Somali Regional State Communication Bureau

Somali Regional State Communication Bureau Ensure a smooth flow of information between the Regional Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information

Objectives
1. Ensure smooth flow of information between the Regional Government and the public and facilitate the process of building a society enriched with information and actively participate in the country’s affairs and, in particular, facilitate the creation of equal opportunities for those people and of the community that need special support in accessing government information.
2. Putting t

he constitutions basic principles and values on the community in wide and continuous way
3. Enhance the responsiveness of the Regional Government to the needs of the society through maintaining an efficient and effective communication service.

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎቱን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በጥምረት እየሠራ እንደሆነ አስታወቀ #ጅግጅጋ:-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአገልግሎት አሰጣጡን ...
03/09/2026

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎቱን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በጥምረት እየሠራ እንደሆነ አስታወቀ

#ጅግጅጋ:-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአገልግሎት አሰጣጡን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ እና ተደራሽነቱን ለማስፋት የሚያስችለውን ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በጥምረት እየተገበረ መሆኑን ገልፆአል።

የተቋሙ የውስጥ የኃይል ማመንጨት ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን እንደገለጹት፣ አሰራሩን ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችል በጥናት የተደገፈ የኢንቨስትመንት ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል።

አቶ ኤፍሬም አክለው እንዳብራሩት፣ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ራዕይን ለማሳካት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ በመሆኑ ተቋማቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል።

የኃይል አቅርቦትን ማዲጂታላይዝ ማድረግ የአገልግሎት ተደራሽነትን በማረጋገጥ ረገድ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው፣ በዘርፉ አጠቃላይ እድገት ለማምጣት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሆነ ጠቁመዋል።

የሀገሪቱ ኃይል የማመንጨት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን የጠቆሙት ኃላፊው፣ የዲጂታል ስርዓቱን በመተግበር አገልግሎቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ልዩ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሆነ አስረድተዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት‎‎"በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮ...
03/09/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

‎"በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።

‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።

‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።"

‎ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
‎👇
https://linktr.ee/Warfaafinta
Somali Regional State Communication Bureau

 በኢ.ፌ.ድ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ ዘርፍ ለማገልገል ፍላጎት ያላችሁ የክልላችን ነዋሪዎች በሙሉየኢ.ፌ.ድ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ ...
02/09/2026


በኢ.ፌ.ድ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ ዘርፍ ለማገልገል ፍላጎት ያላችሁ የክልላችን ነዋሪዎች በሙሉ

የኢ.ፌ.ድ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ (Attaché) የሥራ መደብ ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል።

- የሥራ መደብ፦ አታሼ (Attaché)
- የሚቀጠሩ ሰዎች ብዛት፦ 100
- ደመወዝ፦ ብር 12,566
- የማመልከቻ ጊዜ፦ 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት

ተፈላጊ ችሎታ ፦ በማንኛውም ትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ

- ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ

🖊️ምዝገባው አዲስ አበባ በወጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲሱ ህንጻ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 በአካል በመቅረብ ወይም ከዚህ በታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይቻላል

https://forms.gle/R7PmwCNeqEE3EQBN6

ለበለጠ መረጃ+251- 115 522 079

የኢ.ፌ.ድ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

በሶማሌ ክልል ቆረሄይ ዞን ዶብ ወይን ከተማ በ250 ሚሊዮን ብር የተገነባ  ሆስፒታል ተመረቀ #ጅግጅጋ:- በሶማሌ ክልል ቆረሄይ ዞን ዶብ ወይን ከተማ በ250 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የመጀ...
02/09/2026

በሶማሌ ክልል ቆረሄይ ዞን ዶብ ወይን ከተማ በ250 ሚሊዮን ብር የተገነባ ሆስፒታል ተመረቀ

#ጅግጅጋ:- በሶማሌ ክልል ቆረሄይ ዞን ዶብ ወይን ከተማ በ250 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኢብራሂም ዑስማን ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደረገ።

ተመርቀ‍ኦ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው አዲሱ ሆስፒታል ለዶብ ወይን ከተማና ለአካባቢው ነዋሪዎች የላቀ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት ከ100 ሺህ በላይ የጤና አገልግሎት ፈላጊዎችን እንደሚያስተናግድ ተጠቁሟል።

ሆስፒታሉን መርቀው የከፈቱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢብራሂም ኡስማን መንግሥት ለጤናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው፣ የሆስፒታሉ ተጠናቆ ክፍት መደረግ ይህንኑ ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

አክለውም የሕዝቡን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማሻሻል የሆስፒታሎችን፣ የጤና ጣቢያዎችንና ኬላዎችን ግንባታ በስፋት እያካሄደ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በምረቃው ላይ የክልሉ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ሀላፊ ዶ/ር ሁሴን ቃሲም፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሙሳ አህመድ፣ የመስኖ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ ፋታህ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ማጠቃለያ ላይ በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አከናውነዋል።
Somali Regional State Communication Bureau
Xafiiska Warfaafinta Deegaanka Somalida

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ #ጅግጅጋ:-መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች ይከበራሉ አለ የመ...
02/09/2026

መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራሉ

#ጅግጅጋ:-መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች ይከበራሉ አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፡፡

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፥ የተገባደደው ዓመት የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ ጅማሮ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገበበት ነው ብለዋል፡፡

በዚህም ምክንያት መጪዎቹ የጳጉሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ስያሜዎች እንደሚከበሩ አመልክተዋል፡፡

ጳጉሜን 1 – የእመርታ ቀን – ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ተላቅቃ ወደ ፈጣንና እመርታዊ የእድገት ምህዋር መግባቷን የምናሳይበት ቀን ነው ብለዋል፡፡

ይህ ዕለት በሁሉም ዘርፍ የተሰሩ ሥራዎችን እመርታዊ ለውጥ የምናስገነዝብበት ይሆናል ነው ያሉት፡፡

ጳጉሜን 2 – የማንሰራራት ቀን – 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ እድገት ወደ ሁለንተናዊ ከፍታ መሸጋገር የጀመረችበት ቀን በመሆኑ ዕለቱ የማንሰራራት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡

ጳጉሜን 3 – የጽናት ቀን በሚል ስያሜ ይከበራል፤ ኢትዮጵያ ለዘመናት በጽናት ጠብቃው የኖረችውን ነጻነትና ሉዓላዊነት ማስቀጠል የዛሬው ትውልድ ኃላፊነት መሆኑን ለማስገንዘብ ዕለቱ የጽናት ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡

ጳጉሜን 4 – የኅብር ቀን

ኢትዮጵያ የብዝሃ ማንነቶች ሀገር እንደመሆኗ ብዝሃነት ጌጣችንና ኅብረታችን ነው፤ ኅብረታችን ደግሞ የአንድነትና የጥንካሬያችን ምንጭ መሆኑን በማውሳት፤ ዕለቱ የኅብር ቀን መባሉን አስረድተዋል፡፡

ጳጉሜን 5 – የነገ ቀን የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ዓላማውም ኢትዮጵያ ነገዋን ዛሬ እየሰራች እንደምትገኝ ማስገንዘብ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው ።‎‎ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም‎‎እየተጠናቀቀ በሚገኘዉ 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በማንሰራ...
02/09/2026

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው ።

‎ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

‎እየተጠናቀቀ በሚገኘዉ 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶችን እንዳስመዘገበች የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ የዘንድሮ የጳጒሜን ቀናት የሚከበሩበትን ዓውድ፣ የቀናቱን ስያሜ እና መሪ መልእክት ይፋ ያደረገበትን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

‎መግለጫዉን የሰጡት የአገልግሎቱ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ከበደ ዴሲሳ “ጳጒሜን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ወር ብሎ ለማክበር የሚያስችሉ ስኬቶች እየተጠናቀቀ ባለው ዓመት መመዝገባቸውን ገልጸዋል ፡፡

‎ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ቴክኖሎጂ ነክ ዓመታዊ ስኬቶችን በመግለጫቸዉ ያነሡት ሚኒስትር ድኤታዉ የጳጒሜን ቀናት በልዩ ልዩ ስያሜዎች እና ኹነቶች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አመላክተዋል፡፡ አካታች፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተሳተፉበት ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተካሄደበት፣ ኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን በፅኑ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ አካታች እና የነበሩ ልዩነቶችን በመፍታት የጋራ ትልሞች ላይ እንዲተኮር የሚያስችል ሀገራዊ ምክክር በስኬት የተጠናቀቀበት፣ የውስጥ አንድነቷ የተጠናከረ እና የዲፕሎማሲ ዐቅሟ ያደገች ኢትዮጵያ የታየችበት ዓመት እንደነበር አቶ ከበደ በመግለጫቸዉ አመላክተዋል፡፡

‎ከኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አንጻር የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ለመፍጠር በወቅታዊ ዓለማቀፋዊ ቀውሶች ጭምር ታልፎ ስኬት የተመዘገበበት፣ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር የተቻለበት፣ የዕዳ ጫና በከፍተኛ ደረጃ የቀነሰበት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅም ከ1.5 ትሪሊዮን ብር የተሻገረበት፣ የኢንዱስትሪ ምርታማነት እና የውጭ ምንዛሪ ግኝት ታሪካዊ ዕድገት ያስመዘገበበት፣ የወጪ ንግድ ገቢ ከ10.2 ቢሊዮን ዶላር የተሻገረበት፣ በአንድ ዓለማቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ብቻ ከ13.2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የኢንቨስትመንት የመግባቢያ ሰነድ የተፈረመበት እና በአብዛኛዉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወደ ማውጣት ደረጃ የተሸጋገሩበት፣ የግብርና ምርት እና ምርታማነት በጋ ከክረምት በግብዓት አቅርቦት ታግዞ በከፍተኛ ደረጃ የጨመረበት ስኬታማ ዓመት ነበር፡፡

‎የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ያስቻሉ ከ100 በላይ የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎቶች የተስፋፉበት፣ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በፅኑ መሠረት የሚያስቀምጥ እና ማኅበራዊ መስተጋብርን የሚያጎለብት ስኬታማ ምክክር የተደረገበት፣ የሕዝቡን የማኅበራዊ መሻቶች ለማሳካት ሰፋፊ የበጎ አድራጎት እና የመሠረተ ልማት ማስፋፋት ሥራዎች የተከወኑበት በውጤቱም ኢትዮጵያን ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበት ዕድገት ማሸጋገር የተቻለበት ዓመት እንደነበር ክቡር አቶ ከበደ በመግለጫቸዉ አመላክተዋል፡፡

‎በታዳሽ ኃይል አቅርቦት፣ ግዙፍ መሠረታዊ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት እና ዐዳዲስ መሠረተ ልማቶችን ወደ ግንባታ በማስገባት የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶችንም ዳስሰዋል፡፡ የዐፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ እና የቢሾፍቱ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጀመር ከሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል በክቡር ሚኒስትር ድኤታዉ በአብነት ተነሥተዋል፡፡ እነዚህን ስኬቶች፣ ከተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እና በዕቅድ ከተያዙ ሀገራዊ ትልሞች ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ መኾኗንም አመላክተዋል፡፡
‎የጳጒሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል የጋራ መሪ መልእክት ይከበራሉ፡፡
‎ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፣
‎ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን፣
‎ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን፣
‎ጳጉሜን 4- የኅብር ቀን እና
‎ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን በሚሉ ስያሜዎች እንደ ቅደም ተከተላቸዉ በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበሩ ያስታወቁት ሚኒስትር ድኤታዉ ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል፡፡

‎ዜጎች በዐዲስ ዓመት ለግል ስኬቶቻቸዉ እንደሚያቅዱት ኹሉ ለኹለንተናዊ ሀገራዊ ብልጽግናም የሚጫወቱትን ሚና ታሳቢ እንዲያደርጉ፣ የመንግሥትን ፖሊሲ እና ስትራቴጂ እንዲሁም ዕቅድ ተገንዝበዉ ተሳትፏቸዉን እንዲያሳድጉ ለማነሣሣት ቀናቱ እንደሚከበሩም ገልጸዋል፡፡ የጳጒሜን ቀናቱን ስያሜ መሠረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄዎች፣ የበጎ አድራጎት እና ማዕድ ማጋራት ተግባራት፣ ነፃ ጤና ምርመራ፣ የደም ልገሳ፣ የፓናል ውይይት እና መሰል መርሐ ግብሮች እንደሚኖሩም አስታውቀዋል፡፡

‎ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
‎👇
https://linktr.ee/Warfaafinta

በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የተመራ ልዑክ በሸበሌ ዞን እና ጎዴ ከተማ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ #ጅግጅጋ:- በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም...
01/09/2026

በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የተመራ ልዑክ በሸበሌ ዞን እና ጎዴ ከተማ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

#ጅግጅጋ:- በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን የተመራ ልዑክ በሸበሌ ዞን እና ጎዴ ከተማ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ሀላፊ ሁሴን ሀሺ (ዶ/ር) እና ከተለያዩ የክልሉ አመራሮች ጋር በመሆን በሸበሌ ዞን እና ጎዴ ከተማ አስተዳደር በመካሄድ ላይ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎቶች ለማስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ለማፋጠን የሚያስችሉ እንዲሁም የህዝቡን ግኑኝነትና ትስስር የሚያጠናክሩ ሲሆኑ ፕሮጀክቶቹ የብልፅግና ፓርቲ የልማት ኢኒሼቲቮች ትግበራና በክልሉ መንግስት ትኩረት የሰጣቸው ዕቅዶች አካል ናቸው ተብሏል።

በክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን የተመራው ልዑክ የልማት ፕሮጀክቶቹን ትግበራ ፣የጥራት ሁኔታ እና የደረሱበትን የአፈፃፀም ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክቷል።

ጉብኝቱ በሸበሌ ዞን እና በጎዴ ከተማ እየተካሄዱ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች በሚፈለገው ሁኔታ እና ለህብረተሰቡ የልማት ፍላጎቶች ምላሽ በሚሰጥ ሁኔታ እየተካሄዱ መሆናቸውን ለመገምገም ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

አመራሮቹ የልማት ፕሮጀክቶቹ ቀሪ ስራዎች እንዲፋጠኑ እና ፕሮጀክቶቹን በጥራትና በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ የፕሮጀክቶቹን የግንባታ አላማ እንዲሳካ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በአቶ ኢብራሂም ኡስማን የተመራ ልዑክ በሸበሌ ዞን የስራ ምልከታ በማካሄድ ላይ ነው #ጅግጅጋ:-በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን የተመራ ልዑክ በሸበሌ ዞን የስራ ...
01/09/2026

በአቶ ኢብራሂም ኡስማን የተመራ ልዑክ በሸበሌ ዞን የስራ ምልከታ በማካሄድ ላይ ነው

#ጅግጅጋ:-በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን የተመራ ልዑክ በሸበሌ ዞን የስራ ምልከታ በማካሄድ ላይ መሆኑን ተገልጿል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ሀላፊ ሁሴን ሀሺ (ዶ/ር) ጨምሮ ከተለያዩ የክልሉ አመራሮች ጋር በመሆን በሸበሌ ዞን የብልፅግና ፓርቲ የልማት ኢኒሼቲቮች እና መንግስት ትኩረት የሰጣቸው ዕቅዶች ትግበራን ለመገምገም ያለመ የስራ ምልከታ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።

በክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን የተመራው ልዑክ ከሸበሌ ዞን እና ከጎዴ ከተማ አመራሮች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት የልማት ዕቅዶቹ ትግበራ እና የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶ የቀረበውን ሪፖርት አዳምጠዋል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር በዚህ ወቅት የሸበሌ ዞን እና የጎዴ ከተማ አመራሮች በፓርቲው እና በመንግስት የተቀመጡ ዕቅዶችን በፍጥነት ወደ ተግባር ለማስገባት በትኩረት እንዲሰሩ አሳስበዋል።

የታቀዱ እቅዶችን ወደ ተግባር በማሸጋገር ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲያደርጉና የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዲችሉ የአመራሮቹ ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዘበዋል።

በተለያዩ የአመራር እርከኖች ያለው የተጠያቂነት፣ ክትትልና ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የፓርቲው የልማት እንቅስቃሴዎች የተቀመጡትን ዓላማዎች ለማሳካት አመራሩ የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ አሳስበዋል።

ይህ ምልከታ የፓርቲውን እቅድ አፈፃፀም ለማረጋገጥ፣የነበሩ ክፍተቶችን በማረም እና ለተቀመጠው ተግባር ትክክለኛ ውጤት በየደረጃው የሚገኘውን አመራር ተጠያቂነትን ለማሳደግ የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑን ተገልጿል።

የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ መስራችና የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶ/ር አብዲናስር አህመድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ #ጅግጅጋ:- የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ መስራችና ለ10ዓመታት በፕሬዝደንትነት የመሩ...
01/09/2026

የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ መስራችና የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶ/ር አብዲናስር አህመድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

#ጅግጅጋ:- የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ መስራችና ለ10ዓመታት በፕሬዝደንትነት የመሩት ዶክተር አብዲናስር አህመድ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ለኮሚዩኒኬሽን ቢሮ በላከው መግለጫ ዩኒቨርስቲው ሲቋቋም የመጀመሪያ መሠረት የጣሉት እና ለ10 ዓመታት ያህል በመምራት ህዝባቸውን ባገለገሉት በዶ/ር አብዲናስር ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልፆአል።

ዩኒቨርሲቲው ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ጠንካራ መሠረት እንዲኖረው፣ እያደገ እና እየበለጸገ እንዲቀጥል ታላቅ ታሪካዊ ሚና መጫወታቸውን ጠቁሟል።

በሀላፊነት ዘመናቸው በሰጡት የረዥም ጊዜ ራዕይ፣ ፈር ቀዳጅ አመራር እና ታማኝ አገልግሎት በዩኒቨርሲቲውና በአጠቃላይ ማህበረሰቡ ላይ የማይረሳ አሻራ ጥለው ያለፉት የእኚህ ምሁር ውርስ ለቀጣዩ ትውልድ መነሳሳትን የሚፈጥርና ሁሌም የሚታወስ እንደሆነም ጠቁሟል።

የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በመግለጫው፣ በእኚህ ታላቅ ምሁር ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልፆ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለጅግጅጋ ዩኒቨርሰቲ ማኅበረሰብ እና ለመላው የክልሉ ሕዝብ መጽናናትን በመመኘት አላህ ጀነትን እንዲሰጣቸው ተመኝቷል።

የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ መሥራችና የመጀመሪያው ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶክተር አብዲናሲር አህመድ ዩኒቨርሲቲው ከተመሠረተበት ከመጋቢት 1999 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 2009 ዓ.ም. ድረስ ህዝብን ደከመኝና ሰለቸኝ ሳይሉ ያገለገሉ ምሁር ነበሩ።

የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ በእኚህ ታላቅ ምሁር ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ፣ ለቤተሰብ፣ወዳጅ፣ ዘመድ፣ ለዩኒቨርስቲው ማህበረሰብና ለመላው የክልሉ ህዝብ መፅናናትን ይመኛል።

Address

Infront Of Jigjiga University Referal Hospital
Jijiga
251(365)

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Somali Regional State Communication Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Somali Regional State Communication Bureau:

Shortcuts

Share