና ግብዓትን ስርጭት የሚያቀላጥፍ ስለሆነ ሁሉም ዜጋ የፋይዳ መቃወቂያ ማውጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

የዳንግላ ወረዳ መሬት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተሰማ ግርማ የመወያያ ፅሑፉን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት የፋይዳ መታወቂያ የአርሶ አደሩ የመሬት መረጃ በተገቢው ሁኔታ ለመያዝ፣ የመሬት የኪራይ ገቢን ከመጨመሩ ባለፈ የፋይናንስ ስርዓትን በማስፋፋት የብድርና ቁጠባ አገልግሎትን በትክክል ለማግኘት እንደሚያግዝ ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም የዳንግላ አገልግሎት ማዕከል ኃላፊ ወ/ሮ ሃይማኖት ላቃቸው ማህበረሰቡ ከተለያዩ ማጭበርበሮች ለመከላከልና ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ ለማድረግ የፋይዳ መታወቂያ ጥቅሙ ከፍያለ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም ሁሉም ዜጋ ምዝገባውን ከኢትዮ ቴሌኮም በተጨማሪ በባንኮች በኩል የምዝገባ ሂደቱን በመፈፀም የፋይዳ መታወቂያውን መያዝ እንዳለበት ወ/ሮ ሀይማኖት ተናግረዋል፡፡

24/02/2026
የቻግኒና የጓንጓ ወረዳ ብልፅግና ጽ/ቤት የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ  የምርጫ ምልክት ይፋ አደረገ።በደመቀ ሁኔታ በተከናወነው በዚህ የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር ላይ  የአዊ ብ/አስ ዋ...
18/02/2026

የቻግኒና የጓንጓ ወረዳ ብልፅግና ጽ/ቤት የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የምርጫ ምልክት ይፋ አደረገ።

በደመቀ ሁኔታ በተከናወነው በዚህ የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር ላይ የአዊ ብ/አስ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለውን ጨምሮ የከተማዋ ፣የወረዳው እና የ አዊ ብ/አስ አመራሮች ተገኝተዋል።
የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫን ብልፅግናችን ያሸንፋል!
Awi Communication

28/12/2025

FOLLOW👇
Awi Communication
Official Pages

‎የቻግኒ (ቻ-ጝኒ) ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማት ስራ ዲዛይን‼‎
28/12/2025

‎የቻግኒ (ቻ-ጝኒ) ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማት ስራ ዲዛይን‼

"አንድ አካባቢ የሽፍትነት አስተሳሰብን የሚከንከባከብና የሚደግፍ ከሆነ ለልማትና ለአብሮነት ተመራጭ አይሆንም"    ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)
18/12/2025

"አንድ አካባቢ የሽፍትነት አስተሳሰብን የሚከንከባከብና የሚደግፍ ከሆነ ለልማትና ለአብሮነት ተመራጭ አይሆንም"

ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)

"አንድ አካባቢ የሽፍትነት አስተሳሰብን የሚከንከባከብና የሚደግፍ ከሆነ ለልማትና ለአብሮነት ተመራጭ አይሆንም"-ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)ፈንድቃ: ታኅሣሥ 09/2018 ዓ....
18/12/2025

"አንድ አካባቢ የሽፍትነት አስተሳሰብን የሚከንከባከብና የሚደግፍ ከሆነ ለልማትና ለአብሮነት ተመራጭ አይሆንም"-ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)

ፈንድቃ: ታኅሣሥ 09/2018 ዓ.ም (አዊ ኮሙኒኬሽን ) የአብክመ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በአዊ ብሄ/አስ በፈንድቃ ከተማ አስተዳደሩ እና ከጃዊ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪዎች ጋር እየተወያዩ ነው።

በውይይቱ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአሥተዳደር ክላስተር አሥተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ.ር)፣በኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የምዕራብ ዕዝ የ404ኛ ህዳሴ ኮር ዋና አዛዥ ብ/ጀኔራል ንጉስ ለውጤ ፣የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዋና አሥተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተገኝተዋል።

የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የህዝቡ ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል።

የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት የችግሩ መነሻ ምክንያቶችን በመለየት የሰላም ግንባታን ማፋጠን ይገባል ነው ያሉት

አካባቢው ሰፊ የሥራ ዕድል የሚፈጥር ግዙፍ የስኳር ፋብሪካ እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን አብቃይ መሬት ባለቤት ነው ብለዋል።

ነገር ግን ባለፉት ሁለት አመት ተኩል የተፈጠረው የጸጥታ ችግር የአካባቢው ሕዝብ ጸጋውን እንዳይጠቀም አድርጎታል ነው ያሉት።

የሰላም እጦቱ በትውልድ ላይ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በህዝብ ባህል እና እሴት ጫና ማሳደሩንም ነው ያነሱት።

አብዛኛው የአዊ ብሄ/አሰ ህዝብ የአካባቢው ሰላም ለመጠበቅ መስዋትነት ሲከፍል መቆየቱን ያነሱት ም/ር/ርዕሰ መስተዳድሩ ጃዊ አካባቢ ግን ግጭቱ እንዲራዘም በርካታ አካላት አስተዋጽኦ ነበራቸው ነው ያሉት።

ስለሆነም " ሽፍትነትን የሚንከባከብና የሚደግፍ አካባቢ ለልማትና ለአብሮነት ተመራጭ እንደማይሆን "ነው የገለፁት።

የተፈጠረው የሰላም ችግር በሌሎች አካባቢ ህዝብ ላይ ሆደባሻነትን አስከትሎ ሳለ የብዙ ፀጋ ባለቤት የሆነው ጃዊ እና አካባቢው ህዝብ የውስጥ አንድነት (የአብሮነት) ጉድለት እና አለመተማመን በስፋት ተስተውሏል ብለዋል።

የመንግሥት እና የህዝብ ግንኙነት በመተማመን በመደማመጥ ላይ የተመሠረተ ከሆነ ሰላም እና ልማት እንደሚመጣ ነው የገለፁት።

ስክነት እና መተማመን ከሌለ ግን የሰላም ትሩፋትን ማግኘት አይቻልም ነው ያሉት። ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ደግሞ መወያየት ያስፈልጋል ብለዋል።

የአዊ ብሔ/አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው በበኩላቸው ጃዊና አካባቢው መሬት ልዩ ፀጋ ያለበት እና ይህንን ፀጋ ህዝብና መንግስት በአግባቡ እንዳይጠቀም በተደጋጋሚ ግጭት የሚፈጠርበት አካባቢ ነው ብለዋል።

አካባቢው ለብሔ/አስተዳደሩ፣ ለክልሉ ብሎም ለሀገራችን የኢኮኖሚ የስበት ማዕከል የሚሆን አካባቢ ነው ያሉት አስተዳዳሪው ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥ የሁሉም አካላት ተቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል ሲሉ ገልፀዋል ።

የፈንድቃ ከተማና የጃዊ ወረዳ ማህበረሰብም ሰላምን በፍላጎት ብቻ ከመግለፅ ባሻገር በተግባራዊ እንቅስቃሴ ማረጋገጥ አለበት ሲሉ አብራርተዋል ።

የአገው ህዝብ ሁለንተናዊ ተቋም!! አረንጓዴው  ዩንቨርስቲ በሚልም ይታወቃል እንጅባራ ዩንቨርስቲ ‼
18/12/2025

የአገው ህዝብ ሁለንተናዊ ተቋም!!
አረንጓዴው ዩንቨርስቲ በሚልም ይታወቃል እንጅባራ ዩንቨርስቲ ‼

ለአንጋፋው 86ኛ ለአገው ፈረሰኞች በዓል በድምቀት እንዲከበር ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራን እንገኛለን። ኑ በውቢቷ እንጅባራ ጥር23ን በጋራ እናክብር!!
04/12/2025

ለአንጋፋው 86ኛ ለአገው ፈረሰኞች በዓል በድምቀት እንዲከበር ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራን እንገኛለን።
ኑ በውቢቷ እንጅባራ ጥር23ን በጋራ እናክብር!!

Address

Spantov

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Awi Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Awi Communication:

Share